የምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት ሕዝብ ግንኙነት Qunnamtii Ummataa Kutaa Lallaba Arsii Lixaa

  • Home
  • Ethiopia
  • Shashemene
  • የምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት ሕዝብ ግንኙነት Qunnamtii Ummataa Kutaa Lallaba Arsii Lixaa

የምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት ሕዝብ ግንኙነት   Qunnamtii Ummataa Kutaa Lallaba Arsii Lixaa በኢ.ኦ.ተ.ቤ.ክ የምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት የሕዝብ ግንኙነት

ሸምሸርሸጢን ከሚባለው ከግራር እንጨት የተቀረጸው ታቦት አይነቅዝም አይበላሽም ።እንዲሁም መንፈስ ቅዱስ  ያደረባት የጌታ ዙፋን የሆነች የወላዲተ አምላክ  የታቦተ መቅደስ የድንግል ማርያም ሥጋ...
22/08/2024

ሸምሸርሸጢን ከሚባለው ከግራር እንጨት የተቀረጸው ታቦት አይነቅዝም አይበላሽም ።

እንዲሁም መንፈስ ቅዱስ ያደረባት የጌታ ዙፋን የሆነች የወላዲተ አምላክ የታቦተ መቅደስ የድንግል ማርያም ሥጋዋ በምድር አይኖርም ተነሥታለች ዐርጋለች!

እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለከበረ ትንሣኤና ዕርገት በዓል አደረሳችሁ

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ 12ኛ ዓመት የእረፍታቸው መታሰቢያ በጸሎተ ፍትሐት ታስቦ ዋለ።*****************************************ነሐሴ 10 ቀን 2016 ዓ.ም የብ...
16/08/2024

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ 12ኛ ዓመት
የእረፍታቸው መታሰቢያ በጸሎተ ፍትሐት ታስቦ ዋለ።
*****************************************
ነሐሴ 10 ቀን 2016 ዓ.ም

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት ፕሬዝዳንትና የዓለም ሃይማኖቶች ለሰላም የክብር ፕሬዝዳንት 12ኛ ዓመት የእረፍታቸው መታሰቢያ ክቡር አስከሬናቸው ባረፈበት በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በጸሎተ ፍትሐት ታስቦ ዋለ።

በመርሐ ግብሩ ላይ ብፁእ አቡነ አብርሃም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የባህር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁአ አቡነ ሳዊሮስ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ፣ የሸገር ሲቲ አህጉረ ስብከትና የምስካየኅዘለናን መድኃኔዓለም ገዳም የበላይ ኃላፊ ሊቀ ጳጳስ ፣ የጠቅላይ ቤተክህነት የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች እንዲሁም የገዳማትና የአድባራት አስተዳዳሪዎች በርካታ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ካህናትና ምእመናን በተገኙበት ጸሎተ ፍትሐቱ በዛሬው ዕለት ማለትም ነሐሴ 10 ቀን 2016 ዓ.ም ተከናውኖ መርሐ ግብሩ ተጠናቋል።

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን ለሃያ ዓመታት በፓትርያርክነት ያገለገሉ፣ በርካታ መንፈሳዊና ልማታዊ ውጤታማ ሥራዎችን የሰሩ፣ ቤተክርስቲያንን በዓለም መድረክ ከፍ ብላ እንድትታይ ያደረጉ አባት እንደነበሩ ይታወቃል።

በአፍሪካ ኅብረት ደብረ ምሕረት  ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ሰሞነኛ ጉዳይ ዙሪያ ከመንግሥት አካላት ጋር ውይይት ተካሔደ።ነሐሴ ፮ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም በአፍሪካ ኅብረት ደብረ ምሕረት  ቅዱስ ሚካኤ...
13/08/2024

በአፍሪካ ኅብረት ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ሰሞነኛ ጉዳይ ዙሪያ ከመንግሥት አካላት ጋር ውይይት ተካሔደ።

ነሐሴ ፮ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም

በአፍሪካ ኅብረት ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ሰሞነኛ ጉዳይ ከመንግሥት አካላት ጋር ውይይት ተካሔደ።

በማኅበራዊ ትስስር ገጾች በስፋት ይነሳ የነበረው የአፍሪካ ኅብረት ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል በከተማ አስተዳዳሩ በሚያከናውነው የኮሪደር ልማት ምክንያት መነሻነት "አጥሩ ይፈርሳል" የሚል መረጀ ሲሰራጭ መቆየቱ የሚታወቅ ነው።

ይህን ተከትሎ ዛሬ ነሐሴ 6/2016 ዓ/ም የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ማእምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳር ተወካይ፣ የቂርቆስ ክፍል ከተማ አስተዳደር ሥራ አስፈጻሚ፣ከደብሩ አስተዳዳር፣ ካህናት፣ ሰንበት ትምህርት ቤት፣ የአካባቢው ወጣጣቶችና ከማኅበራት ኅብረት የተውጣጡ ተወካዮች በተገኙበት የጋራ ውይይት በመከናወኑ ተገልጿል።

