The Firstborn Assembly Church

The Firstborn Assembly Church Welcome to The Firstborn Assembly Church official page. Like, share, invite, and follow us. Nazareth, Ethiopia. Know more, do better, get ALL.

The Firstborn Assembly Church work hard for the likelihood of the Church to bring maturity and fulfillment of the mission (Ephesians 4:13) through the rightly divided word of God, since 2002!

 መንፈሳዊ ነገር ከእኛ አይጀምርም። ከእኛ ከጀመረ አንድ ቀን መብረድና መቆሙ አይቀርም። በመንፈስ ያልተጀመረ በሥጋ አይገለጥም። የሚታየው ከማይታየው ነው። ሥር አይታይም ነገር ግን የሚታይ ፍ...
18/05/2024


መንፈሳዊ ነገር ከእኛ አይጀምርም። ከእኛ ከጀመረ አንድ ቀን መብረድና መቆሙ አይቀርም። በመንፈስ ያልተጀመረ በሥጋ አይገለጥም። የሚታየው ከማይታየው ነው። ሥር አይታይም ነገር ግን የሚታይ ፍሬ እንዲያፈራ ያደርጋል። ክርስቶስ የቤተክርስቲያን ሥርና መሠረት እንጂ ስምና መታወቂያ አይደለም። የአንድን ዛፍ ፍሬ ሁኔታ የሚወስነው ሥሩ ነው። ብዙ ሰዎች ግን የሚጨነቁት ስለ ፍሬው እንጂ ስለ ተተከሉበት ሥር አይደለም። ክፉ ዛፍ ክፉ ፍሬ፣ መልካም ዛፍ መልካም ፍሬ እንደሚያፈራ እኛም መልካም ፍሬ እንድናፈራ እግዚአብሔር ክርስቶስ ላይ ተክሎናል። የምናፈራው ፍሬ የክርስቶስ አይነት ነው። ክርስቶስ ላይ ስለ ተተከልን እርግጠኛና የተማመነ የሕይወት ምስክርነት (ፍሬ) አለን።

  #ወንጌል፡-1. የሰዎች አመጽና ክፋት እየጨመረ ሲሄድ እግዚአብሔር ምን ላድርግ ብሎ ተጨንቆ የፈጠረው የማስጠንቀቂያ ድምጽ ወይም ዘዴ ሳይሆን፥ ዓለሙን ለማዳን ወደ ምድር የላከው በዘመናችን...
17/05/2024


#ወንጌል፡-
1. የሰዎች አመጽና ክፋት እየጨመረ ሲሄድ እግዚአብሔር ምን ላድርግ ብሎ ተጨንቆ የፈጠረው የማስጠንቀቂያ ድምጽ ወይም ዘዴ ሳይሆን፥ ዓለሙን ለማዳን ወደ ምድር የላከው በዘመናችን ከምናየው አሳሪ፣ ኮናኝና አፍራሽ መልዕክት በተቃራኒ ገንቢና አዎንታዊ የሆነ መልካም ዜና ነው፡፡

2. ክርስቶስ በድካም ተሰቅሎ በእግዚአብሔር ኃይል የተነሳበት፣ ከሰው ብርታት ይልቅ የእግዚአብሔር ድካም የበረታበት፣ ከሰው ጥበብ ይልቅ የእግዚአብሔር ሞኝነት የተጠበበበት መለኮታዊ እቅድና አላማ ነው (1 ቆሮንቶስ 1፡26-29)፡፡

3. የሕይወት ፈተናዎችን ፈርተን ከዓለም የምንሸሽበት፣ የምናመልጥበትና የምንደበቅበት ሳይሆን ፊት ለፊት የምንጋፈጥበት ነው፡፡

4. ሊፈቱና ሊፈጸሙ የማይችሉ የሚመስሉትን፣ በማንኛውም ደረጃ ለሚነሱ የሰው ልጆች ጥያቄዎች የተብራራ መልስ የሚሰጥ መልዕክት ነው፡፡

 ሰው የእግዚአብሔር ዋነኛው ትኩረትና የልቡ አሳብ ነው። እግዚአብሔር ከሰው በላይ ምንም ትኩረት የለውም። የአሳቡ ማዕከል ሰው ነው። መጽሐፍ ቅዱስ የሚናገረው ስለ ሰው ነው። ወንጌል ስለ ሰው...
12/05/2024


