Wolaita Sodo Mehal Ketema Kale Heywet Church

Wolaita Sodo Mehal Ketema Kale Heywet Church ሠላም ለእናንተ ይሁን !
ይህ ትክክለኛው የወላይታ ሶዶ መሀል ከተማ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ገጽ ነው። ከእኛ ጋር ስለነበሩ እናመሰግናለን🥰

ይህን መግለጫ በአክብሮት ተቀብያለሁ። ቤተክርስቲያኗ በእውነት በፍቅር እና በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት ላይ ቆማ እንድትጓዝ ያላችሁን ጥረት እጅግ አከብራለሁ።እኔም እንደ አንድ ኣጥብያ የቤተክርስቲ...
23/05/2026

ይህን መግለጫ በአክብሮት ተቀብያለሁ። ቤተክርስቲያኗ በእውነት በፍቅር እና በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት ላይ ቆማ እንድትጓዝ ያላችሁን ጥረት እጅግ አከብራለሁ።
እኔም እንደ አንድ ኣጥብያ የቤተክርስቲያኗን ሥርዓት አንድነት እና መንፈሳዊ እድገት በሙሉ እደግፋለሁ። በዚህ ዘመን ከመከፋፈል ይልቅ በጸሎት በፍቅር እና በመተባበር እንድንቆም ያስፈልጋል።
‘እርስ በርሳችሁ በፍቅር ተባበሩ እንደሚል የእግዚአብሔር ቃል ሁላችንም ለወንጌል ክብር በአንድነት እንቁም።
እግዚአብሔር ቤተክርስቲያኗን ይባርክ መሪዎቿንም ጥበብና ጸጋ ይስጥ። አሜን::

      የትምህርት እና የአምልኮ ጊዜ በመሀል ከተማ ቃለ ህይወት ቤተክርስቲያን  በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ተከታታይ ትምህርት ክፍል 3 በፓስተር ማሎታ ማጋ ዛሬ ዕረቡ ስለሚቀጥል ከ11:00 ጀም...
20/05/2026



የትምህርት እና የአምልኮ ጊዜ በመሀል ከተማ ቃለ ህይወት ቤተክርስቲያን
በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ተከታታይ ትምህርት ክፍል 3 በፓስተር ማሎታ ማጋ ዛሬ ዕረቡ ስለሚቀጥል ከ11:00 ጀምሮ መፀሀፍ ቅዱስና ማስታወሻ በመያዝ በጊዜ እንድትገኙ በጌታ ፍቅር እንጋብዛለን።

Wolaita S**o Mehal Ketema Kale Heywet Church

አፌ. 4:11 አንብበን ስአገልግሎት የተሰጠ ጸጋ እንጂ ስለሹመትና ሥልጣን ማውራት የምንችልበት ምክንያት አይታየኝም። 👉 ክፍሉ ላይ ክርስቶስ የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ባለቤትና የጸጋ ሥጦታ...
20/05/2026

አፌ. 4:11 አንብበን ስአገልግሎት የተሰጠ ጸጋ እንጂ ስለሹመትና ሥልጣን ማውራት የምንችልበት ምክንያት አይታየኝም።

👉 ክፍሉ ላይ ክርስቶስ የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ባለቤትና የጸጋ ሥጦታዎች ምንጭ ነው።