በዚህም የተሰራጨው መረጃ የተሳሳተና ሐሰተኛ መረጃ መሆኑን የከተማ አስተዳዳሩ ከፍተኛ የሥራ ሐላፊዎች ገልጸዋል።

የከተማ አስተዳዳሩ ተወካዮች እንዳሉት የደብሩ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን የሥርዓተ አምልኮ መፈጸሚ ከመሆን አልፎ የአሠራር ጥበቡ ትውልድ ተሻጋሪና የከተማ አስተዳዳሩ ለያዘው የከተማው ውበት አቅጣጫም ልዩ ድምቀት መሆኑን ጠቁመዋል።

አክለውም የሕንጻ ቤተ ክርስቲያኑ ጥበብና መልክ በማስጠበቅ ረገድ የደብሩ አስተዳዳር በትኩረት እንዲመለከተው ያሳሰቡ ሲሆን በተለይም በሕንጻ ቤተ ክርስቲያኑ ላይ የሚታየውን አልጌ በማጽዳት ጥበቡን መጠብቅ ይገባል ብለዋል።

የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ማእምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ በበኩላቸው እንደዚህ ዓይነት የተሳሳቱ መረጃዎች የቤተ ክርስቲያን ሰላምን የሚያናጉ ጉዳዮች በመሆናቸው እንደዚህ መሰል ሁኔታዎች ሲያጋጥሙ ካህናቱና ምዕመናኑ ከሀገረ ስብከቱ ጋር ተቀራርቦ መሥራትና መናበብ እንደሚገባቸው ያሳሰቡ ሲሆን ከተሳሳቱና ሐሰተኛ ከሆኑ መረጃዎች ራሳቸውን ሊጠብቁ ያስፈልጋቸዋል ብለዋል።

አያይዘውም ከተማ አስተዳዳሩ በኮሪደር ልማቱ ምክንያት ለፈረሱ የቤተ ክርስቲያን ይዞታዎች ምትክ ቦታዎች በመስጠትና ከአባቶች ጋር ያለውን መልካም ግንኙነቶች ሀገረ ስብከቱ እንደሚያደንቅ የገለጹ ሲሆን በዚህም ክብርት ከንቲባ አዳነች አቤቤንና ካብኔቸውን አመስገነዋል።

በመጨረሻም ሀገረ ስብከቱ በቤተ ክርስቲያን የተለያዩ ጉዳዮች ላይ ከከተማ አስተዳደሩ ጋር በቅርበት በመመካከር እየሠራ እንደሚቀጥልም ሊቀ ማእምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ ገልጸዋል።
++++++++++++++++++++++++
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

ብፁዕ አቡነ ዜናማርቆስ ሊቀ ጳጳስ በምዕራብ አርሲ ሻሸመኔ ማረሚያ ቤት ገነተ ብርሃን ቅ/እግዚአብሔር አብ ቤተክርስቲያን የፍልሰታ ጾምን አስጀመሩ።~~~~~~~~~~~ነሐሴ ፩ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም...
07/08/2024