ሰው የእግዚአብሔር ዋነኛው ትኩረትና የልቡ አሳብ ነው። እግዚአብሔር ከሰው በላይ ምንም ትኩረት የለውም። የአሳቡ ማዕከል ሰው ነው። መጽሐፍ ቅዱስ የሚናገረው ስለ ሰው ነው። ወንጌል ስለ ሰው ነው። ስለ ሰው ማውራት በየትኛውም መስፈርት ስህተት ሊሆን አይችልም። ስለ ሰው ማውራት የክርስቶስን ሥራ አይጋርድም። በወንጌል እውነት ስለ ሰው ማውራት የእግዚአብሔርን ስም በምድር ላይ ማመስገንና ከፍ ከፍ ማድረግ ነው። ሰውን ሸፍኖ ስለ እግዚአብሔር ማውራት ግን ስህተት ነው።

 ኢየሱስ 99% ሰው ሆኖ 1% አምላክ ቢሆን ማንም ሊድን አይችልም ነበር። ምክንያቱም የጎደለው የ1% የኃጢአት ደመወዝ ሞት ነውና። ለዚህ ነው ኢየሱስ 100% ሰው የሆነውና   የተባለው። "ስ...
10/05/2024


ኢየሱስ 99% ሰው ሆኖ 1% አምላክ ቢሆን ማንም ሊድን አይችልም ነበር። ምክንያቱም የጎደለው የ1% የኃጢአት ደመወዝ ሞት ነውና። ለዚህ ነው ኢየሱስ 100% ሰው የሆነውና የተባለው። "ስለዚህ የሕዝብን ኃጢአት ለማስተስረይ፥ ለእግዚአብሔር በሆነው ነገር ሁሉ የሚምርና የታመነ ሊቀ ካህናት እንዲሆን፥ በነገር ሁሉ ወንድሞቹን ሊመስል ተገባው" (ዕብ. 2:17)። የሰው ልጅ ማለት የሰውን ማንነት ሙሉ ለሙሉ የተካፈለ ወይም በነገር ሁሉ ወንድሞቹን የሚመስል ማለት ነው።

እንዲሁም ኢየሱስ 99% አምላክ ሆኖ 1% ሰው ቢሆን ድነት የሚባል ነገር አይኖርም ነበር። ከአምላክነቱ 1% ቢጎድል ሰውንና እግዚአብሔርን ማስታረቅ ወይም ወደ አንድነት (ሕብረት) ማምጣት አይችልም ነበር። ለዚህ ነው ኢየሱስ 100% በሥጋ የተገለጠ አምላክ ስለሆነ ዓለሙን ከራሱ ጋር ያስታረቀው። "እግዚአብሔር በክርስቶስ ሆኖ ዓለሙን ከራሱ ጋር ያስታርቅ ነበርና፥ በደላቸውን አይቆጥርባቸውም ነበር፤" (2ቆሮ. 5:19)

(1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች ምዕ. 15)----------45፤ እንዲሁ ደግሞ። ፊተኛው ሰው አዳም ሕያው ነፍስ ሆነ ተብሎ ተጽፎአል፤ ኋለኛው አዳም ሕይወትን የሚሰጥ መንፈስ ሆነ።46፤ ነገር ግን...
08/05/2024

(1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች ምዕ. 15)
----------
45፤ እንዲሁ ደግሞ። ፊተኛው ሰው አዳም ሕያው ነፍስ ሆነ ተብሎ ተጽፎአል፤ ኋለኛው አዳም ሕይወትን የሚሰጥ መንፈስ ሆነ።

46፤ ነገር ግን አስቀድሞ ፍጥረታዊው ቀጥሎም መንፈሳዊው ነው እንጂ መንፈሳዊው መጀመሪያ አይደለም።

" #ፊተኛው፣ #ኋለኛው" እንዲሁም " #አስቀድሞ፣ #ቀጥሎም"
የሚለው ቃል በሥጋ ከመገለጥ ወይም ከመታየት አንጻር ካልሆነ በቀር ከህልውና አንጻር የተነገረ አይደለም። ከህልውና አንጻር ሥጋዊ ማንነት ከመንፈስ ማንነት አይቀድምም። ፊተኛው አዳም ከኋለኛው አዳም በፊት አልነበረም። እርሱ ከፍጥረት ሁሉ በፊት በኩር ነው። ምንም ነገር ሳይኖር በፊት የነበረ ሁሉን የፈጠረና ያስገኘ የዘላለም አባት (ምንጭ) ነው።

