Soddo Christian Hospital

Soddo Christian Hospital Soddo Christian Hospital is located in southern Ethiopia where there is limited healthcare available for a population of more than 10 million people.

እጅግ በጣም የምንወዳቸውን እና የምንናፍቃቸውን ሚሲዮናዊያንን ወደ ሀገራቸው አሜሪካ ሸኝተናቸዋል!ከዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ ወደ ሀገራችን ኢትዮጵያ መጥተው ላለፉት በርካታ ዓመታት በሶዶ ...
20/05/2026

እጅግ በጣም የምንወዳቸውን እና የምንናፍቃቸውን ሚሲዮናዊያንን ወደ ሀገራቸው አሜሪካ ሸኝተናቸዋል!

ከዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ ወደ ሀገራችን ኢትዮጵያ መጥተው ላለፉት በርካታ ዓመታት በሶዶ ክርስቲያን አጠቃላይ ሆስፒታል እንዲሁም በሌሎችም የኢትዮጵያ ክፍሎች በሕክምና ሚሲዮናዊነት እጅግ በጣም በከፍተኛ ርህራሄ፣ ፍቅር እና ትህትና ማህበረሰባችንን በሕክምና አገልግሎት ያገለገሉትን ሚሲዮናዊያንን፦ ዶ/ር ማርክ ካርነስ (የማሕጸን እና ጽንስ ሕክምና ሐኪም) እና ባለቤታቸው አሊሰን ካርነስ፣ ጆይ ፒየርሰን (የአይ.ሲ.ዩ ነርስ)፣ ዶ/ር ቲም ላቭ (የአጠቃላይ ቀዶ ሕክምና ሐኪም፣ የፓን አፍሪካን አካዳሚ ኦፍ ክርስቲያን ሰርጅንስ ፕሮግራም ዳይሬክተር) እና ባለቤታቸው ላውራ ላቭ ከነልጆቻቸው በዚህ ያለውን የአገልግሎት ጊዜያቸውን ስለጨረሱ በክብር ሸኝተናቸዋል።

ሚሲዮናዊያኑ ለሀገራችን ኢትዮጵያ ደግሞም ለሶዶ ክርስቲያን አጠቃላይ ሆስፒታል በሚሲዮን አገልግሎት፣ ድሆችን በመርዳት፣ ካላቸው በማካፈል፣ ሕሙማንን በነጻ በማከም ወዘተ … እጅግ በጣም ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያበረከቱ ከመሆናቸውም በላይ ሆስፒታሉ አሁን ላይ ለደረሰበት የሕክምና አድማስ እና ቴክኖሎጂ ትልቅ መሠረት የጣሉም ናቸው። በኢትዮጵያ በነበራቸው የአገልግሎት ጊዜ እጅግ በጣም ደስተኞች መሆናቸውን እና ሀገራችንን እንደቤታቸው እንደሚያስቡም ገልጸዋል።

በአገልግሎታቸው በርካቶች ተፈውሰዋል፣ ልጅ መውለድ ያልቻሉ ወልደዋል፣ ያለቀሱ ተጽናንተዋል፣ በርካቶች የኢየሱስ ክርስቶስን ፍቅር ተካፍለዋል። እያዘኑ እና እያለቀሱ ወደ ሆስፒታላችን ለመጡ እልፍ ታካሚዎች በደስታ እና በሳቅ ለመመለሳቸው ምክንያት መሆን ችለዋል።

ዶ/ር ቲም ላቭ በሆስፒታሉ የአጠቃላይ ቀዶ ሕክምና ሐኪም በመሆን እንዲሁም የ ፓን አፍሪካን አካዳሚ ኦፍ ክርስቲያን ሰርጅንስ ፕሮግራም ዳይሬክተር ሆነው ለበርካታ ዓመታት በትጋት ያገለገሉ ሚሲዮናዊ ሲሆኑ በዛሬው ሽኝታቸው የሥራ ኃላፊነታቸውን ለምክትላቸው ዶ/ር ገዛኸኝ ጥላሁን አስረክበዋል። በኢትዮጵያ በነበራቸው ቆይታ እጅግ በጣም ደስተኛ እንደነበሩ የገለጹ ሲሆን ወደፊትም ከሆስፒታሉ ጋር ሊሠሩ እንደሚችሉ ተናግረዋል፤ ለሆስፒታሉ አጠቃላይ ሠራተኞች “እግዚአብሔርን ነው የምታገለግሉት ወይስ ሥራ ብቻ ነው የምትሠሩት” የሚል ጥያቄን በማቅረብ እግዚአብሔርን ልናገለግል እንደሚገባን በምክራቸው አሳስበውናል።