ክርስቶስ የቤተ ክርስቲያን መሥራችና ባለራዕይ የአካሉ ራስና ባለቤት ነው። የጸጋ ሥጦታዎችን ለቤተ ክርስቲያን መታነጽና ዕድገት የሰጠው እርሱ ነው። “እርሱም አንዳንዶቹ ሐዋርያት፥ ሌሎቹም ነቢያት፥ ሌሎቹም ወንጌልን ሰባኪዎች፥ ሌሎቹም እረኞችና አስተማሪዎች እንዲሆኑ ሰጠ” (ኤፌ. 4:11) ይላል። እዚህ ክፍል ላይ “እርሱም” የተባለው ሞትን ድል አድርጎ የተነሳው ክርስቶስ ነው። ትንሽ ከፍ ብለን ስናነብብ:- “ነገር ግን እንደ ክርስቶስ ስጦታ መጠን ለእያንዳንዳችን ጸጋ ተሰጠን።” (ኤፌ. 4:7) “ሰጠ” የሚለውም ቃል የሥጦታው ባለቤትና ምንጭ እርሱ ክርስቶስ መኾኑን የሚናገር ነው። በክፍሉ ላይ ጉልህ ሥፍራ የተሰጠው ለሰጪው ነው። ምርኮን የማረከው ለሰዎችም ሥጦታ የሰጠው እርሱ ነው። “አንዳንዶቹ” የሚለው ደግሞ የአገልግሎት ሥጦታዎችን እንደፈቀደ የሚሰጥ መኾኑን የሚገልጽ ነው። እዚህ ክፍል ላይ የክርስቶስን ሥልጣን እንጂ የሰዎችን ሥልጣን አንመለከትም ሰጪውና አድራጊው እርሱ ነው። ክፍሉ ስለ ሰጪው ሥልጣንና ፈቃድ እንጂ ስለተቀባዮች ሹመት አይናገርም።

በዚህ መሠረት ወደ ላይ ለወጣው፥ ምርኮ ለማረከው፥ ጸጋን እንደፈቃዱ ለሰዎች ለሰጠው ለክርስቶስ የበላይነት ዕውቅና የማይሰጥ የሥጦታ ተቀባይን ሹመትና ሥልጣን አገዛዝና የበላይነት የሚናገር ሰውን ሿሚ የኾነ የትኛውም ልምምድ የጤናማ ቤተ ክርስቲያን ልምምድ አይደለም። ይህ ክፍል የሚያጎላው ከሞት የተነሳውን ምርኮ የማረከውን ሥጦታ ለሰዎች የሰጠውን ክርስቶስን የሚያከብር ነው። በዚህ ዘመን ባለቤትና ባለ አደራ የማይለይበት ሁኔታ እየመጣ መኾኑ ምን ያህል ሐሰት የገነነ ለመኾኑ ማስረጃ ነው። በማቴዎስ ወንጌል 16:18 ላይ ጌታችን ሲናገር:- “… ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ” ብሏል። የቤተ ክርስቲያን መሥራች የራዕዩም ባለቤት አምላክ እንጂ ሰው አይደለም። ቤተ ክርስቲያን የቤተ እምነት መሪዎች፥ የመጋቢያንና የሌሎች አገልጋዮች አይደለችም። ፈቃዱ እየተጠየቀ እርሱ ወደ ወደደው አቅጣጫ የምትመራ እንጂ ቤተ ክርስቲያን ማንም እንደወደደ የሚንፈላሰስባት የሰው ሠራሽ ተቋም አይደለችም። እንግዲህ ይህንን ክፍል (አፌ. 4:11) በውል ለመረዳት የርሱን ባለቤትነት እውቅና በመስጠት መጀመር ተገቢ ነው።

👉 በክፍሉ መሠረት የአገልግሎት ጸጋ አማኞችን ወደ ብስለት ለማሳደግ እንጂ አገልጋዮችን ለማግዘፍ አይደለም።

በዚህም ረገድ እዚህ ክፍል ሹመትና ሥልጣን አይታይም። ክፍሉ ለሰዎች የተሰጠ የሹመት ሥርዓት ወይም ሰዎች እንዲሾሙ የተላለፈ መመሪያ ስለመኾኑ ምንም ፍንጭ አናይም። በክፍሉ ላይ title or ranks or institutional authority እንዳለ ለማስመሰል የሚፈልጉ ሰዎች “ለራስ ሲቆርሱ አያሳንሱ” ዓይነት የሥልጣን ጥም ያናወዛቸው ናቸው እንጂ ክፍሉ ሰጪውን ከፍ አድርጎ ተናግሮ ሲያበቃ ሥጦታዎቹ የተሰጡበትን ዓላማ ወደ መዘርዘር ትኩረቱን ያዞራል። እነዚህ የጸጋ ሥጦታዎች (የአገልግሎት ዘርፎች) ለቤተ ክርስቲያን የተሰጡበትን ምክንያት ስንመለከት የNAR ሐሰተኞች እንደሚሉት የአመራር የበላይነት ወይም አገዛዝ (leadership authority) ሳይኾን አገልግሎት ሰጪነት ነው።