ብፁዕ አቡነ ዜናማርቆስ ሊቀ ጳጳስ በምዕራብ አርሲ ሻሸመኔ ማረሚያ ቤት ገነተ ብርሃን ቅ/እግዚአብሔር አብ ቤተክርስቲያን የፍልሰታ ጾምን አስጀመሩ።
~~~~~~~~~~~
ነሐሴ ፩ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም ሻሸመኔ/ኢትዮጵያ

ብፁዕ አቡነ ዜናማርቆስ የጉጂ ምዕራብ ጉጂ ቦረና ሊበንና የምዕራብ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የቅዱስ ሲኖዶስ አባል፤ በምዕራብ አርሲ ዞን በሻሸመኔ ከተማ ማረሚያ ቤት ገነተ ብርሃን ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ቤተክርስቲያን ሥርዓተ ቅዳሴውን አስጀምረዋል።

ብፁዕነታቸው በደብሩ ሰበካ ጉባኤ እንዲቋቋም በማድረግ አስተዳዳሪና ልዩ ልዩ አገልጋዮች እንዲሟሉ መመሪያ በመስጠት ለሕግ ታራሚዎችና ለአከባቢው ምዕመናን ቤተ-ክርስቲያኑ መንፈሳዊ አገልግሎት እንዲሰጥ ከፍተኛ ሥራዎች እንዲሰራ ያደረጉ ሲሆን ለአገልግሎቱ መሳካት በመንበረ ጵጵስናው ያሉ አድባራትና ገዳማት አቢያተ ክርስቲያናት የአድባራትና የገዳማት አስተዳዳሪዎች፣ የሰበካ ጉባኤ አባላት እንዲሁም ምእመናን በተለይም የምዕራብ አርሲ ዞን የመንግሥት አካላት የማረሚያ ቤቱ ኃላፊና ጉዳዩ የሚመለከታቸው ሁሉ ከፍተኛ ትብብርና ድጋፍ አድርገዋል ፤

ብፁዕነታቸው ሥርዓተ ቅዳሴውን በመምራት የሱባኤው የመጀመሪያ ቀን ከመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቸው ጋር በጋራ በመሆን የቆዩ ሲሆን ለአገልግሎቱ መሳካት ቀና ትብብር ላደረጉ ሁሉ በቅድስት ቤተክርስቲያን ስም አመስግነው ፣ የተጀመረውን ሱባኤ በሰላምና በፍቅር እንዲከናወን እስከመጨረሻው በመጽናት ካህናትና ዲያቆናት መዘምራንና ምእመናን በትጋት በአንድነትና በእምነት እንዲቆሙ አባታዊ መልእክት አስተላልፈው በብፁዕነታቸው ጸሎተ ቡራኬ ተፈጽሟል።

በዕለቱ የሀገረስብከቱ ዋና ሥራአስኪያጅ ሊቀ ብርሃናት ተፈሪ ታደሠ የሀ/ስ ልዑካን የደብሩ አስተዳዳሪ በማረሚያ ቤቱና በአካባቢው የሚኖሩ ምእመናን ተገኝተዋል።
=================

ሊቀ ብርሃናት ተፈሪ ታደሰ የምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት መንበረ ጵጵስና ግባታን ጎበኙ የምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት  ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ብርሃናት ተፈሪ ታደሰ ለአንድ ዓመት ከ5 ወራት ...
06/08/2024

ሊቀ ብርሃናት ተፈሪ ታደሰ የምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት መንበረ ጵጵስና ግባታን ጎበኙ

የምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ብርሃናት ተፈሪ ታደሰ ለአንድ ዓመት ከ5 ወራት ያህል ግንባታው ተቋርጦ የቆመውን መንበረ ጵጵስናን ጎበኙ።

ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ ሊቀ ጳጳስ በወላይታ ዞን በደረሰው የመሬት ናዳ በሞቱ ወገኖች ኀዘናቸውን ገለጹ።ሐምሌ 30 ቀን 2016. ዓ.ም ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ የቅዱስ ሲኖዶስ አባልና የወላይታ ሀገረ...
06/08/2024

ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ ሊቀ ጳጳስ በወላይታ ዞን በደረሰው የመሬት ናዳ በሞቱ ወገኖች ኀዘናቸውን ገለጹ።

ሐምሌ 30 ቀን 2016. ዓ.ም

ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ የቅዱስ ሲኖዶስ አባልና የወላይታ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በወላይታ ዞን በካዎ ኮይሻ ወረዳና በኪንዶ ኮይሻ ወረዳ በደረሰው ድንገተኛ የመሬት መንሸራተት አደጋ ውድ ሕይወታቸውን ላጡ ወገኖች ዕረፍተ ነፍስን ለቤተሰቦቻቸው መጽናናትን ተመኝተዋል ።

ብፁዕነታቸው አያይዘውም ፈጣሪ መዓቱን በምሕረት ቁጣውን በትዕግስት እንዲመልስ ከነሐሴ 1እስከ 14 ቀን 2016 ዓ/ም ድረስ በሀገረ ስብከቱ በሁሉም ገዳማት አድባራትና የገጠር አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ጸሎተ ምኅላ እንዲደረግ መመሪያ አስተላልፈው።