የሆስፒታሉ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ኤፍሬም ገ/ሥላሴ ፣ ምክትል ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር አብርሃም አዴ እንዲሁም የሥራ ክፍል ኃላፊዎች ሚሲዮናዊያኑ ስለ ሠሯቸው ሥራዎች ከፍተኛ አድናቆትን እና ምስጋናን አቅርበዋል።

ማስታወቂያቀን፡ 11-09-2018የሶዶ ክርስቲያን ሆስፒታል ኃላ.የተ.የግ.ማህበር የጠቅላላ ሐኪም ባለሙያዎችን አወዳድሮ ለመቅጠር ባለው ፍላጎት በቁጥር SCH-586-10-18 በቀን 30-8-20...
19/05/2026

ማስታወቂያ
ቀን፡ 11-09-2018
የሶዶ ክርስቲያን ሆስፒታል ኃላ.የተ.የግ.ማህበር የጠቅላላ ሐኪም ባለሙያዎችን አወዳድሮ ለመቅጠር ባለው ፍላጎት በቁጥር SCH-586-10-18 በቀን 30-8-2018 ዓ.ም ባወጣው ማስታወቂያ መሠረት የተመዝገባችሁና ፈተና የተፈተናችሁ-

ጠቅላላ ድምር 75 እና ከዚያ በላይ ያመጣችሁ ተወዳዳሪዎች ያለፋችሁ ስለሆነ በቀን 13/09/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ወደ ሆስፒታሉ ቅጥር ግቢ አስተዳደር ቢሮ ቀርባችሁ የቅጥር ፎርማሊቲ እንድታሟሉና ስትመጡ ከ8ኛ ክፍል ጀምሮ ያሉትን የትምህርት ማስረጃ original እና softcopy ይዛችሁ እንድትቀርቡ ማስፈለጉን ጭምር እንገልፃለን፡፡

ሁሌም ለላቀ የሕክምና አገልግሎት እንተጋለን!
ሶዶ ክርስቲያን አጠቃላይ ሆስፒታል
አድራሻችን፦ ወ/ሶዶ ከጉታራ በስተጀርባ እንገኛለን
ለበለጠ መረጃ: 0465511164 ይደውሉ
ጤና ነክ የሆኑ መረጃዎችን በየጊዜው ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ይከታተሉ
https://t.me/soddochristiangeneralhospital
በጤና ይቆዩ !

ማስታወቂያቀን፡ 10/09/2018የሶዶ ክርስቲያን ሆስፒታል ኃላ.የተ የግ ማሀበር የጠቅላላ ሐኪም ባለሙያን አወዳድሮ ለመቅጠር ባለው ፍላጎት በቁጥር SCH-586-10-18 በቀን 30-8-2018...
18/05/2026

ማስታወቂያ
ቀን፡ 10/09/2018
የሶዶ ክርስቲያን ሆስፒታል ኃላ.የተ የግ ማሀበር የጠቅላላ ሐኪም ባለሙያን አወዳድሮ ለመቅጠር ባለው ፍላጎት በቁጥር SCH-586-10-18 በቀን 30-8-2018 ዓ.ም ባወጣው ማስታወቂያ መሠረት የተመዘገባችሁና የጽሑፍ ፈተና የተፈተናችሁ፡-

የጽሑፍ ፈተና ውጤት 20 እና ከዚያ በላይ ያመጣችሁ ተወዳዳሪዎች ዛሬ በቀን 10/09/2018 ክቀነ- 08:30 ሰዓት ላይ ለቃለመጠይቅ ፈተና ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያና ቀደም ሲል ያቀረባችሁትን ዶክሜንት original copy በመያዝ ወደ ሆስፒታሉ አስተዳደር ሕንፃ እንድትቀርቡ ማስፈለጉን እያስታወቅን መታወቂያ ሳይዝ የሚቀርብ ተወዳዳሪ ለፈተና መቅረብ የማይችል መሆኑን ጭምር በጥብቅ እናስታውቃለን፡፡

