Nek'emte Emmanuel United Church

Nek'emte Emmanuel United Church Yesuus gooftaa ta'uu labsina.

16/05/2026
  guyyaa ayyaana yaadannoo du'aa ka'uu Yesuus.
13/04/2026

guyyaa ayyaana yaadannoo du'aa ka'uu Yesuus.

  guyyaa yaadannoo du'aa  ka'uu gooftaa keenya Yesuus Kiristoos kan bara 2018.Baga geessan!
12/04/2026

guyyaa yaadannoo du'aa ka'uu gooftaa keenya Yesuus Kiristoos kan bara 2018.

Baga geessan!

የኢትዮጵያ አማኑኤል ኀብረት ቤተክርስቲያን ለግንባታ የሀብት ማሰባሰብ ስራ በይፋ ጀመረች‼️የኢትዮጵያ አማኑኤል ህብረት ቤተክርስቲያን “የሰማይ አምላክ ያከናውንልናል፤ እኛም ባሪያዎቹ ተነስተን...
29/01/2026

የኢትዮጵያ አማኑኤል ኀብረት ቤተክርስቲያን ለግንባታ የሀብት ማሰባሰብ ስራ በይፋ ጀመረች‼️

የኢትዮጵያ አማኑኤል ህብረት ቤተክርስቲያን “የሰማይ አምላክ ያከናውንልናል፤ እኛም ባሪያዎቹ ተነስተን እንሰራለን” (ነህሚያ 2፡20) የሚለውን የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል እንደ መንፈሳዊ መርሆ በማድረግ ከሶስት ዓመታት ቆይታ ክርክር በኋላ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ውሳኔ መሰረት የተረከበችው ቦታ ላይ በአፋጣኝ ግንባታ ለመጀመር የሚያስችላትን የሀብት ማሰባሰብ ስራ ጥር 18/2018 ዓ.ም.በይፋ አስጀመረች ።

ለዚህም የመጀመሪያ ዙር ጥሪ የተደረገላቸው የአጥቢያ መሪዎች በአዲስ አበባ ሳሮ–ማርያ ሆቴል ተገኝተው ውይይት ማድረጋቸውንና ምላሽ መስጠታቸው ተገልጿል።

በተመሳሳይ ቦታ፣ ሀሙስ ጥር 21/2018 ዓ.ም. በሚካሄደው ሁለተኛ ዙር ጥሪ የተጠሩ የአጥቢያ መሪዎችም እንዲገኙ የተጠየቀ ሲሆን፣ ከመጀመሪያው ዙር ጋር ተመሳሳይ አበረታች ምላሽ እንደሚኖር ይጠበቃል።

መረጃው የኢትዮጵያ አማኑኤል ህብረት ቤተክርስቲያን ነው ።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ አና ንጉሴ

15/01/2026

የአማኑኤል ሕብረት ቤተ ክርስቲያን ሕጋዊ ይዞታዋ ተመለሰ ።

የአማኑኤል ሕብረት ቤተ ክርስቲያን ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለስርዓተ አምልኮ ማስፈጸሚያ የሚሆን ቦታ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 02 ተረክባ በተወሰነላት መሰረት አስፈላጊውን ካሳ ከፍላ እያለ ቤቱን ማስረከብ የነበረበት የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በልዩ ልዩ ምክንያት ተፈጻሚ ሳያደርግ መቆየቱ የሚታወስ ሲሆን በኋላም የቤተክርስቲያኒቱን ህጋዊ ይዞታ ለሌላ የሃይማኖት ተቋም አስተላልፎ ነበረ ፡፡

የኢትዮጵያ አማኑኤል ህብረት ቤተክርስቲያን ፕሬዝዳንት መጋቢ ጌታሁን ታደሰ የቤተክርስቲያኗ ህጋዊ ይዞታ መመለሱን በቤተክርስቲያኒቱ ገጽ ባስተላለፉት ልጥፍ መመልከት ችለናል ።ለዚህም ከፍተኛ አስተዋጻኦ ላደረጉ ተቋማት ፣ በተለይም ለኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ፣ ለኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ህብረት ፣ ለሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ ፣ ለከተማ አስተዳደሩና ከጎናቸው ለቆሙ አካላት ሁሉ ምስጋና አቅርበዋል ።

ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ አና ንጉሴ

የኢትዮጵያ አማኑኤል ህብረት የምሥጋና መልክት! የኢትዮጵያ አማኑኤል ቤተ ክርስቲያን የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ሳያስረክብ ፍትሐዊ ጥያቄና አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጥ የኢትዮጵያ አማኑኤል ህብረት ...
15/01/2026

የኢትዮጵያ አማኑኤል ህብረት የምሥጋና መልክት!