በደረሰው አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ቤተሰቦችና ወገኖች ሁሉም የኅብረተሰብ ክፍል ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።

በወረዳው ጤፓ ቀበሌ ትናንትና ሐምሌ 29 ቀን 2016 ዓ.ም ማለዳ ለሰዓታት የዘነበውን ከባድ ዝናብ ተከትሎ የተከሰተው ናዳ የ11 ነዋሪዎች ህይወት መቅጠፉ ይታወቃል።

የቅዱስ ፓትርያርክ የጾመ ፍልሰታ መልእክት በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!በሀገር ውስጥና በተለያዩ ክፍለ ዓለማት የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያ...
06/08/2024

የቅዱስ ፓትርያርክ የጾመ ፍልሰታ መልእክት

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

በሀገር ውስጥና በተለያዩ ክፍለ ዓለማት የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት በሙሉ!

በማሕፀነ ማርያም በፈጸመው እውነተኛ ተዋሕዶ የሰው ልጅን ከኃሣር ወደ ክብር የመለሰ እግዚአብሔር አምላካችን፣ እንኳን ለሁለት ሺሕ አሥራ ስድስት ዓመተ ምሕረት ጾመ ቅድስት ማርያም በደኅና አደረሰን አደረሳችሁ!

‹‹ተፈሥሒ ኦ ምልእተ ጸጋ፣ ተፈሥሒ እስመ ረከብኪ ሞገሰ በኀበ እግዚአብሔር፡- ምልእተ ጸጋ ሆይ ደስ ይበልሽ፤ በእግዚአብሔ ዘንድ ሞገስን አግኝተሻልና ደስ ይበልሽ››
(ሉቃ. 1÷28-30")
የክብር አምላክ እግዚአብሔር የሰው ልጅን ከወደቀበት ዐዘቅተ ኵነኔ የሚያድንበት ዕድል እንዳዘጋጀ በብሉይ ኪዳን በስፋት ተገልጿል፤ የማዳን ሥራውም ከሰው ወገን ከሆነች ቅድስት ድንግል በሚወለደው መሲሕ እንደሚፈጸም አስረድቶአል፤ የማዳን ቀኑ በደረሰ ጊዜም መልእክቱን በፊቱ በሚቆመው በቅዱስ ገብርኤል በኩል ልኮአል፤ ቅዱስ ገብርኤልም የተነገረውን መልእክት ለድንግል ማርያም አድርሶአል፡፡

ቅዱስ ገብርኤል ለድንግል ማርያም እንዲነግር ከታዘዘባቸው መካከል ‹‹ጸጋን የተመላሽ ደስተኛይቱ ሆይ÷በእግዚአብሔር ዘንድ ሞገስን አግኝተሻልና ደስ ይበልሽ›› የሚል አስደናቂ መልእክት ይገኝበታል፡፡

የተወደዳችሁ ሕዝበ ክርስቲያን!

ከእግዚአብሔር መንጭቶ በቅዱስ ገብርኤል በኩል ለድንግል ማርያም የተነገረ ይህ መልእክት፣ የቅድስት ድንግል ማርያምን ክብር ከመግለጽ ባሻገር ለሰው ልጆች ሁሉ ያለው ፋይዳ በእጅጉ የላቀ ነው፤
‹‹ጸጋ›› የሚለው ቃል እንደ ቅዱስ መጽሐፍ አስተምህሮ ያልተወሰነ፣ ገደብና ቅድመ ሁኔታ የሌለው ስጦታን ሲያመለክት ‹‹ሞገስ›› የሚለው ቃል ደግሞ ተወዳጅነትን ተደማጭነትን ተሰሚነትን የሚያመለክት የክብርና የባለሟልነት መግለጫ ቃል ነው፡፡

እነዚህ ቃላት ከእግዚአብሔር ዘንድ በቅዱስ ገብርኤል በኩል ለቅድስት ድንግል ማርያም ተነግረዋል፤ የእግዚአብሔር ቃል የማይለወጥ ነውና ቃላቶቹ ለድንግል ማርያም ቃል ኪዳን ሆነው የተሰጡ ናቸው፤ የተሰጡበትም ምክንያት ሰውን ለማዳን ሥራ እንዲውሉ እንጂ ለሌላ አይደለም፡፡

ምክንያቱም የእግዚአብሔር የማይናወጥ ፈቃድ ሰውን ማዳን ነውና፤ በመሆኑም ቅድስት ድንግል ማርያም ከእግዚአብሔር በተሰጣት በዚህ ገደብ የሌለው ቃል ኪዳኗ ሰውን ልትታደግ በቅታለች፤ይህም በቃና ዘገሊላ ባደረገችው ምልጃ በጭንቀት የተዋጡትን ሰርገኞች እንዴት እንደታደገች በቅዱስ ወንጌል ተጽፎ እናገኘዋለን፤ ቅድስት ድንግል ማርያም ቀድሞውኑም ከፍ ያለ ሞገስ ተሰጥቶአታልና የሰርጉ አሳላፊዎችን ‹‹የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ›› በማለት ስታዝዝ እናያለን፤ ይህ ለሰው ልጆች ሁሉ የተሰጠ አስደናቂ የትድግና ስጦታ ነው፡፡

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን!

የድንግል ማርያም የጸጋ ስጦታ በብሥራተ ገብርኤል ተገልጾ፣ በቃና ዘገሊላ ተተግብሮ በዕለተ ስቅለት ‹‹እነሆ ልጅሽ፣ እነኋት እናትህ›› በሚል መለኮታዊ ማኅተም የታተመ ነው፤ ይህ ቃል እሷ እናታችን መሆኗን፤ እኛም ልጆችዋ መሆናችንን ያረጋገጠ ማኅተመ ቃል ኪዳን ነው፤ የቃል ኪዳኑ ይዘት እሷ በአማላጅነቷ እንደ ልጅ ልትንከባከበን እኛም እንደ እናት ልናከብራትና ልንማፀናት የሚገባን መሆኑን ያሳያል፤ የእናትነትና የልጅነት ማረጋገጫ የሆነ ይህንን የቃል ኪዳን ማኅተም ሊሰርዝም ሆነ ሊፍቅ ሊደመስስም የሚችል ኃይል የለም፡፡