ሁሌም ለላቀ የሕክምና አገልግሎት እንተጋለን!
ሶዶ ክርስቲያን አጠቃላይ ሆስፒታል
አድራሻችን፦ ወ/ሶዶ ከጉታራ በስተጀርባ እንገኛለን
ለበለጠ መረጃ: 0465511164 ይደውሉ
ጤና ነክ የሆኑ መረጃዎችን በየጊዜው ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ይከታተሉ
https://t.me/soddochristiangeneralhospital
በጤና ይቆዩ !

16/05/2026
ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ፤የሶዶ ክርስቲያን አጠቃላይ ሆስፒታል ኃላ/የተ/ግ/ማ ባለው ክፍት የሥራ ቦታ ጠቅላላ ሐኪም (General Practitioner) አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል፤ብዛት ...
08/05/2026

ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ፤

የሶዶ ክርስቲያን አጠቃላይ ሆስፒታል ኃላ/የተ/ግ/ማ ባለው ክፍት የሥራ ቦታ ጠቅላላ ሐኪም (General Practitioner) አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል፤

ብዛት = 03
ፆታ = ወንድ/ሴት
የሥራ ቦታ = ሶዶ ክርስቲያን አጠቃላይ ሆስፒታል ቅጥር ግቢ

መስፈርት፤

1ኛ/ ከታወቀ ዩኒቨርስቲ ወይም ኮሌጅ በጠቅላላ ሐኪምነት (General Practitioner) ሙያ ሠልጥኖ/ና ስለመመረቃቸው የሰለጠኑበት ዩኒቨርሲቲ/ኮሌጅ ዲግሪና ትራንስክርፕት ኮፒ ያለው/ያላት፤
2ኛ/ የሥራ ልምድ 0 ዓመትና ከዚያ በላይ ያለው/ያላት፤
3ኛ/ እንግሊዝኛ ቋንቋ ችሎታ ያለው/ያላት፤
4ኛ/ ጊዜው ያላለፈ የሙያ ፈቃድ ምዝገባ ማስረጃ ኮፒ የሚያቀርብ/የምታቀርብ፣
5ኛ/ የመግቢያ የቃለ መጠይቅ ፈተና ላይ የሚቀርብ/የምትቀርብ፡፡
6ኛ/ ሆስፒታሉ በሥራው አስገዳጅነት የሚያወጣውን የሥራ ፕሮግራም ተቀብሎ ለመሥራት ፈቃደኛ የሚሆን/የምትሆን፤
7ኛ/ በእነዚህ መስፈርቶች መሠረት በወጣው ማስታወቂያ ተወዳድሮ ለመቀጠርየሚፈልግ ማመልከቻና በማመልከቻቸው ላይ ስለራሱ/ሷ ምስክርነት ሊሰጡ የሚችሉ 3 ሰዎች ስም ዝርዝር ስልክ፡- (ሞባይል/መደበኛ) ጋር ጠቅሶ/ጠቅሳ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ07 ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ ወደ ሆስፒታሉ መዝገብ ቤት ድረስ ቀርቦ/ባ መመዝገብ የሚችል/የምትችል መሆኑን እናስታውቃለን፡፡
8ኛ/ ደመወዝ በሆስፒታሉ ስኬል መሠረት ይሆናል፤

ማሳሰቢያ፡-
የሥራ ልምድ ያላቸው በፈተና ሲያልፉ ከሚሠሩበት መ/ቤት መልቀቂያ የማቅረብ ግዴታ አለባቸው፡፡

ሁሌም ለላቀ የሕክምና አገልግሎት እንተጋለን!
ሶዶ ክርስቲያን አጠቃላይ ሆስፒታል
አድራሻችን፦ ወ/ሶዶ ከጉታራ በስተጀርባ እንገኛለን
ለበለጠ መረጃ: 0465511164 ይደውሉ
ጤና ነክ የሆኑ መረጃዎችን በየጊዜው ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ይከታተሉ
https://t.me/soddochristiangeneralhospital
በጤና ይቆዩ

