Waldaa Duuka Bu'ootaa wiirtuu Sabbataa

Waldaa Duuka Bu'ootaa wiirtuu Sabbataa Tajaajila Afuuraa Afaan Oromootiin

Hunduu qophaa'eera kottaa🙏Ayyaana hundeeffama WDB waggaa 14ffaa sababeeffachuun Waldaan WDBWS sagantaa Afuurawaa guddaa ...
27/01/2026

Hunduu qophaa'eera kottaa🙏
Ayyaana hundeeffama WDB waggaa 14ffaa sababeeffachuun Waldaan WDBWS sagantaa Afuurawaa guddaa Mana Kiristaana D/N/Q/G sabbataatti qopheesse irratti argamuun qooddattoota sagantichaa akka taataniif affeeramtaniirtu🙏 WDBWS

Baga ifa cuuphaa Gooftaa fi Fayisaa keenyaan isin ga'e jechaa obboloonni sabbataa fi naannawashee jirta miseensota WDBWS...
17/01/2026

Baga ifa cuuphaa Gooftaa fi Fayisaa keenyaan isin ga'e jechaa obboloonni sabbataa fi naannawashee jirta miseensota WDBWS waliin ayyaanicha akka dabarsitan kabajaan isiniif dhaamna! Koree hoji raawwachiistuu WDBWS irraa

Yaa'ii ji'aaWaldaan duuka bu'ootaa Wiirtuu sabbataa ji'a ji'aan gaafa 27 yaa'ii afuurawaa ni gaggeessa. egaa har'as 27/4...
05/01/2026

Yaa'ii ji'aa

Waldaan duuka bu'ootaa Wiirtuu sabbataa ji'a ji'aan gaafa 27 yaa'ii afuurawaa ni gaggeessa. egaa har'as 27/4/2018 sa'atii 11: 30 irraa eegalee yaa'iin ji'aa keenya waan itti fufuuf Akka irratti argamtan isin afeerra.

Baga jala bultii ayyaana ifa dhalachuu Gooftaa Keenyaa geessan jechaa ayyaanicha sababeeffachuun qophii addaa WDB wiirtu...
05/01/2026

Baga jala bultii ayyaana ifa dhalachuu Gooftaa Keenyaa geessan jechaa ayyaanicha sababeeffachuun qophii addaa WDB wiirtuu sabbataa Wiirtuu muummee waliin ta'uun isiniif qophee karaa fuula miidiyaa TV Sagalee Dhugaa daawwadhaa🙏

ከወልዳ ዱከ ቡኦታ የተሰጠ ወቅታዊ መግለጫ“በባልንጀራህ ላይ በሐሰት አትመስክር” (ኦሪት ዘጸአት 20:16)ሰሞኑን በዋልዳ ዱከ ቡኦታ ጠቅላላ ማኀበር ላይ የተከፈተውን የስም ማጥፋት ዘመቻ አጥ...
20/12/2025

ከወልዳ ዱከ ቡኦታ የተሰጠ ወቅታዊ መግለጫ

“በባልንጀራህ ላይ በሐሰት አትመስክር” (ኦሪት ዘጸአት 20:16)

ሰሞኑን በዋልዳ ዱከ ቡኦታ ጠቅላላ ማኀበር ላይ የተከፈተውን የስም ማጥፋት ዘመቻ አጥብቀን እንቃወማለን!
ወልዳ ዱከ ቡኦታ ጠቅላላ ማኀበር በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በአፋን ኦሮሞ መንፈሳዊ አገልግሎት ለመስጠት በ2004 ዓ.ም ተመሠረተ። ከተመሰረተ ጊዜ አንስቶም በተለያዩ አህጉረ ስብከት ከሚገኙ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ጋር በመነጋገር የአገልግሎት ፈቃድ በማግኘት በአፋን ኦሮሞ በሚሰጥ መንፈሳዊ አገልገሎት ላይ ትኩረት በማድረግ የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንን ዶግማ፤ቀኖና እና ትዉፊትን መሰረት በማድረግ ሲያገለግል ቆይቷል፣ እያገለገለም ይገኛል። በ2013 ዓ.ም ደግሞ ከጠቅላይ ቤተ ክህነት በመላው አሮሚያ እንዲያገለግል የተፈቀደለት ሲሆን ቤተክርስቲያናችን በ2015 ዓ.ም በሥሯ የሚንቀሳቀሱ አዲስም ይሁን ነባር መንፈሳዊ ማኅበራትን ለመመዝገብ እና ለመቆጣጠር ባወጣችው መመሪያ መሠረት የተጠየቁ መስፈርቶችን ሁሉ አሟልቶ ሰኔ 27 ቀን 2016 ዓ.ም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የማኀበራት ምዝገባ፣ ክትትል እና ቁጥጥር መመሪያ ሥር ተመዝግቦ፣ ቤተክርስቲያን ባለችበት ቦታ ሁሉ እንዲያገለግል የጠቅላላ ማኀበር እውቅና አግኝቷል።