ይህ ጸጋና ሞገስ በምድር ብቻ ሳይሆን በሰማይም የሚቀጥል እንጂ የሚገደብ አይደለም፤ ሞት፣ ቦታና ዘመንም አይወስኑትም፤ ምክንያቱም የእግዚአብሔር ቃል ኪዳን በሞት በቦታና በዘመን አይገደብምና ነው፤ ‹‹ኪዳኑንም ለዘለዓለም ያስባል›› ተብሎ የተገለጸውም ለዚህ ነው፤ (መዝ. )111÷5)
መንፈስ ቅዱስም በእሷ አንደበት ‹‹እነሆ ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ነሽ ይሉኛል›› በማለት የተናገረው ይህንን ለማስረዳት እንደሆነ ማስተዋል ያሻል፡፡

በእግዚአብሔር ተሰጥቶ፣ በቃል ኪዳን ታትሞ፣ በቅዱስ ገብርኤል ተብራርቶ፣ በጌታችን ተረጋግጦና በሐዋርያት በኩል የተላለፈልን፣ ሰውን ማዳን ግቡ የሆነ የድንግል ማርያም ምልጃ ጥንታዊት፣ ሐዋርያዊት፣ በሁሉ ያለች፣ አንዲትና ቅድስት ኦርቶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ለሁለት ሺሕ ዓመታት ያህል አምና እና ተቀብላ ስትጠቀምበት ኖራለች፤ አሁንም በዚሁ ትቀጥላለች፡፡

በኦርቶዶክሱ ዓለም ዛሬ የሚጀመረው የጾመ ማርያም ሱባዔም የዚሁ ጭብጥ ማሳያ ነው፤ ዋናው መልእክቱም ድንግል ማርያም በተሰጣት ጸጋና ሞገስ በጸሎቷ ከእግዚአብሔር ዘንድ ምሕረትንና ይቅርታን የምታሰጠን ስለሆነች እሷን በመማፀን ወደ እግዚአብሔር እንቅረብ የሚል ሆኖ ይመሰጠራል፡፡

የተወደዳችሁ ሕዝበ ክርስቲያን ልጆቻችን!

ጾም ፈቃደ ሥጋን በማድከምና ፈቃደ ነፍስን በማጎልበት ምሕረተ እግዚአብሔር መሻታችንን የምናሳይበት መንፈሳዊ ማመልከቻ ነው፤ ጾም ከጥንት ጀምሮ የነበረ ከእግዚአብሔር ጋር የሚያገናኝ ድልድይ ነው፤ ቀደምት አበው በጾም ምክንያት ከጥፋት ድነዋል፤ የለመኑትንም አግኝተዋል፤ ምስጢርም ተገልጾላቸዋል፤ ዲያብሎስም ድል አድርገውበታል፡፡

እኛም ዛሬ ጾምን ስንጾም በሀገራችንም ሆነ በአካባቢያችን ብሎም በዓለም ዙሪያ ሁሉ ስጋትን እየጫረ ያለው የጥፋት እንቅስቃሴ እግዚአብሔር እንዲያስቆምልን ከልብ በመጸለይ ሊሆን ይገባል፤ ይህንንም ስናደርግ በጸሎት ብቻ ሳይሆን ንስሐ በመግባትና ቅዱስ ቁርባንን በመቀበል እንደዚሁም የሰላም የፍቅርና የዕርቅ ሰው ሆኖ በእግዚአብሔር ፊት በመቆም ሊሆን ይገባል፡፡

ችግሮችንና አለመግባባቶችን በሰላማዊ መንገድ በውይይትና በምክክር ለመፍታት የሚደረገው ጥረትም በእጅጉ ሊደገፍ ይገባል፤ ግጭትና ጦርነት ከሚያጠፋን በቀር ሊያተርፍልን የሚችል አንዳች ጥቅም የለም፡፡

በመሆኑም በየትኛውም የሀገራችን አካባቢ ያላችሁ ልጆቻችን እባካችሁ ለሰላም ለውይይትና ለሰው ልጆች መብት መከበር ቅድሚያ ስጡ፤ ግድያ፣ ዕገታ፣ አብያተ ሃይማኖትን መዳፈር፣ ዘረፋና ቅሚያ፣ የሴት ልጅን መድፈርና ሰውን ማንገላታት አቁሙ፤ እነዚህ ድርጊቶች ሰብአዊነትን ዝቅ የሚያደርጉ፣ እግዚብሔርን የሚያስቆጡ፣ በታሪክም የሚያሳፍሩ ናቸው፤ እነዚህን ሳናርም የምንጾመው ጾም ትርጉም ስለሌለው ንስሐ ገብተን ከእንደዚህ ያለው ድርጊ ርቀን ጾሙን መጾም ይገባል፤ ይህን ስናደርግ ጾማችን በእግዚአብሔር ፊት ዋጋ ይኖረዋል፡፡

በመጨረሻም

የኢትዮጵያ ሕዝብ በሙሉ በተለይም በጾመ ማርያም ሱባዔ በንስሐና በጸሎት የሚያሳልፉ ሕዝበ ክርስቲያን ስለ ሃይማኖት መጠበቅ፣ ስለሀገር ሰላምና አንድነት፣ እንደዚሁም ስለሕዝቦች ደኅንነትና ጤንነት አጥብቀው እንዲጸልዩ በእግዚአብሔር ስም መልእክታችንን እናስተላልፋለን፡፡

መልካም የሱባዔ ወቅት ያድርግልን
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
አሜን
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም
ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ነሐሴ 1 ቀን 2016 ዓ.ም
ዋሽንግተን ዲሲ - ዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ

06/08/2024
ሊቀ ብርሃናት ተፈሪ ታደሰ የምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሆነው ተመደቡሊቀ ብርሃናት ተፈሪ ታደሰ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት...