አራት ህፃናት በአንድ መሃፀንየምሰራዉ የማህፀን እና የህፃናት ህክምና ክፍል ተናበዉ እና ተነጋገረዉ በሚሰሩበት ሆስፒታል ነዉ ። በእለቱ ተረኛ ሁኘ በጣም የታመመ ጨቅላ ህፃን ለማትረፍ ደረቱን...
23/04/2026

አራት ህፃናት በአንድ መሃፀን

የምሰራዉ የማህፀን እና የህፃናት ህክምና ክፍል ተናበዉ እና ተነጋገረዉ በሚሰሩበት ሆስፒታል ነዉ ። በእለቱ ተረኛ ሁኘ በጣም የታመመ ጨቅላ ህፃን ለማትረፍ ደረቱን በመጫን እና በማስክ ኦክሲጅን እየሰጠሁ በአለበት ሰዓት ከማህፀን እና ፅንስ ስፔሻሊስት ሀኪሙ ስልክ ተደወለልኝ ፤ በመድማት ላይ ያለች እናት 29ሳምንት የሆናቸዉ መንታ እንዳረገዘች ከሚገልፅ የሪፈራል ወረቀት ጋር እንደመጣች እና የሶኖግራፊ ምርመራ ለማድረግ ጊዜ እንደለለዉ ቀጥታ ወደ ኦፕሬሽን ክፍል እየተወሰደች እንደሆነ ህፃኖች ያለድሚያቸዉ የሚወለዱ ስለሆኑ እገዛ እንዳደርግ ኦፕሬሽን ክፍል በፍጥነት እንድሄድ ጠራኝ ።

መንታ በሚወለድበት ጊዜ አንድ ሰዉ ህፃኖችን ለማገዝ በቂ ስላልሆነ እኔ ብቻ ሌላ የህፃናት ሃኪም እንዲያግዘኝ ጠርቸ በሞት መካከል ያለዉን ጨቅላ ለሌላ የህፃናት ሃኪም እገዛ እንድታደርግለት አስረክቤ ወደ ኦፕሬሽን ክፍል በቻልኩት ፍጥነት ለመድረስ ሮጥኩ። ኦፕረሽን ክፍል ከደረስኩ በኋላ ሁለት ህፃናት ለማገዝ የሚችል neonatal corner አዘጋጀን። ሁለት የኦክሲጅን ሶርስ ፣ሁለት ህፃናት የሚያስተኛ የማሞቂያ ቦታ። የማህፀን ሀኪሙ ኦፕሬሽን ጀመረ። እኔ የመጀመሪያ የሚወለደዉን መንታ (twin A) ጓደኛየ ሁለተኛዉን መንታ (Twin B) ለመቀበል ተዘጋጀን።

የመጀመሪያዉ ልጅ ተወለደ አያለቅስም አይተነፍስም ተቀበልኩ እርዳታ ማድረግ ጀመርኩ። ሁለተኛዉ ልጅ ተወለደ ጓደኛየ ተቀብላ እገዛ ማድረግ ጀመረች። ነገር ግን የማህፀን ሀኪሙ ሌላ ሶስተኛ ልጅ አለ ተቀበሉኝ አለ። ለሶስተኛ ልጅ ዝግጁ አልነበርነም። መጀመሪያ የተወለደዉን ልጅ ለጠቅላላ ሃኪሙ በመስጠት ሶስተኛዉን ልጅ ሌላ የኦክሲጅን ሶርስ በመፈለግ ማገዝ ጀመርኩ። ሌላ የህፃናት ሀኪም በፍጥነት ለእገዛ እንዲደርስ ተደወለ ።ሶስት የህፃናት ሀኪም ሶስት ህፃናት። ከሰከንዶች በኋላ ሌላ አራተኛ ልጅ እንዳለ የማህፀን እና የፅንስ ሃኪሙ ነገረን። ምንም የማይተነፍስ የልብ ምቱ የቆመ አራተኛ ልጅ ። ኦክስጅን ሶርስ የለም:ቦታም የለም እገዛ ለመስጠት። በዚህ ሰዓት ያደረግነዉ አንደኛዉን እና ሁለተኛዉን ልጅ ጥብቅ የጨቅላ ህፃናት ክትትል ክፍል(NICU) መላክ ነበር። ሶስተኛዉ እና አራተኛዉን ኦፕረሽን ክፍል እየረዳን ቆይተን አራተኛዉን የጭቅላ ጥብቅ ጥንቃቄ ክፍል በመላክ ሶስተኛዉን ለአንድ ሰዓት ያህል ርዳታ ከተደረገለት በኋላ በአርቲፊሻል መተንፈሻ መሳሪያ (Mechanical ventilator ) በማገዝ ወደ ጥብቅ ጥንቃቄ ክፍል መላክ ቻልን። ሁለት ሴት ሁለት ወንድ በሰላም የተገላገለች ሲሆን እኛ የህፃናት ሀኪሞች የተወለዱ የጨቅላ ህፃናት እንዲተነፍሱ የልብ ምታቸዉ እንዲመለስ ስናግዝ የማህፀን እና የፅንስ ስፔሻሊስት ሀኪሙ እና ረዳቶቹ ደም የሚፈሳትን እናት ለማዳን የቻሉትን ጥረት አድርገዉ ለማትረፍ ችለዋል።