 #ስቅለት  ወ   #ትንሣኤበኃጢአት ምክንያት፤ የልቦናችንን ፈቃድና የሥጋችንን ምኞት በማድረግ እንጂ ከፍጥረታችን የቁጣ ልጅች አልነበርንም። "በእነዚህም ልጆች መካከል እኛ ሁላችን ደግሞ፥ የ...
03/05/2024

#ስቅለት ወ #ትንሣኤ
በኃጢአት ምክንያት፤ የልቦናችንን ፈቃድና የሥጋችንን ምኞት በማድረግ እንጂ ከፍጥረታችን የቁጣ ልጅች አልነበርንም። "በእነዚህም ልጆች መካከል እኛ ሁላችን ደግሞ፥ የሥጋችንንና የልቡናችንን ፈቃድ እያደረግን፥ በሥጋችን ምኞት በፊት እንኖር ነበርን እንደ ሌሎቹም ደግሞ ከፍጥረታችን የቁጣ ልጆች ነበርን" (ኤፌ. 2:3)። የክርስቶስን የትንሳኤ ሕይወት ከተካፈልን በኋላ ኃጢአትን፣ በደልን፣ መተላለፍን ማሰብ የለብንም። ምክንያቱም ኃጢአትን ክርስቶስ በሞቱ ሽሮታል፣ ከመንገድም ጠርቆ አስወግዶታል። ያለ ማንም እርዳታ፣ ያለ ማንም እገዛ፣ ማንንም ሳይደገፍ፣ ማንንም ሳይመረኮዝ ብቻውን በፍቃዱ ነፍሱን ለኃጢአት መስዋዕት አድርጎ ከሰጠና ከተነሳ በኋላ ያለ ነውር እና ያለ ነቀፋ ነን። ስለዚህ ትንሳኤና ፋሲካችን (ክርስቶስን) በደስታ እናምልክ።

እግዚአብሔር በኃጢአት ምክንያት በሰው ልጆች ላይ የነበረውን ቁጣና ንዴት ለማብረድ በእኛ ፋንታ ኢየሱስን መስቀል ላይ አልገደለውም። ኢየሱስ የእግዚአብሔር ቁጣ ማብረጃ አይደለም። እግዚአብሔር ...
01/05/2024

እግዚአብሔር በኃጢአት ምክንያት በሰው ልጆች ላይ የነበረውን ቁጣና ንዴት ለማብረድ በእኛ ፋንታ ኢየሱስን መስቀል ላይ አልገደለውም። ኢየሱስ የእግዚአብሔር ቁጣ ማብረጃ አይደለም። እግዚአብሔር በሰው ልጆች ኃጢአት የሚቆጣና የሚናደድ አምላክ አይደለም። እግዚአብሔር ፍቅር ነው።
እግዚአብሔር ኢየሱስን አልገደለውም። የገደለው የእኛ (የሰው ልጆች) ኃጢአት ነው። እግዚአብሔርም የቀጣው ኃጢአትን እንጂ ኢየሱስን አይደለም። የእኛን ኃጢአት ሁሉ ወስዶ እሱ ላይ አፈሰሰው። ስለዚህ መጽሐፍ ኃጢአት እንጂ ኃጢአተኛ አደረገው አይልም። መስቀል ላይ ኃጢአት እንጂ ኃጢአተኛ ሆኖ አይደለም የሞተው። "እኛ በእርሱ ሆነን የእግዚአብሔር ጽድቅ እንሆን ዘንድ ኃጢአት ያላወቀውን እርሱን ስለ እኛ ኃጢአት አደረገው" (2ቆሮ. 5:21)። የኢየሱስ የመስቀል ሞት የኃጢአት እንጂ የኃጢአተኛ ደመወዝ አይደለም ቃሉ እንደሚለው። "የኃጢአት ደመወዝ ሞት ነውና፤ የእግዚአብሔር የጸጋ ስጦታ ግን በክርስቶስ ኢየሱስ በጌታችን የዘላለም ሕይወት ነው።" (ወደ ሮሜ ሰዎች 6:23)። እግዚአብሔርም የሞትን ጣር አጥፍቶ አስነሳው። "እግዚአብሔር ግን የሞትን ጣር አጥፍቶ አስነሣው፥ ሞት ይይዘው ዘንድ አልቻለምና" (ሐዋ. 2:24)። ሲያስነሳው ተነስ ብሎ ጮኾበት አይደለም። የተለየ ውለታ ሊያደርግለትም ፈልጎ አይደለም። በሦስተኛው ቀን ሞት ሊይዘው የማይችል የሕይወት ጥራት ውስጥ ስለ ገባ ሞት አይመጥነውም። (Death was no match for him).