06/08/2024

ሊቀ ብርሃናት ተፈሪ ታደሰ የምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሆነው ተመደቡ

ሊቀ ብርሃናት ተፈሪ ታደሰ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሆነው ተመደቡ

ዛሬ በምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ብፁዕ አቡነ ዜና ማርቆስ የቦረና የጉጂ የምዕራብ ጉጂ የሊበን ዞኖችና የምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ የጠቅላይ ቤተክህነት የመምሪያ ኃላፊዎችና የሀገረ ስብከቱ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

ወደ ኦሮምኛ የተተረጎመው ተአምረ ማርያም መጽሐፍ ተመረቀ፡፡በሰሜን አሜሪካ የሚኒሶታና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ  ናትናኤል እና ዲያቆን እንዳለው መለሰ አዘጋጅነት በኦሮም...
31/07/2024

ወደ ኦሮምኛ የተተረጎመው ተአምረ ማርያም መጽሐፍ ተመረቀ፡፡

በሰሜን አሜሪካ የሚኒሶታና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል እና ዲያቆን እንዳለው መለሰ አዘጋጅነት በኦሮምኛ ፣ በግእዝና በአማርኛ ቋንቋዎች የተጻፈው ተአምረ ማርያም መጽሐፍ ዛሬ ሐምሌ 24 ቀን 2016 ዓ.ም በማኅበረ ቅዱሳን ሕንጻ ላይ ተመርቋል።

መጽሐፉ በማኅበረ ቅዱሳን የኤዲቶርያል አገልግሎት ተመርምሮ ለኅትመት የበቃ ሲሆን አሳታሚና አከፋፋይ ማኅበረ ቅዱሳን መሆኑ ተገልጿል፡፡

በመርሐ ግብሩ ላይ መልእክት ያስተላለፉት ብፁዕ አቡነ ናትናኤል በሰሜን አሜሪካ የሚኒሶታና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ቤተ ክርስቲያን በቋንቋ ማገልገልና መገልገልን ከሐዋርያት ተቀበላ እያስቀጠለች መሆኗን ገልጸው እኛም የኦሮምኛ ቋንቋ ተናጋሪ ኦርቶዶክሳውያንን መሠረት ያደረገውን መጽሐፍ እንደ አቅማችን ተርጉመን ለኅትመት አብቅተናል ብለዋል፡፡

ብዙ ከማውራት ትንሽ መሥራት የተሻለ ነው ያሉት ብፁዕነታቸው በእግዚአብሔር መልካም ፈቃድ ይህንን አድርገናል፣ በቀጣይ ደግሞ የትርጉም ሥራዎችን ከዚህ በበለጠ ለመሥራት መጽሐፍትን እየመረጥንና እየተመካከርን ነው ብለዋል፡፡

ቋንቋ ተግባብተን የምንለወጥበትና የምንስማማበት እንጅ መንግሥተ ሰማያት የምንገባበት አይደለም ሲሉም አጽዕኖት ሰጥተዋል።

ብፁዕነታቸው ጨምረው እንደገለጹት መጽሐፉ የኦሮምኛ ቋንቋ ተናጋሪ ምእመናንን መሠረት ተደርጎ የተዘጋጀ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

እኛ ይህንን የትርጉም ሥራ ለመሥራት ያነሳሳን ምክንያት የቤተ ክርስትያንን ተደራሽነት በመረዳት ምእመናን በቋንቋቸው እንዲገለገሉ በማሰብ ነው ያሉት ዲያቆን እንዳለው ቋንቋን ምክንያት በማድረግ በአጉል ትርክት የተጠቁ ሁሉ ሊማሩበት የሚገባ ነው ሲሉ አስረድተዋል፡፡

የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ጸሐፊ መምህር ዋሲሁን በላይ በበኩላቸው ማኅበረ ቅዱሳን መንፈሳዊ አገልግሎትን ለማስፋፋት መጽሐፍትን በተለያዩ ቋንቋዎች በመተርጎም ረገድ ዘርፈ ብዙ ሥረዎችን መሥራቱንና ወደፊትም አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡

ፀሐይሽ አትጠልቅም መንፈሳዊ ማኅበረ ለብፁአን አባቶችና መጽሐፉ ለሚያስፈልጋቸው አብያተ ክርስቲያናት እንዲደርስ 100 መጽሐፍትን ወስደዋል።

በምርቃት መርሐ ግብሩ ላይ በሰሜን አሜሪካ የሚኒሶታና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል፣ ሌሎች ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ፣ የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ጸሐፊ መምህር ዋሲሁን በላይና የማኅበራት ተወካዮች ተገኝተዋል፡፡

ዘገባው፦የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ማዕከል ነው።
ሐምሌ ፳፬ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም

