06/05/2026
🛑 “ ” የሚለውን ቃል በቀጥታ ለቢሮ መጠሪያነት ከመጠቀም ይልቅ፣ የሐዋርያዊ አገልግሎት ዋና መገለጫ የሆኑትን የወንጌል ተልዕኮ (Mission) እና የቤተ ክርስቲያን ተከላ (Church Planting) ተግባራትን በመስራት መገለጥ እንዳለበት ታምናለች።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ "ቢሮ" የሚለው ቃል በአሁኑ ጊዜ እኛ እንደምንረዳው "ወንበር"፣ "ሥልጣን" ወይም "ክፍል" በሚል ትርጉም አልተቀመጠም። የግሪኩ ቃል "ዶማታ" (Domata) የሚለውን ሲጠቀም ትርጉሙም "ስጦታዎች" ማለት ነው።
ክርስቶስ ለቤተክርስቲያን የሰጣት ስጦታዎች እንጂ ለሰዎች የተሰጠ የሹመት ማዕረግ ላይ ያተኮረ አይደለም።አምስቱ አገልግሎቶች ክርስቶስ ለቤተክርስቲያኑ ዕድገት የሰጣቸው የጸጋ ስጦታዎች እንጂ፣ ግለሰቦች ራሳቸውን ከፍ የሚያደርጉባቸው የሹመት ወንበሮች ባለመሆናቸው "አገልግሎቶች" ወይም "ስጦታዎች" ማለት ይበልጥ መንፈሳዊ ትርጉሙን ይገልጸዋል።
ቤተ ክርስቲያን "ሐዋርያዊ አገልግሎት" ስትል እንደ ግል ማዕረግ ሳይሆን እንደ ተልዕኮ (Mission) ነው የምትረዳው።
የቤተ ክርስቲያኗ ሐዋርያዊ አገልግሎት በዋናነት በሦስት ትላልቅ ዘርፎች ይከፈላል :-
1. የወንጌል ስርጭት እና የቤተ ክርስቲያን ተከላ (Evangelism and Church Planting)
ይህ የቤተ ክርስቲያኗ "ሐዋርያዊ ልብ" የሚታይበት ዘርፍ ነው።ወንጌል ያልተሰማባቸውን አካባቢዎች መድረስ ዋና ግቧ ነው። በአሁኑ ወቅት ቤተ ክርስቲያኗ ከ12,000 በላይ አጥቢያዎች ያሏት ሲሆን፣ ይህ የመጣው በየገጠሩና በየከተማው በሚላኩ የወንጌል ሰራተኞች ጥረት ነው።
2. የዓለም አቀፍ ሚሲዮን አገልግሎት (Cross-Cultural Missions)
ቤተክርስቲያኗ ሐዋርያዊ አገልግሎት ከኢትዮጵያ ድንበር አልፎ ወደ ተለያዩ የዓለም ሀገራት ተዘርግቷል።
ቤተ ክርስቲያኗ ከ1,500 በላይ የሙሉ ጊዜ ሚሲዮናውያን አሏት። እነዚህ አገልጋዮች በጎረቤት ሀገራት (እንደ ደቡብ ሱዳን፣ ኬንያ) እና በሌሎች የዓለም ክፍሎች (እንደ ፓኪስታንና ሕንድ) ድረስ በመሄድ ወንጌልን ይሰብካሉ፣ አብያተ ክርስቲያናትን ይተክላሉ። ቤተ ክርስቲያኗ ከአፍሪካ ቀዳሚ ሚሲዮናውያንን ከሚልኩ አብያተ ክርስቲያናት አንዷ እንደሆነች ይታወቃል።
3 .ሁለንተናዊ አገልግሎት (Holistic Ministry)
ሐዋርያዊ አገልግሎት በቃሉ ብቻ ሳይሆን በተግባርም መገለጥ አለበት የሚል ጽኑ እምነት አላት። ቤተ ክርስቲያኗ "ሙሉ ወንጌል ለሙሉ ሰው" በሚል መርህ ትምህርት ቤቶችን፣ የጤና ተቋማትን እና የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶችን ከወንጌል ስርጭት ጎን ለጎን ታከናውናለች። ቤተ ክርስቲያኗ "የመሃይምነት ዘመቻ" በማካሄድና ሰዎችን በማንበብና መጻፍ በማብቃት ሐዋርያዊ ሚናዋን ተወጥታለች።
በአጠቃላይ ቤተ ክርስቲያኗ ሐዋርያዊ አገልግሎት ማለት ወንጌል ያልደረሰበት ቦታ መድረስ፣ አጥቢያ መትከልና ለክርስቶስ ምስክር መሆን ነው ብላ ታምናለች።
“ኢየሱስ ክርስቶስ ትናንትና ዛሬ እስከ ለዘላለምም ያው ነው።”
— ዕብራውያን 13፥8