ካዉንስሉ ማንነቱን አዉቀዉ እንኳ ያልጨረሱት 4 ሺህ ቸርችጋ የካዉንስሉ አባል ነዉ ብለን ኮንፍራንስ ህብረት አናደርግም። ከመካነ ኢየሱስ ሙሉ ወንጌልና ከቀደምት አብያተ ክርስቲያናት ማለት ግን...
18/05/2026

ካዉንስሉ ማንነቱን አዉቀዉ እንኳ ያልጨረሱት 4 ሺህ ቸርችጋ የካዉንስሉ አባል ነዉ ብለን ኮንፍራንስ ህብረት አናደርግም። ከመካነ ኢየሱስ ሙሉ ወንጌልና ከቀደምት አብያተ ክርስቲያናት ማለት ግን አይደለም።
ዶ/ር ስምዖን ሄሊሶ የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ፕሬዝደንት

የካዉንስሉ ህልዉና በቤተ ክርስቲያናት ላይ የተመሰረተ ነዉ። የቤተ ክርስቲያናት ሕልዉና ግን በካዉንስሉ ላይ አይደለም። ካዉንስል ለመመስረት ሲቋቋም በግርግር ስለነበር ተጠንቶ፤ ተሰርቶ፤ ተዘርዝሮ አይደለም! ሕጉ መዉጣት ስላለበት በችኮላ የተቋቋመ ነዉ።

በስደቱ ዘመን የኢትዮጵያ አብያተ ክርስቲያናት ሕብረት የሚባል ነበረ። በዚያ ሂደት ዉስጥ መድረክ መጋራት፤ እርስ በርስ እጅና ጓንት ሆኖ መስራት ለምሳሌ ሕዝቡ በወቅቱ መካነ ኢየሱስ ወደጠራችዉ ኮንፍራንስ ቢሄድ ቃለ ሕይወት አትቆጣም። አንዱ ወደ ሌላኛዉ ቢሄድ አትቆጣም ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን!
አብሮ የማገልገል፤ አብሮ የመዉጣት በጋራ ኮንፍራንስ አድርገን አዳዲስ ወደ ጌታ የመጡ ነፍሳት ካሉ አንተ ያኛዉ ይቀርብሃል፤ አንተ ለመኖሪያህ ይሄ ይቀርብሃል ብለን ተባብለን ነበር ያለፍንባቸዉ ጊዜዎች ነበሩ።

ነገር ግን ካዉንስሉ ዉስጥ ወደ 4 ሺህ ቤተ እምነት የሚባሉ አሉ። ማንነቱን አዉቀዉ እንኳ ያልጨረሱት ቸርች ጋራ የካዉንስሉ አባል ነዉና ብለን ኮንፍራንስ ህብረት አብረነዉ አናደርግም። እንደዛ የሚባል የዋህነት የለም።

ከመንግስት ጋር የሚኖር ጉዳይ ሲኖር ስራዉ የተሳለጠ እንዲሆን ከካዉንስሉ ጋር እንሰራለን እንጂ ከአባል ቤተ እምነት ከተባሉት ሁሉ ጋር አንድ ነን ማለት አይደለም።

በመከባበር በወንድማማችነት ላይ የተመሰረተ ካልሆነ በሕግ እርምጃ ወስደን የቃለ ሕይወትን ዋስትና መብት እናስጠብቃለን። በካዉንስሉ ካሉት ሁሉ ጋር ሕብረት ሊኖረን አይችልም። ገደብ አድርገናል። ከመካነ ኢየሱስ፤ ከሙሉ ወንጌልና ከቀደምት አብያተ ክርስቲያናት ማለት ግን አደለም።
ሕግ አዉቆት ስራ ለመጀመር የመጀመሪያም ስለነበር ካዉንስል ለመመስረት ግርግር ስለነበረ በዚያ ግርግር ዉስጥ ተጠንቶ፤ ተሰርቶ፤ ተዘርዝሮ አደለም ሲቋቋም! ሕጉ መዉጣት ስላለበት በችኮላ ነዉ።