‹‹በእሳትና በውኃ መኻከል አሳለፍኸን›› (መዝ.፷፭፥፲፪)ሐምሌ ፲፰፤፳፻፲፮ ዓመተ ምሕረትሥራው ግሩም የሆነ አምላካችን እግዚአብሔር ማዳንም መግደልም የሚችል የባሕርይ አምላክ ነው፡፡ (መዝ.፷...
26/07/2024

‹‹በእሳትና በውኃ መኻከል አሳለፍኸን›› (መዝ.፷፭፥፲፪)

ሐምሌ ፲፰፤፳፻፲፮ ዓመተ ምሕረት

ሥራው ግሩም የሆነ አምላካችን እግዚአብሔር ማዳንም መግደልም የሚችል የባሕርይ አምላክ ነው፡፡ (መዝ.፷፭፥፫) በእርሱ የሚታመኑት ቅዱሳን ሰማዕታት የሚደርስባቸውን መከራና ፈተና ሁሉ በጽናት፣ በልበ ሙሉነት የሚያልፉት ለዚህ ነው፡፡

እሳት ለቅዱሳን ሰማዕታት ጌጣቸው ነው፡፡ በመልክአ ሥላሴ ‹‹የሰማይ ግምጃ ብርሃን ሸማኖች የሆናችሁ ሥላሴ ሆይ ልብሰ ምሕረታችሁ የሰማዕትነት ልብስን ይሁነኝ፤ የእስጢፋኖስ ልብስ ደንጊያ በእኔ ላይ የለምና፤ የሕፃኑ ቂርቆስ ጌጡ የሚሆን እሳትም በእኔ ላይ የለምና›› ብለን የምንጸልየውም ለዚህ ነው፡፡ (መልክአ ሥላሴ፡- ለአያጺክሙ)

ወርቅና ብር በእሳት ተፈትነው እንደሚጠሩ ቅዱሳን ሰማዕታትም በመከራ ውስጥ ተፈትነው እግዚአብሔርን አስደስተው ለእኛም የጽናት ምልክት ሆነው የክብር አክሊልን በመቀዳጀት ከገቡ መውጣት፣ ካገኙ ማጣት እና መከራ ወደ ሌለበት ዘለዓለማዊ ማረፊያቸው ይሄዳሉ፡፡
ቅዱሳን ሰማዕታት በመከራ ነፍስ ከመፈተን በመከራ ሥጋ መፈተንን መርጠው፣ ነፍሳቸውን በእሳተ ገሃነም ከመፈተን በምድራዊው ሰው ሠራሹ እሳት ውስጥ ሥጋቸውን ሳይሰቅቁ በመጨመር በመፈተን ዘለዓማዊ ዕረፍት ማግኘትን መርጠዋል፡፡

ሰው በባሕርዩ እንዲራባ በክፉ ግብር የሚራቡ አጋንንት እያደሩባቸው ዓላውያን ነገሥታት ቅዱሳን ሰማዕታት ላይ በጠላትነት እየተነሡ ያልፈፀሙት ክፉ ሥራ የለም፡፡ በሐምሌ ፲፱ ቀን የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ተራዳኢነትን ያገኙት ልጅ እና እናት ቅዱስ ቂርቆስ እና ቅድስት ኢየሉጣም ስለ ንጽሕት ሃይማኖታቸው ለመመስከር ፈተናቸው የመጣውም ከዓላውያን ነገሥታት አንዱ በሆነው በእለ እስክንድሮስ ነው፡፡

ይህ ከሓዲ መኮንን ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስን ይዞ ‹‹ስምህ ማነው›› ብሎ በጠየቀው ጊዜ ‹‹ነቅዕ ዘእምዐዘቅት ንጸሕ ወእማይ ዘኢይማስን ክርስቲያን ስምየ፤ ከንጹሕ ዐዘቅትና ከማይለወጥ ከማይጠፋ ውኃ የተገኘ ስሜ ክርስቲያን ነው›› በማለት መልሶለታል፡፡

ሹሙ እለ እስክንድሮስ በቅዱስ ቂርቆስና በቅድስት ኢየሉጣ ብዛት ያላቸውን መከራ አድርሶም ስላልረካ ጭፍሮቹን በብረት ጋን ውስጥ ሰም፣ ጨው፣ ባሩድ፣ ሙጫ፣ የዶሮ ማር እና እርሳስ ብረትን በማስጨመር ሊያሠቃያቸው ፈለገ፡፡ ከጋኑ የሚወጣው ድምፅም እንደ ነጎድጓድ የሚሰማና ወላፈኑም እንደ ፀሐይ የሚያንጸባርቅ ነበር፡፡

ይህ የጋኑ ፍላት ግርማው እጅግ ያስፈራ ነበርና ቅድስት ኢየሉጣ ተሸበረች፡፡ ልጇ ቅዱስ ቂርቆስ ግን ይህን ፍርሃት ለማራቅ እግዚአብሔር ከእነርሱ በፊት በነበሩት ቅዱሳን በአናንያ፣ በአዛርያ እና በሚሳኤል፣ በሶስና እና በዳንኤል ሕይወት ሥራ ውስጥ የነበረውን የማዳን ችሎታ (ከሃሊነት) እያነሣ ሊያበረታት ሞከረ፡፡ ‹‹እናቴ ሆይ፥ ከሚያልፈው ዓለም ጭንቅና መከራ ለማምለጥ ስትዪ በማያልፈው ዘለዓለማዊ እሳት መቀጣት አይገባሽምና ጽኚ›› አላት፡፡ እንዲሁም ዓይኖቹን ወደ ሰማይ አቅንቶ ወደ እግዚአብሔር እጅግ ልብን የሚነካ ጸሎት አደረሰ፡፡

‹‹ባርያህ የሆነች እናቴ የሌለችበት ለእኔ ያዘጋጀሃት ርስት ውስጥ ከምገባ ከሕይወት መጽሐፍ ፋቀኝ፤ እርሻውን ልታቃጥል ፍሬውን ልትባርክ፣ ዕንጨቱን ቁረጡና አንድዱት፤ ቅጠሉን ጠብቁት፤ ልትል አይገባም፤ ጠላት ዲያብሎስ የአንተ የሆነውን ቅዱሳኑን ድል ነሳኋቸው ብሎ እንዳይመካና ከመንጋውም አንድ በግ ቀማሁ እንዳይል አቤቱ የኃይል መንፈስ ለእናቴ በመስጠት አበርታት›› በማለት ጸለየ ፡፡ የዚህ ሕፃን ሲሆን በመንግሥተ ሰማያት ለእናቱ አባት የሆነ ቅዱስ ጸሎት ከእግዚአብሔር ደርሶ እናቱን አጽንቶ ጭራሽ የብረት ጋኑን ውኃ በምንጭ ላይ በዝቶ እንደሚወርድ ጠል ሁኖ አሳያት፤ ወዲያውም ሁለቱንም ከብረት ጋን ውስጥ ጨመሯቸው፡፡