የተወለዱት ጨቅላ ህፃናት

1ኛዉ 29 ሳምንት , ክብደት 1055ግራም ፆታ ሴት
2ኛዉ 29ሳምንት , ክብደት 1125ግራም ፆታ ሴት
3ኛዉ 29 ሳምንት , ክብደት 1090 ግራም ፆታ ወንድ
4ኛዉ 29 ሳምንት, ክብደት 1075 ግራም ፆታ ወንድ

አባት ልጆች በሂወት ይወለዳሉ የሚል ሃሳብ አልነበረዉም። ብቻዉን ሆኖ ሚስቱ የማትተርፍ ስለመሰለዉ እያለቀሰ ነበር። ለሚስቱ መድሃኒት እንዲያመጣ ተደዉሎለት ከሰመመን ወደ ሚነቁበት ክፍሌ ሲሄድ አንዲት እናት አራት ልጆች ተገላገለች እያሉ እያወሩ ይሰማል። እሱ የሚስቱን በሂወት መትረፍ እንጅ ስለልጆች በሂወት መወለድ አልሰማም/አያሳስበዉም ነበር።

የመተንፈሻ ጡንቻቸዉ ፣ ሳንባቸዉ እንዲሁም ትንፈሳን የሚቆጣጠረዉ የአእምሮ ክፍል ስላለበሰለ ወደ ጥብቅ ጥንቃቄ ክፍል ከገቡ በኋላ የሳንባ ማጠንከሪያ (surfactant ) ተሰጣቸዉ። ትንፈሳ እንዳይረሱ ካፊን እየተሰጣቸዉ በማሽን እየታገዙ በተለያየ ጊዜ ለኢንፈክሽን ታክመዉ ፣ ለደም ማነስ ብዙ ጊዜ ደም ወስደዉ 3ኛዉ መንታ በተወለደ በ6ቀን ሂወቱ ሲያልፍ 3ቱ መንታ ህፃናት ከ98 ቀናት የሆስፒታል ቆይታ በኋላ ወደ ቤት በሰላም ተሸኝተዋል። ወደ ቤት ሲላኩ የነበራቸዉ
ክብደት

1ኛዋ :2040ግራም
2ኛዋ :2065ግራም
4ኛዉ :1925ግራም

ምስጋና
-ወጫቸዉን ለሸፈነልን BF (Benevolence fund)
-ሰርፋክታንት (Surfactat) ላቀረበልን ድርጅት
-በሂወት ተርፈዉ አድገዉ ወደ ቤት እንዲሄዱ ላደረጋቸሁ የጨቅላ ክፍል ሰራተኞች
-ቀን ከሌት ሳተኙ ስተከታተሉ ለነበራቹ የህፃናት ሃኪሞች
ዶ/ር ሚሸል
ዶ/ር ያዴል
ዶ/ር ሀይሌ
-ተጨማሪ የሰዉ ሃይል ሲያስፈልግ ስታመቻቹ የነበራቹ የአስተዳደር ሰራተኞች።