እኛም በትንሣኤ ቀን ከሙታን የምንነሣው ኢየሱስ ከሙታን በተነሣበት መንገድ ነው። ስለ ሙታን ትንሣኤ አሳብና ጽንሰ አሳብ ስለምናውቅ ሳይሆን ሞት የማይመጥነውና ሊይዘው የማይችል የሕይወት ጥራት ውስጥ ስለ ገባን ነው።

28/04/2024


ድነትን በተገቢ ሚዛናዊነት ያለ መረዳትና ያለ ማስተማር በአማኞች ዘንድ ግራ መጋባትን ይፈጥራል:: አንድ አማኝ መዳን በሥራ የሚገኝ ሳይሆን በእግዚአብሔር ጸጋ በነጻ የሚሰጥ ስጦታ መሆኑን በትክክለኛ መንገድ መረዳቱ በእግዚአብሔር እንዲተማመን እንደሚያደርገው ሁሉ፥ ይህን መሠረታዊ ሥርዓት በግልጽ ካልተረዳ፣ ስለ ድነቱ በፍርሃት ያለና ከእግዚአብሔር ጋር ስላለው ግንኙነት እርግጠኛ ያለ መሆን ስሜት ሊፈጠርበት ይችላል።

የድነትን (salvation) ጽንሰ ሃሳብ "በጸጋ ብቻ" የሚለውን ዋና ትምህርት በቅጡ መረዳት እና በአግባብ መያዝ ወሳኝ ጉዳይ ነው። ምክንያቱም በአማኝ ሕይወት እና ኑሮ ውስጥ "በእምነት ጸድቄ በሥራዬ ልቀደስ እችላለሁ" የሚል ሥር የሰደደ አደገኛ አመለካከት አለ። እንደ ንጹህ የጸጋ ወንጌል ትምህርት ከክርስቶስ ተለይቶ በሕግ ለመጽደቅ መሞከር ከክርስቶስ ተለይቶ መውደቅን እንደሚያመጣ (ገላትያ 5:4) ከክርስቶስ ተለይቶ በሕግ ሥራ ለመቀደስ መሞከር መንፈሳዊ ውድቀትን እና ሃይማኖታዊ ሕጋዊነትን (Religious legalism) ያመጣል::

ሰማይ የሚለው ቃል እንደ አግባቡ (አውዱ) ተለዋዋጭ ትርጉም ያለው ቢሆንም፤ እግዚአብሔር ግን ዘፍጥረት 1:1 ላይ ፍጥረታዊውን ዓለም ለመፍጠር አሃዱ ያለበትን ሰማይና ምድር ከፈጠረ በኋላ በፈ...
26/04/2024