እሳቱ ዓርባ ክንድ ወደላይ ተመዝዞ ወጥቷል (ወተለዓለ ነበልባል መጠነ አርብዓ በእመት) ፣ የሁለቱ ቅዱሳን ሰማዕታት አምላክም ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤልን ከሰማይ ልኮ በብርሃን በትር ቢመታው እንዳደረ ውርጭ ሆኗል፡፡ የብረት ጋኑም እሳት ጠፍቶ አንዳች ሳይጎዱ ምስክርነታቸውን ፈፀሙ፡፡ በዚህም አስቀድሞ ቅዱስ ዳዊት በመዝሙሩ የዘመረው ቃል ተፈፀመ፡፡ ይህም፡- ‹‹አኅለፍከነ ማዕከለ እሳት ወማይ፤ በእሳትና በውኃ መካከል አሳለፍኸን፡፡›› በቀደመ ግብሩ እሳት የነበረ በኋላ ግብሩ ውኃ ሆነ፡፡ (መዝ.፷፭፥፲፪)

ቃሉ የማይታበል ልዑል እግዚአብሔር አስቀድሞ በነቢየ ልዑል ቅዱስ ኢሳይያስ የተናገረውን ቃልም በሁለቱ ቅዱሳን ሰማዕታት ተፈፅሞ አገኘነው፡፡ ‹‹ወእመኒ ዐደውከ ማየ አነ: ሀሎኩ ምስሌከ: ወአፍላግኒ ኢያሰጥሙከ ወእመኒ ዐደውከ እሳተ ነበልባል ኢያውዕየከ፤ በውኃ ውስጥ ባለፍህ ጊዜ ከአንተ ጋር እሆናለሁ፤ በወንዞችም ውስጥ ባለፍህ ጊዜ አያሰጥሙህም፤ በእሳትም ውስጥ በሄድህ ጊዜ አትቃጠልም፤ ነበልባሉም አይፈጅህም፡፡›› (ኢሳ.፵፪፥፪)

እኛ እንደነ ቅዱስ ቂርቆስ እና ቅድስት ኢየሉጣ ከእሳት እና ከፈላ ውኃ ውስጥ ጨክኖ በመግባት በእምነት መውጣት የምንችልበት አቅምም ሆነ የጸሎት ኃይል ባይኖረንም በልባችን ጋን ውስጥ እየነደደ ለሀገራችን ኢትዮጵያም የተረፈው በፍቅርና በአንድነት እንዳንኖር ያስቸገረንን ክፉ እሳት አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልን ልኮ እንዲያጠፋልን መለመን ይገባል፡፡ ለዚህም የአምላካችን ልዑል እግዚአብሔር ቸርነት፣ የመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል አማላጅነት አይለየን!

ምንጭ ፡-
• መጽሐፍ ቅዱስ
• ድርሳነ ቅዱስ ገብርኤል ዘሐምሌ
• የመዝሙረ ዳዊት ትርጓሜ
• መጽሐፈ ስንክሳር
• መልክአ ሥላሴ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን !“እግዚኦ ሚ በዝኁ እለ ይሣቅዩኒ፦አቤቱ፥ የሚያስጨንቁኝ ምንኛ በዙ ! ” (መዝ. 3፡1)                    በጎፋ ዞን፣ በ...
24/07/2024

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን !

“እግዚኦ ሚ በዝኁ እለ ይሣቅዩኒ፦አቤቱ፥ የሚያስጨንቁኝ ምንኛ በዙ ! ”
(መዝ. 3፡1)



በጎፋ ዞን፣ በገዜ ጎፋ ወረዳ፣ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት ናዳ እጅግ ብዙ የሚሆኑ ወገኖቻችን በመሞታቸው ታላቅ ኀዘን ተሰምቶናል ። ምንም እንኳ የመከራ ድሀ ባንሆንም ይህ መከራ ለነጋሪውም ለሰሚውም ከባድ መሆኑን እንገነዘባለን ።

ይሁን እንጂ ጭንቀታችን ብዙ ቢሆንም እግዚአብሔር መልካም የምንሰማበትን ዘመን እንደሚያመጣ ተስፋ እናደርጋለን ።

በተለይም ደግሞ እኛ ክርስቲያኖች በወገኖቻችን መጎዳት ብናዝንም በትንሣኤ ሙታን ስለምናምን የምንጽናና በመሆኑ የሞቱት ልጆቻችን ዕረፍተ ነፍስ እንዲያገኙ እየጸለይን፤ የመከራው ገፈት ቀማሽ ለሆኑት የአካባቢው ማኅበረሰብእ ሁለንተናዊ ድጋፍ በማድረግ ሁሉም አቅሙ በፈቀደው መጠን እንዲደርስላቸው ስንል አባታዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን።

እግዚአብሔር አምላክ ለቤተሰቦቻቸውና ለሕዝቡ መጽናናትን ይስጥልን፤ ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
አሜን።

አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ
ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም
ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት

ሐምሌ 17 ቀን 2016 ዓ.ም. ዋሽንግተን ዲሲ~ አሜሪካ

Address

Shashemene

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት ሕዝብ ግንኙነት Qunnamtii Ummataa Kutaa Lallaba Arsii Lixaa posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to የምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት ሕዝብ ግንኙነት Qunnamtii Ummataa Kutaa Lallaba Arsii Lixaa:

Share