ማኀበሩ ባለፉት አሥራ አራት ዓመታት በቤተክርስቲያናችን ውስጥ የነበረውን የአፋን ኦሮሞ አገልግሎት እጥረት በመቅረፍ ረገድ ከፍተኛ አስተዋፅዖ አድርጓል። አርአያነት ያላቸው በርካታ ጠንካራ ሥራዎችን ሲሠራ የቆየ እና አሁንም እየሠራ የሚገኝ መንፍሳዊ፤ አርቶዶክሳዊ ተቋም ነወ፡፡ ማኅበሩ ካከናወናቸው በርካታ ሥራዎች መካከልም፦በመንፈሳዊ ምጽህፍት ትርጉም ረገድ አዲስ ኪዳንን፣ መጽሐፈ ስንክሳርን፣ ሃይማኖተ አበውን፣ መጽሐፈ ግጻዌን፣ መጽሐፈ ክርስትና እና ተክሊልን፤ ገድለ መጥመቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስን እና የመሳሳሉትን መጽሐፍት ወደ አፋን ኦሮሞ ተርጉሞ ለአገልግሎት አብቅቷል፡፡ ቤተ ክርስቲያናችን በአፋን ኦሮሞ አሳትማ እየተጠቀመችበት ያለውን ቃለ ዓዋዲን በነፃ ወደ አፋን ኦሮሞ ተርጉሞ ለጠቅላይ ቤተ ክህነት አስረክቧል። የእነዚህ ቅዱሳት መጸሕፍት መተርጎም ቤተ ክርስቲያናችን በአፋን ኦሮሞ የምትሰጠውን አገልግሎት በከፍተኛ ደረጃ ያሳደገ እና በዚህ ረገድ በቤተ ክርስቲያናችን ላይ ሲነሱ የነበሩ ጥያቄዎችንም የቀረፈ ነወ።

ምዕመናን በተለይም ወጣቶች ስለ ሃይማኖታቸው በቂ ግንዛቤ እና እውቀት ኖሯቸው በሃይማኖታቸው እንዲጸኑ የተለያዩ መንፈሳዊ መጻሕፍትን ለምዕመናን አድርሷል። ማኀበሩ በመላው ኦሮሚያ የዞን ማዕከላት፣ የወረዳ ማዕከላት፣ ቅርንጫፎች፣ እንዲሁም የውጭ ሃገር ማዕከላትን በመክፈት ክርስቲያኖች በእነዚህ የማኅበሩ መዋቅራት ሥር ታቅፈው የቤተ ክርስትያናችንን መሰርታዊ አስተምህሮ እንዲረዱ አንዲሁም በሕብረት ሆነው ቅድስት ቤተክርስቲያንን እንዲያገለግሉ በማድረግ ታላቅ ሥራ ሠርቷል። ከገጠር እስከ ከተማ በሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት፣ ውስጥ ታላላቅ መንፈሳዊ ጉባኤያትን በማዘጋጀት ምዕመናን በሚረዱት ቋንቋ የእግዚአብሔርን ቃል እንዲማሩ የድርሻውን እየተወጣ ይገኛል፡፡ መንፈሳዊ ጉዞዎችን በማዘጋጀትም ምዕመናን ወደ ቅዱሳን ቦታዎችና ገጠር አብያተ ክርስቲያናት በመሄድ የሃይማኖታቸውን ታሪክ እንዲረዱ፣ በገጠር የሚገኙ ክርስቲያኖችን እንዲያበረታቱና እንዲደግፉ ሲያደርግ ቆይቷል። በዚህም ረገድ “ኦርቶዶክስ የሌላ ብሄር ሃይማኖት ነው” የሚለዉን የተቀዋሚዎቻችንን የተሳሳተ አመለካከት ለማስቀረት ማኅበሩ ግንባር ቀደምና ውጤታማ ተግባር ፈጽሟል።