የኢትዮጵያ አማኑኤል ቤተ ክርስቲያን የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ሳያስረክብ ፍትሐዊ ጥያቄና አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጥ የኢትዮጵያ አማኑኤል ህብረት በጠየቀችዉ መሰረተ የተመለሰ ሲሆን ለዚህም፦ ምላሽ አግኝተናል። ውሳኔ የሰጡንን የከተማ አስተዳደሩንና በተለያየ መንገድ አብረውን የቆሙትን ሁሉ እናመሰግናለን! ክብር ለጌታ ይሁን! ብለዋል።

⚖️ የኢትዮጵያ አማኑኤል ሕብረት ቤተ ክርስቲያን ሕጋዊ ይዞታዋ በይፋ ተመለሰ  | ለረጅም ጊዜ አወዛጋቢ ሆኖ የቆየውና የቤተ ክርስቲያኒቱ ሕጋዊ መብት ተጥሶ የነበረው የቦታ ይዞታ ጉዳይ፣ በስ...
14/01/2026

⚖️ የኢትዮጵያ አማኑኤል ሕብረት ቤተ ክርስቲያን ሕጋዊ ይዞታዋ በይፋ ተመለሰ

| ለረጅም ጊዜ አወዛጋቢ ሆኖ የቆየውና የቤተ ክርስቲያኒቱ ሕጋዊ መብት ተጥሶ የነበረው የቦታ ይዞታ ጉዳይ፣ በስተመጨረሻ እልባት አግኝቷል።

📜 ጉዳዩ ምን ነበር?

የአማኑኤል ሕብረት ቤተ ክርስቲያን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አማካኝነት በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 02 ለሥርዓተ አምልኮ ማስፈጸሚያ የሚሆን ቦታ ተረክባ፣ የሚጠበቅባትን የካሳ ክፍያ በሙሉ ፈጽማ ነበር።

ሆኖም ቤቱን ማስረከብ የነበረበት የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በተለያዩ ምክንያቶች ሳይፈጽም በመቆየቱና ይባስ ብሎም ይዞታውን ለሌላ የሃይማኖት ተቋም አሳልፎ በመስጠቱ ጉዳዩ ወደ ከፍተኛ ውዝግብ አምርቶ ቆይቷል።

✨ የምስጋና መልዕክት

የኢትዮጵያ አማኑኤል ሕብረት ቤተ ክርስቲያን ፕሬዝዳንት መጋቢ ጌታሁን ታደሰ፣ የቤተ ክርስቲያኒቱ ሕጋዊ ይዞታ መመለሱን በይፋ አረጋግጠዋል።

ፕሬዝዳንቱ ይህ ውጤት እንዲገኝ ላበረከቱ አካላት ባስተላለፉት የደስታ መግለጫ የሚከተሉትን አመስግነዋል፦

* ለኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል

* ለኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ሕብረት

* ለኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ

* ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና ከጎናቸው ለቆሙ አጋሮች ሁሉ።

ይህ ውሳኔ የሃይማኖት ተቋማት ሕጋዊ ከይዞታቸው ተከብሮ ሥርዓተ አምልኳቸውን ያለ ስጋት እንዲያከናውኑ የሚያስችል ሲሆን፣ በተቋማት መካከል የሚፈጠሩ የይዞታ ጥያቄዎች በውይይትና በሕግ አግባብ መፈታታቸው ለዘላቂ ሰላም ያለውን ፋይዳ የሚያሳይ ነው።

#አማኑኤልሕብረት #ፍትህ #ቤተክርስቲያን #አዲስአበባ #ቂርቆስ #ኢትዮጵያ #ወንጌልአማኞች #ፍትህተረጋገጠ

  irraa hin hafinaa
10/01/2026

irraa hin hafinaa

29/12/2025

አጭር ማስታወሻ

የኢትዮጵያ አማኑኤል ህብረት ቤተክርስቲያን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ወስኖ የሰጣትን 1298ካሬ ሜ. ቦታ ሙሉ ለሙሉ መረከብ እንዳትችል በዋናነት የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን የካሳ ግምት የተቀበለበትን ቦታ ውል አቋርጦ ለቤተክርስቲያኒቱ ማስረከብ ሲገባው ለሌላ አካል ማከራየቱን ተከትሎ የገጠመንን ፈተና ከታህሳስ 14/2018ዓ.ም ጀምሮ ስናሳውቃችሁ ቆይተናል።
ምንም እንኳ በቦታው ላይ ምንም አይነት እንቅስቃሴ እንዳይደረግ አሁንም የፀጥታ አካላት ተገቢውን ጥበቃ እያደረጉ ቢሆንም ከኮርፖሬሽኑ መስተዳድርንም ሆነ ከሚመለከታቸው አካላት ይህ ማስታወሻ እስከተቀመጠበት ጊዜ ድረስ ምንም አይነት የውሳኔ ሀሳብ አልሰማንም።
ስለሆነም የጉዳዩን መጨረሻ ለመስማት ተግታችሁ የምትጠይቁንን ሁሉ እያመሰገንን አሁንም በፀሎት ከጎናችን እንድትሆኑ በአክብሮት እንጠይቃለን።

በዚህ አጋጣሚ የግለሰቦችን ስም ባልተገባ መልኩ ለማንሳት መሞከር የቤተክርስቲያናችን እምነት እና አቋም ስላልሆነ ጥንቃቄ እንድታደርጉ ለማስታወስ እንወዳለን

በእኛ በኩል ግን የሚመለከታቸው አካላት የቤተክርስቲያኒቱን ፍታሀዊ ጥያቄ ፈጥነው ይመልሳሉ ብለን በጽኑ እናምናለን።
እግዚአብሔር ምድራችን ይባርክ!!

Address

Oromia Regional State
Nek'emte

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Nek'emte Emmanuel United Church posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Nek'emte Emmanuel United Church:

Share