🖋 ዶ/ር ሀበንዮም ተበጀ | የሕጻናት ስፔሻሊስት

ሁሌም ለላቀ የሕክምና አገልግሎት እንተጋለን!
ሶዶ ክርስቲያን አጠቃላይ ሆስፒታል
አድራሻችን፦ ወ/ሶዶ ከጉታራ በስተጀርባ እንገኛለን
ለበለጠ መረጃ: 0465511164 ይደውሉ
ጤና ነክ የሆኑ መረጃዎችን በየጊዜው ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ይከታተሉ
https://t.me/soddochristiangeneralhospital
በጤና ይቆዩ

ማስታወቂያቀን፡ 12-06-2018 ዓ.ምየሶዶ ክርስቲያን ሆስፒታል ኃላ.የተ.የግ.ማህበር የጥበቃ ሠራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ባለው ፍላጎት በቁጥር SCH-16/265/18 በቀን 10/07/201...
20/04/2026

ማስታወቂያ
ቀን፡ 12-06-2018 ዓ.ም
የሶዶ ክርስቲያን ሆስፒታል ኃላ.የተ.የግ.ማህበር የጥበቃ ሠራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ባለው ፍላጎት በቁጥር SCH-16/265/18 በቀን 10/07/2018 ዓ.ም እና በቁጥር SCH-187-10-18 በቀን 2-7-2018 ዓ.ም ባወጣው ማስታወቂያ መሠረት ቀርባችሁ የተመዘገባችሁና ፈተና የተፈተናችሁ፡-

ጠቅላላ ድምር 68 እና ከዚያ በላይ ያመጣችሁ ተወዳዳሪዎች ያለፋችሁ ስለሆነ በቀን 19/08/2018 ዓ.ም ወደ ሆስፒታሉ ግቢ አስተዳደር ቢሮ ቀርባችሁ የቅጥር ፎርማሊቲ እንድታሟሉና ስትመጡ ቀደም ሲል ያቀረባችሁትን የትምህርት ማስረጃ original copy እና softcopy እንዲሁም ለጤና ምርመራ የሚሆን ገንዘብ ይዛችሁ እንድትቀርቡ ማስፈለጉን ጭምር እንገልፃለን፡፡

ሁሌም ለላቀ የሕክምና አገልግሎት እንተጋለን!
ሶዶ ክርስቲያን አጠቃላይ ሆስፒታል
አድራሻችን፦ ወ/ሶዶ ከጉታራ በስተጀርባ እንገኛለን
ለበለጠ መረጃ: 0465511164 ይደውሉ
ጤና ነክ የሆኑ መረጃዎችን በየጊዜው ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ይከታተሉ
https://t.me/soddochristiangeneralhospital
በጤና ይቆዩ

ከሁለት ሺህ አንድ መቶ ዘጠና አምስት (2,195) በላይ ሕጻናትን ከትበናል!በሆስፒታላችን የሕጻናት ክትባት መርሃ-ግብር የተጀመረበትን ጊዜ በማስመልከት ዛሬ 08/08/2018ዓ.ም አንደኛ ዓመ...
16/04/2026

ከሁለት ሺህ አንድ መቶ ዘጠና አምስት (2,195) በላይ ሕጻናትን ከትበናል!

በሆስፒታላችን የሕጻናት ክትባት መርሃ-ግብር የተጀመረበትን ጊዜ በማስመልከት ዛሬ 08/08/2018ዓ.ም አንደኛ ዓመት ምስረታ አክብረናል።

ይህንን መርሃ-ግብር በሆስፒታላችን ለማስጀመር ላለፉት አስር ዓመታት ያክል ብዙ ጥረቶች ሲደረጉ የቆየ ሲሆን ካለፈው አንድ ዓመት ጀምሮ በተሳካ ሁኔታ ለሕጻናት ክትባቶችን ስንሰጥ ቆይተናል። ይህን ማድረጋችን የምንሰጠውን የላቀ የሕክምና አገልግሎት አንድ እርምጃ ወደፊት የሚያስኬድ ሲሆን የክትባት መርሃ-ግብሩ እዚሁ እንዲጀመር የተለያዩ ቁሳቁሶችን በማበርከት የበኩላቸውን ኃላፊነት የተወጡትን የመንግሥት ባላድርሻ አካላት በተለይም የዞኑ ጤና መምሪያ እና የሶዶ ከተማ ክትባት ክፍል አስተባባሪዎች፣ የሆስፒታሉ ማኔጅመንት እንዲሁም ዶ/ር ሚሼል ዬትስ እና አቶ በቃሉ ቶማስ ያላሰለሰ ጥረት በማድረጋቸው ይህ ሥራ በሆስፒታላችን እውን መሆን ችሏል።