ከሁሉም በላይ በተለያዩ ጊዜያትና ቦታዎች በክርስቲያኖች ላይ የሚፈጸሙ ግድያዎችንና መፈናቀሎችን በመቃወም መግለጫዎችን በማውጣት ግንባር ቀደም ሆኖ ድምጹን ሲያሰማ ቆይቷል፤ አሁንም እያሰማ ይገኛል። ማኀበሩ እነዚህን መንፈሳዊ ሥራዎች የሠራው በተመቻቸ ሁኔታ ወስጥ ሆኖ ሳይሆን በየቦታዎቹ እና በየጊዜያቱ የሚያጋጥሙ እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚደርሱ በርካታ ፈተናዎችን በእግዚአብሔር እርዳታ በማለፍ ነው።

ከዚህ ጋር ተያይዞ ሁልጊዜ የማይረሱት የማኀበሩ ዋና ማዕከል የትምህርት ክፍል ኃላፊ የነበሩት መጋቢ ሃይማኖት ቀሲስ ጴጥሮስ ተስፋዬ እንዲሁም የአለምገና ቅዱስ ጊዮርጊስ ቅርንጫፍ የንስሐ አባት የነበሩት ቀሲስ ዮሐንስ ግርማ ይህንኑ አገልግሎት በመደገፋቸው ብቻ በማኀበሩ እየተሰጠ ያለው አገልግሎት እንዳይስፋፋ በሚፈልጉ አካላት ተሰውቷል። በማኀበሩ አባላት ላይም የስም ማጥፋት ዘመቻዎች፣ ከስራ እና ከሚኖሩበት አከባቢ የማፈናቀል ሴራዎች፣ድብደባዎቸ፣ ዛቻዎች እና ተደጋጋሚ እስሮች፤ሲደርሱበት ቆይቷል፡፡ ማኀበሩ ግን የሐዋርያትን መንገድ ተከትሎ ስለተመሠረተ እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት በእግዚአብሔር እርዳታ እና በመንፈሳዊ ተጋድሎ እና ጥንካሬ የሚደርስበትን ፈተና በመቋቋም እስከ ዛሬ ደርሷል።

ሰሞኑን በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ሀገረ ስብከት በወልዳ ዱካ ቡኦታ ሆሮ ጉዱሩ (ሻምቡ) ማዕከል የማኅበራችን አባል እና የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ በነበሩት በመልአከ ኤዶም ቀሲስ ዱጉማ ዱፋ እንዲሁም በቀሲስ ደሳለኝ ነሞምሳ ላይ በማይታወቁ አካላት አሰቃቂ ግድያ መፈጸሙን በተመለከተ ማኅበሩ በሚዲያው ይህንን ልብ ሰባሪ ድርጊት በማዉገዝ ሀዘኑን መግለጹ ይታወሳል፡፡ መልአከ ኤዶም ቀሲስ ዱጉማ ዱፋ በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ሀገረ ስብከት ከሥራ አስኪያጅነታቸው በተጨማሪ የማኀበሩን ዓላማ በማመን አብሮም ለማገልገል አባል በመሆን በማኀበሩ ወስጥ ከፍተኛ አስተዋፅዖ ሲያበረከቱ የነበሩ አባት ነበሩ፡፡

ይሁን እንጂ ማኅበራችን በአባቶቻችን ላይ በደረሰው በዚህ ልብ ሰባሪ ሀዘን ሳለ ዛሬም ማኅበሩን በማሳደድና አገልግሎቱን ወደ ኋላ ለማስቀረት ተግተው እየሰሩ በሚገኙ ግለሰቦች ጉዳዩን እንደመልካም አጋጣሚ በመጠቀም እና ወደ ማኅበሩ በማዞር ለታሪክ ይቅር የማይባል እና በእግዚአብሔርም ዘንድ ትልቅ ኃጥአት የሆነውን የስም ማጥፋት ዘመቻ በሰፊዉ ከፍተውበት ይገኛሉ። ከተፈጸመው ግድያ ጋር በማያያዝ፣ የሞቱት አባት የማኅበሩ አባል ሆነው ሳለ ለደረሰባቸው ግድያ የማኀበሩ እጅ እንዳለበት በማስመሰል፣ ሆን ብለው በማኅበራዊ ሚዲያ ገጾቻቸው ላይ የስም ማጥፋትና የማጠልሸት ሥራቸውን በውሸት ጽሑፍ እና በተቀናበረ ፎቶ በመልቀቅ ሕዝበ ክርስቲያኑን እያደናገሩ ይገኛሉ። የሚመለከታቸው የጸጥታ አካላት ጉዳዩን እያጣሩ ባሉበት በዚህ ወቅት፣ ራሳቸውን ከወንጀሉ ነጻ አድርገው እንደ ወንጀል መርማሪ ሆነው በጸጥታ አካላት የምርመራ ሂደት ላይ ተጽዕኖ በመፍጠር ያለ ምንም ማስረጃ ማኀበሩን በመወንጀል ላይ ይገኛሉ። ይሁን እንጂ እነዚሁ ከሳሾቻችን ቀደም ሲል ከማኀበሩ ጋር ሆነው በአፋን ኦሮሞ ስላገለገሉ ብቻ በብዙ የማኅበሩ አባላት አባቶች ላይ ግድያ ሲፈጸም ምንም እንዳልተፈጠረ ዝምታን መርጠው የነበሩ ናቸው።