የካዉንስሉ ህልዉና በቤተ ክርስቲያናት ላይ የተመሰረተ ነዉ። የቤተ ክርስቲያናት ሕልዉና ግን በካዉንስሉ ላይ አደለም።

ከራሳቸዉ ለማድመጥ👇
https://www.facebook.com/reel/1477596107393757/?app=fbl

      የትምህርት እና የአምልኮ ጊዜ በመሀል ከተማ ቃለ ህይወት ቤተክርስቲያን  በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ተከታታይ ትምህርት ክፍል 2 በፓስተር ማሎታ ማጋ ዛሬ ዕረቡ ስለሚቀጥል ከ12:00 ጀም...
12/05/2026



የትምህርት እና የአምልኮ ጊዜ በመሀል ከተማ ቃለ ህይወት ቤተክርስቲያን
በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ተከታታይ ትምህርት ክፍል 2 በፓስተር ማሎታ ማጋ ዛሬ ዕረቡ ስለሚቀጥል ከ12:00 ጀምሮ መፀሀፍ ቅዱስና ማስታወሻ በመያዝ በጊዜ እንድትገኙ በጌታ ፍቅር እንጋብዛለን።

Wolaita S**o Mehal Ketema Kale Heywet Church

‎🛑    “ ” የሚለውን ቃል በቀጥታ ለቢሮ መጠሪያነት ከመጠቀም ይልቅ፣ የሐዋርያዊ አገልግሎት ዋና መገለጫ የሆኑትን የወንጌል ተልዕኮ (Mission) እና የቤተ ክርስቲያን ተከላ (Church...
06/05/2026

‎🛑 “ ” የሚለውን ቃል በቀጥታ ለቢሮ መጠሪያነት ከመጠቀም ይልቅ፣ የሐዋርያዊ አገልግሎት ዋና መገለጫ የሆኑትን የወንጌል ተልዕኮ (Mission) እና የቤተ ክርስቲያን ተከላ (Church Planting) ተግባራትን በመስራት መገለጥ እንዳለበት ታምናለች።

‎በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ "ቢሮ" የሚለው ቃል በአሁኑ ጊዜ እኛ እንደምንረዳው "ወንበር"፣ "ሥልጣን" ወይም "ክፍል" በሚል ትርጉም አልተቀመጠም። የግሪኩ ቃል "ዶማታ" (Domata) የሚለውን ሲጠቀም ትርጉሙም "ስጦታዎች" ማለት ነው።

ክርስቶስ ለቤተክርስቲያን የሰጣት ስጦታዎች እንጂ ለሰዎች የተሰጠ የሹመት ማዕረግ ላይ ያተኮረ አይደለም።አምስቱ አገልግሎቶች ክርስቶስ ለቤተክርስቲያኑ ዕድገት የሰጣቸው የጸጋ ስጦታዎች እንጂ፣ ግለሰቦች ራሳቸውን ከፍ የሚያደርጉባቸው የሹመት ወንበሮች ባለመሆናቸው "አገልግሎቶች" ወይም "ስጦታዎች" ማለት ይበልጥ መንፈሳዊ ትርጉሙን ይገልጸዋል።

‎ ቤተ ክርስቲያን "ሐዋርያዊ አገልግሎት" ስትል እንደ ግል ማዕረግ ሳይሆን እንደ ተልዕኮ (Mission) ነው የምትረዳው።

‎የቤተ ክርስቲያኗ ሐዋርያዊ አገልግሎት በዋናነት በሦስት ትላልቅ ዘርፎች ይከፈላል :-

‎1. የወንጌል ስርጭት እና የቤተ ክርስቲያን ተከላ (Evangelism and Church Planting)

‎ይህ የቤተ ክርስቲያኗ "ሐዋርያዊ ልብ" የሚታይበት ዘርፍ ነው።ወንጌል ያልተሰማባቸውን አካባቢዎች መድረስ ዋና ግቧ ነው። በአሁኑ ወቅት ቤተ ክርስቲያኗ ከ12,000 በላይ አጥቢያዎች ያሏት ሲሆን፣ ይህ የመጣው በየገጠሩና በየከተማው በሚላኩ የወንጌል ሰራተኞች ጥረት ነው።

‎2. የዓለም አቀፍ ሚሲዮን አገልግሎት (Cross-Cultural Missions)