ይህ በመሆኑ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ከሁለት ሺህ አንድ መቶ ዘጠና አምስት (2,195) በላይ ሕጻናትን ከዜሮ እስከ ዘጠኝ ወር ድረስ የሚሰጡ ክትባቶችን በተሳካ ሁኔታ መከተብ ችለናል።

ሁሌም ለላቀ የሕክምና አገልግሎት እንተጋለን!
ሶዶ ክርስቲያን አጠቃላይ ሆስፒታል
አድራሻችን፦ ወ/ሶዶ ከጉታራ በስተጀርባ እንገኛለን
ለበለጠ መረጃ: 0465511164 ይደውሉ
ጤና ነክ የሆኑ መረጃዎችን በየጊዜው ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ይከታተሉ
https://t.me/soddochristiangeneralhospital
በጤና ይቆዩ

ተሻሽሎ የወጣ ማስታወቂያቀን፡ 05/08/2018 ዓ.ምየሶዶ ክርስቲያን ሆስፒታል ኃላ.የተ.የግ.ማህበር የጥበቃ ሠራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ባለው ፍላጎት በቁጥር SCH-16/265/18 በቀን ...
14/04/2026

ተሻሽሎ የወጣ ማስታወቂያ

ቀን፡ 05/08/2018 ዓ.ም
የሶዶ ክርስቲያን ሆስፒታል ኃላ.የተ.የግ.ማህበር የጥበቃ ሠራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ባለው ፍላጎት በቁጥር SCH-16/265/18 በቀን 10/07/2018 ዓ.ም እና በቁጥር SCH-187-10-18 በቀን 2/7/2018 ዓ.ም ባወጣው ማስታወቂያ መሠረት ቀርባችሁ የተመዘገባችሁና የጽሑፍ ፈተና ተፈተናችሁ 27.5 ከዚያ በላይያመጣችሁ ለቃለ-መጠይቅ ፈተና እንድትቀርቡ በሚል ማስታወቂያ ያወጣን ቢሆንም ማሻሻያ እንዲደረግ ስለተወሰነ ከዚህ በታች በተዘረዘረው መሠረት ማሻሻያ ተደርጎ ማለትም፡-

የጽሑፍ ፈተና ውጤት 24.5 እና ከዚያ በላይ ያመጣችሁ ተወዳዳሪዎች በቀን 08/08/2018 ዓ.ም ከጧቱ 3፡00 ሰዓት ላይ ለቃለ-መጠይቅ ፈተና ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያና ቀደም ሲል ያቀረባችሁትን ዶክሜንት original copy በመያዝ ወደ ሆስፒታሉ አስተዳደር ሕንፃ እንድትቀርቡ ማስፈለጉን እያስታወቅን መታወቂያ ሳይዝ የሚቀርብ ተወዳዳሪ ለፈተና መቅረብ የማይችል መሆኑን ጭምር በጥብቅ እናስታውቃለን፡፡

ሁሌም ለላቀ የሕክምና አገልግሎት እንተጋለን!
ሶዶ ክርስቲያን አጠቃላይ ሆስፒታል
አድራሻችን፦ ወ/ሶዶ ከጉታራ በስተጀርባ እንገኛለን
ለበለጠ መረጃ: 0465511164 ይደውሉ
ጤና ነክ የሆኑ መረጃዎችን በየጊዜው ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ይከታተሉ
https://t.me/soddochristiangeneralhospital
በጤና ይቆዩ!