ወልዳ ዱከ ቡኦታ የተቋቋመው የቅድስት ቤተክርስቲያናችንን አገልግሎት ለማስፋፋት እንጂ ስም አጥፊዎች የማኅበራችንን አገልግሎት ወደ ኋላ ለመመለስ የሚጥሩ አካላት እንደሚሉት የቤተክርስቲያን አገልጋዮችን መግደል ወይም ለማስገደል የተቋቋመ አይደለም። ይልቁንም ማኀበራችንማ ሲሰደድ፣ ሲታሰርና ሲገደል ቆየ እንጂ አሳዳጅ ሆኖ ኖሮ አያውቅም። የቤተክርስቲያናችንን የወንጌል አገልግሎት ሕዝቡ በሚሰማው ቋንቋ የማስፋፋትና በዚሁ በቋንቋ አገልግሎት እጥረት ምክንያት ከቤተክርስቲያናችን የተለዩትን የመመለስ እንጂ ሌላ ልዩ ምድራዊ እና ሥጋዊ ዓላማ የለውም።

እንዲህ ዓይነቱ በደቦ በግልጽም ሆነ በእጅ አዙር በሚያደርጉት የስም ማጥፋት ዘመቻ እነሱ አንድሚመኙ እና እንደሚያልሙት ማኅበሩ በቋንቋ የጀመረዉን ሰፊ አገልግሎት ወደ ኋላ የሚመልሰው ሳይሆን፣በሙሉ ጉልበት እና ኃይል በሀገር አቀፍ እና ዓለም አቀፍ ደረጃ ተስፋፍቶ የሚቀጥል ይሆናል፡፡ ለዚሁም ደግሞ አምለከ ቅዱሳን ሐዋርያት እንደሚረዳን እና የቅዱሳን ሐዋርያት አባቶቻችን ምልጃና ጸሎትም እንደማይለየን በፍጹም ልባችን እናምናለን፡፡

በመሆኑም በመላ ሀገራችን፤በውስጥ እና በውጭ በተለያዩ ቦታዎች የምትገኙ የማኅበሩ አባላት በጸሎት በመትጋት የጥንታዊት፤ሐዋርያዊት ኩላዊት እና የቅድስት ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያናችንን አገልግሎት ከቀድሞ በበለጠ አብዝታችሁ ተግታችሁ እንድትቀጥሉ ጥብቅ መልእክታችንን እናስተላልፋለን። እንዲሁም ምዕመናንም ልዩ አጀንዳ ያነገቡ ግለሰቦች ለሚለጥፉት ከፋፋይ የጥላቻ መልዕክቶች ቦታ ሳይሰጡ በአንድነት እንዲቆሙ ማኅበራችንንም በጸሎት እንዲያስቡ እንጠይቃለን፡፡