‎ቤተክርስቲያኗ ሐዋርያዊ አገልግሎት ከኢትዮጵያ ድንበር አልፎ ወደ ተለያዩ የዓለም ሀገራት ተዘርግቷል።
‎ቤተ ክርስቲያኗ ከ1,500 በላይ የሙሉ ጊዜ ሚሲዮናውያን አሏት። እነዚህ አገልጋዮች በጎረቤት ሀገራት (እንደ ደቡብ ሱዳን፣ ኬንያ) እና በሌሎች የዓለም ክፍሎች (እንደ ፓኪስታንና ሕንድ) ድረስ በመሄድ ወንጌልን ይሰብካሉ፣ አብያተ ክርስቲያናትን ይተክላሉ። ቤተ ክርስቲያኗ ከአፍሪካ ቀዳሚ ሚሲዮናውያንን ከሚልኩ አብያተ ክርስቲያናት አንዷ እንደሆነች ይታወቃል።

‎3 .ሁለንተናዊ አገልግሎት (Holistic Ministry)

‎ሐዋርያዊ አገልግሎት በቃሉ ብቻ ሳይሆን በተግባርም መገለጥ አለበት የሚል ጽኑ እምነት አላት። ቤተ ክርስቲያኗ "ሙሉ ወንጌል ለሙሉ ሰው" በሚል መርህ ትምህርት ቤቶችን፣ የጤና ተቋማትን እና የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶችን ከወንጌል ስርጭት ጎን ለጎን ታከናውናለች። ቤተ ክርስቲያኗ "የመሃይምነት ዘመቻ" በማካሄድና ሰዎችን በማንበብና መጻፍ በማብቃት ሐዋርያዊ ሚናዋን ተወጥታለች።

‎በአጠቃላይ ቤተ ክርስቲያኗ ሐዋርያዊ አገልግሎት ማለት ወንጌል ያልደረሰበት ቦታ መድረስ፣ አጥቢያ መትከልና ለክርስቶስ ምስክር መሆን ነው ብላ ታምናለች።

“ኢየሱስ ክርስቶስ ትናንትና ዛሬ እስከ ለዘላለምም ያው ነው።”
— ዕብራውያን 13፥8

       የትምህርት እና የአምልኮ ጊዜ በመሀል ከተማ ቃለ ህይወት ቤተክርስቲያን  በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ተከታታይ ትምህርት በፓስተር ማሎታ ማጋ ዛሬ ዕረቡ ስለሚቀጥል ከ12:00 ጀምሮ መፀሀ...
06/05/2026



የትምህርት እና የአምልኮ ጊዜ በመሀል ከተማ ቃለ ህይወት ቤተክርስቲያን
በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ተከታታይ ትምህርት በፓስተር ማሎታ ማጋ ዛሬ ዕረቡ ስለሚቀጥል ከ12:00 ጀምሮ መፀሀፍ ቅዱስና ማስታወሻ በመያዝ በጊዜ እንድትገኙ በጌታ ፍቅር እንጋብዛለን።

Wolaita S**o Mehal Ketema Kale Heywet Church Workineh Abraham

" ነገር ግን ሐሰተኞች ነቢያት ደግሞ በሕዝቡ መካከል ነበሩ እንዲሁም በመካከላችሁ ደግሞ ሐሰተኞች አስተማሪዎች ይሆናሉ፤ እነርሱም የዋጃቸውን ጌታ እንኳ ክደው የሚፈጥንን ጥፋት በራሳቸው ላይ ...
21/04/2026

" ነገር ግን ሐሰተኞች ነቢያት ደግሞ በሕዝቡ መካከል ነበሩ እንዲሁም በመካከላችሁ ደግሞ ሐሰተኞች አስተማሪዎች ይሆናሉ፤ እነርሱም የዋጃቸውን ጌታ እንኳ ክደው የሚፈጥንን ጥፋት በራሳቸው ላይ እየሳቡ የሚያጠፋ ኑፋቄን አሹልከው ያገባሉ፤"
(2ኛ የጴጥሮስ መልእክት 2:1)

3394 likes, 148 comments. “ 💗 ”

19/04/2026
19/04/2026

እሁድ ማለዳ የአምልኮ ጊዜ

Address

S**o
60021

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Wolaita Sodo Mehal Ketema Kale Heywet Church posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Wolaita Sodo Mehal Ketema Kale Heywet Church:

Share

Category