ማስታወቂያቀን፡ 05/8/2018 ዓ.ምየሶዶ ክርስቲያን ሆስፒታል ኃላ.የተ.የግ.ማህበር የጥበቃ ሠራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠርባለው ፍላጎት በቁጥር SCH-16/265/18 በቀን 10/07/2018 ...
13/04/2026

ማስታወቂያ
ቀን፡ 05/8/2018 ዓ.ም
የሶዶ ክርስቲያን ሆስፒታል ኃላ.የተ.የግ.ማህበር የጥበቃ ሠራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠርባለው ፍላጎት በቁጥር SCH-16/265/18 በቀን 10/07/2018 ዓ.ም እና በቁጥር SCH-187-10-18 በቀን 2-7-2018 ዓ.ም ባወጣው ማስታወቂያ መሠረት ቀርባችሁ የተመዘገባችሁና የጽሑፍ ፈተና የተፈተናችሁ፡-

የጽሑፍ ፈተና ውጤት 27.5 እና ከዚያ በላይ ያመጣችሁ ተወዳዳሪዎች በቀን 08/08/2018 ዓ.ም ከጧቱ 3፡00 ሰዓት ላይ ለቃለ-መጠይቅ ፈተና ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያና ቀደም ሲል ያቀረባችሁትን ዶክሜንት original copy በመያዝ ወደ ሆስፒታሉ አስተዳደር ሕንፃ እንድትቀርቡ ማስፈለጉን እያስታወቅን መታወቂያ ሳይዝ የሚቀርብ ተወዳዳሪ ለፈተና መቅረብ የማይችል መሆኑን ጭምር በጥብቅ እናስታውቃለን፡፡

ሁሌም ለላቀ የሕክምና አገልግሎት እንተጋለን!
ሶዶ ክርስቲያን አጠቃላይ ሆስፒታል
አድራሻችን፦ ወ/ሶዶ ከጉታራ በስተጀርባ እንገኛለን
ለበለጠ መረጃ: 0465511164 ይደውሉ
ጤና ነክ የሆኑ መረጃዎችን በየጊዜው ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ይከታተሉ
https://t.me/soddochristiangeneralhospital
በጤና ይቆዩ

በዛሬው ዕለት 30/07/2018 ዓ.ም በሶዶ ክርስቲያን አጠቃላይ ሆስፒታል የRHD (Rheumatic Heart Disease) Prevention and Control Program የRHD በበይነ-መ...
08/04/2026

በዛሬው ዕለት 30/07/2018 ዓ.ም በሶዶ ክርስቲያን አጠቃላይ ሆስፒታል የRHD (Rheumatic Heart Disease) Prevention and Control Program የRHD በበይነ-መረብ የታገዘ የታካሚዎች (ልየታ የተደረገላቸው ዕድሜያቸው ከ5-20 የሚደርሱ በትምህርት ቤት የሚገኙ ልጆች እና ወጣቶች) የምዝገባ እና የሕክምና ሁኔታዎች መከታተያ እንዲሁም የተሟላ የሕክምና የመረጃ አያያዝ ዘዴ ACT (Active Community Case Management Tool) የተሰኘ ሲስተም / Platform የማስመረቅ እና ለRHD ቡድን አባላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጥቷል።

ይህ Platform ወደ ትግበራ መግባቱ የታካሚዎችን መረጃ በዘመናዊ እና ዲጂታል መንገድ ለመሰነድ የሚረዳ ከመሆኑም በተጨማሪ የሐኪሞችን እና ታካሚዎችን ጊዜ ከአላስፈላጊ ብክነት የሚታደግ መሆኑም ጭምር በስልጠናው ላይ ተመላክቷል።

ከስልጠናው ተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎች በአቶ ፈቃዱ ኤልያስ እና በዶ/ር ሚሼል ዬትስ ምላሽ እና ማብራሪያ ተሰጥቷል።

ሁሌም ለላቀ የሕክምና አገልግሎት እንተጋለን!
ሶዶ ክርስቲያን አጠቃላይ ሆስፒታል
አድራሻችን፦ ወ/ሶዶ ከጉታራ በስተጀርባ እንገኛለን
ለበለጠ መረጃ: 0465511164 ይደውሉ
ጤና ነክ የሆኑ መረጃዎችን በየጊዜው ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ይከታተሉ
https://t.me/soddochristiangeneralhospital
በጤና ይቆዩ!

Address

Christian Hospital Street
Sodo

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Soddo Christian Hospital posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Soddo Christian Hospital:

Share