በመጨረሻም ጉዳዩ የሚመለከታቸው የፀጥታ አካላት ምርመራቸውን ጨርሰው በእነዚህ አባቶች ላይ እንዲህ ያለውን ዘግናኝ እና አጸያፊ እንዲሁም ርህራሄ አልባ ኢሰብአዊ ድርጊት የፈጸሙትን አካላት ለሕግ በማቅረብ፣ የአባቶቻችንን ፍትህ ለህዝብ እንዲያሳውቁ በትህትና እንጠይቃለን። በተጨማሪም በተናበበ እና በተቃናጀ መልኩ በየማኀበራዊ ሚዲያዎቻቸው መልካሙን የማኀበራችንን ቅዱስ አገልግሎት እና ስሙንም እያጠፉ ያሉትን እንደ፦ ‘ስማዐ ተዋሕዶ፣ Tewahedo ተዋህዶ፣ Adebabay Media እና ቀሲስ ኤፍሬም እሸቴ፣ እቅበተ ተዋህዶ፣ Kumneger/ቁምነገር፣ Birhanu Admass Anleye፣ Simur Alamrew፣ Arega Abate፣ Tsegaye Kiflu፣ Maryamawit Henok Lamesa እና ሌሎችም’ ለጊዜዉ ያላቸውን የተከታይ ቁጥር ብዛት እንዲሁም ታዋቂነታቸውን ለዚህ ክፉ እና ጠማማ ዓላማቸው እንደመልካም አጋጣሚ በመጠቀም መረጃዎችን በማዛባት እና ትክክለኛ መረጃ እንዳላቸው በማስመሰል ሕዝብን ከሕዝብ የሚያጋጭ፤ ቤተ ክርስቲያንን የሚከፋፍል እና ለሌላ ፈተና የሚጋብዝ ኢሚዛናዊ፣ ኢኦርቶዶክሳዊ የጥላቻ መልዕክት በመሆኑ ከዚህ ክፉ ተግባራቸው እንዲቆጠቡ እንደወትረው ሁሉ በክርስቲያናዊ ወንድማማችነት ፍቅር እያሳሰብን፤ ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት በሕብረተሰቡ መካከል እንዲህ ያለውን አግባቢነት የሌለውን እና ውዥንብር የሚፈጥር ተግባር የሚያሰራጩትን ሁሉ እንዲከታተል እናሳስባለን፡፡

የአባቶቻችን የቅዱሳን አምላክ እግዚአብሔር ክፉውን ሁሉ ከመላው ሀገራችን እና ከሕዝባችን እንዲያርቅልን እንጸልያለን፡፡

በኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን ወልዳ ዱከ ቡኦታ ጠቅላላ ማኀበር
ታኅሣሥ 10/2018 ዓ.ም፣ አዲስ አበባ

Waldaan Duuka Bu'ootaa Wiirtuu Sabbataa damee haaraa Kawaala Iyyasuusitti banee xalayaa beekamtii kennee jira. Bara taja...
14/12/2025

Waldaan Duuka Bu'ootaa Wiirtuu Sabbataa damee haaraa Kawaala Iyyasuusitti banee xalayaa beekamtii kennee jira. Bara tajaajilaa gaarii WDB Damee Kawaala Iyyasuusiif🙏

Sagantaa Yaa'ii ji'aa keenya haala gaariin xumurame🙏 Galata Waaqayyoo. Saganticharratti Bsaa Dn Warquun "Kunoo Hoolaa Wa...
07/12/2025

Sagantaa Yaa'ii ji'aa keenya haala gaariin xumurame🙏 Galata Waaqayyoo. Saganticharratti Bsaa Dn Warquun "Kunoo Hoolaa Waaqayyoo kan cubbuu addunyaa haqu" Mata duree jedhuun nu tajaajilaniiru. Ftaa Birhaan waliinis yeroo gaarii qabaanne. Dhumarrattis Abbaan keenya Qomos Abbaa Waldahawwaariyaat gorsa abbummaa isaanii nuuf dabarsuun sagantaa keenya kadhannaan xumurre🙏 Gochasaa himamee hin dhumneef Waaqayyo haa galatu🙏
Sadaasa 27/2018

Waliin haa imallu. WDBWSNamoonni deemuu barbaaddan nu qunnamaa🙏+251910649965+251920202205Iddoon ka'uumsaa Gabri'eelii Sa...
17/11/2025

Waliin haa imallu. WDBWS
Namoonni deemuu barbaaddan nu qunnamaa🙏
+251910649965
+251920202205
Iddoon ka'uumsaa Gabri'eelii Sabbataa
Yeroo ganama 1:00

Sagantaa keenya yaa'ii ji'aa suuraadhaanonk 27/2018
07/11/2025

Sagantaa keenya yaa'ii ji'aa suuraadhaan
onk 27/2018

Waaqa isa nu gargaareef galanni haa ta'u🙏Imala Duuka Bu'ummaa marsaa tokkooffaa haa gaariin dabarsineerra💪
02/11/2025

Waaqa isa nu gargaareef galanni haa ta'u🙏
Imala Duuka Bu'ummaa marsaa tokkooffaa haa gaariin dabarsineerra💪

WDBWS Tajaajila baadiyyaa irratti🙏 Tokko jennee eegalleerra🙏Galaan Qul Mikaa'el❤
02/11/2025

WDBWS Tajaajila baadiyyaa irratti🙏
Tokko jennee eegalleerra🙏
Galaan Qul Mikaa'el❤

Address

Sabbataa
Sebeta

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Waldaa Duuka Bu'ootaa wiirtuu Sabbataa posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share