03/03/2026
የአራተኛ ዓመት ክብረ በዓል – የመጨረሻ ቀን ኮንፈረንስ 🔥
በእግዚአብሔር ጸጋ የጀመርነውን የአራተኛ ዓመት ክብረ በዓል ዛሬ በድል አጠናቀናል! የመጨረሻው ቀን ኮንፈረንስ ከተጀመረበት ሰዓት ጀምሮ እስከ መዝጊያው ድረስ በክብርና በመንፈስ ኃይል የተሞላ ድንቅ ጊዜ ነበር።🔥
እግዚአብሔር ከእኛ ጋር እንደነበረ በግልፅ ተመልክተናል፤ ልቦች ተለወጡ፣ እምነት በረታ፣ ተስፋ ለመለመ።
“ይህን ሁሉ በምንወደው በእርሱ እጅግ እንሻላለን” (ሮሜ 8፥37) የሚለው ቃል በእውነት ተፈጸመ፤ በእርሱ ረዳትነት በድል አጠናቀናል።
በዚህም ቀን በቃል በዝማሬ ያገለገሉን
ነብይ ገዳ
ነብይ ንጉሴ
ነብይ እሸቱ
ዘማሪ ለሎ
እንዲሁም የቤተክርስቲያናችን አገልጋዬች በሙሉ ጌታ አብዝቶ ይባርካቹ ተባረኩ🙏
ከጎናችን ቆማችሁ በጸሎት፣ በመገኘትና በድጋፍ ያበረታችሁን ሁሉ እናመሰግናለን።
በፍቅርና በትጋት ያገለገላችሁ አገልጋዮቻችን እግዚአብሔር አገልግሎታችሁን ይባርክ፣ ድካማችሁን በብዙ በረከት ይተካ።🙏
ከሁሉ በላይ ግን ምስጋናችን ለረዳን አምላክ ይሁን፤ መጀመሪያችንም መጨረሻችንም እርሱ ነው። ክብር ለእርሱ ይሁን🙏