ሰማይ የሚለው ቃል እንደ አግባቡ (አውዱ) ተለዋዋጭ ትርጉም ያለው ቢሆንም፤ እግዚአብሔር ግን ዘፍጥረት 1:1 ላይ ፍጥረታዊውን ዓለም ለመፍጠር አሃዱ ያለበትን ሰማይና ምድር ከፈጠረ በኋላ በፈጠረው ሰማይ ውስጥ አልኖረም። በሰማይ ነው የኖረው ካልን ሰማይና ምድር ከመፈጠራቸው በፊት የት ነው የኖረው የሚል ጥያቄ ያስነሳል። እግዚአብሔር ሰማይና ምድርን የፈጠረው ለእራሱ አይደለም ለሰው ልጆች ነው። ለእርሱ አያስፈልጉትም። ሐዋርያው ጳውሎስ እንዳለው እግዚአብሔር የሚኖረው ማንም ሊቀርበውና ሊያየው በማይችል ብርሃን ነው። "እርሱ ብቻ የማይሞት ነው፤ ማንም ሊቀርበው በማይችል ብርሃን ይኖራል፤ አንድ ሰው እንኳ አላየውም ሊያይም አይቻለውም፤ ለእርሱ ክብርና የዘላለም ኃይል ይሁን፤ አሜን" (1ጢሞ. 6:16)። አሁን ደግሞ እኛ ውስጥ።
====================================
👉 ። ዘፍጥረት 1:1 ላይ እግዚአብሔር የፈጠረው ከእኛ በላይ ያለውን ሰማይ እንጂ ሰማያዊ ስፍራን አይደለም። ሰማያዊ ስፍራ ያለና ወደፊትም የሚኖር ነው። ሰማያት ወይም ሰማያዊ ስፍራ መንፈሳዊ ዓለም ነው። እኛም ከክርስቶስ ጋር የተቀመጥነው ሰማይ ሳይሆን ሰማያዊ ስፍራ ነው (ኤፌ. 2:6-7)። (ማቴ. 6:9) ላይ ኢየሱስ "በሰማያት የምትኖር አባታችን ሆይ ሥምህ ይቀደስ" ብላችሁ ጸልዩ ብሎ ያስተማራቸው በሰማያት (በሰማያዊ ስፍራ) ሥሙን እንዲቀድሱ ነው። ሰማያት ቀና ብለን ወደ ላይ ስናይ የምንመለከተው ሰማያዊ ቀለም ሳይሆን ሰማያዊ ስፍራን ወይም መንፈሳዊ ዓለምን (spiritual realm) ነው። (ዕብ. 9:24) ወደ ሰማይ ገባ ማለትና በሰማይ ይኖራል ማለትም ለየቅል ናቸው። ሰማይ (ደመና) ውስጥ ቁጭ ብሎ እኛን የሚያይና የሚቆጣጠር አምላክ በዚያ የለም። በሰማይ ያለው የዝናብ ደመና እንጂ እግዚአብሔር አይደለም። ትናንት ከፍጥረተ ዓለም በፊት ማንም ሊቀርበው በማይችል ብርሃን ይኖር የነበረው እግዚአብሔር አሁን የሚኖረው እኛ ውስጥ ነው።

 ።==================================== #1 አንዳንድ ሰዎች ድነታቸውን እንደማያጡ ቢናገሩም መልካም ባልሆነ ሥራቸው ግን ሽልማታቸውን ወይም አክሊላቸውን ሊያጡ እንደሚችሉ...
24/04/2024


====================================
#1 አንዳንድ ሰዎች ድነታቸውን እንደማያጡ ቢናገሩም መልካም ባልሆነ ሥራቸው ግን ሽልማታቸውን ወይም አክሊላቸውን ሊያጡ እንደሚችሉ ያስባሉ። የጽድቅ አክሊል ላጣ እችላለሁ ማለት ስሜት የሚሰጥ አባባል አይደለም። አመጻና ኃጢአቱ ዳግመኛ የማይቆጠርበት ሰው ሽልማቱን እንዴት ሊያጣ ይችላል? ቅዱሳን አንዴና ለዘላለም ጻድቅ በሆኑበትና ሌላ ጽድቅ በማይጨመርላቸው ሁኔታ እንዴት የጽድቅ አክሊል ሊያጡ ይችላሉ? አንዴ ጻድቅ ከሆን በኋላ ክርስቶስ ሥራችንን መርምሮ የሚጨምርልን ጽድቅ ስለሌለ በአንድ ጊዜ ጻድቅም የጽድቅ አክሊል ማጣትም አይቻልም።

#2 ትናንት በአዳም ኃጢአተኛ፣ ያልተቀደስን፣ ፍጹም ያልሆን፣ ያልዳንን፣ ያልነጻን፣ ከእግዚአብሔር የተለየን፣ የራቅን እና የተረገምን ነበርን። ዛሬ ደግሞ በክርስቶስ የዳንና የጸደቅን አዲስ ፍጥረት ነን። ለዘላለም ይቅር ከተባልንና ከዳንን በኋላ በድጋሚ ይቅር የምንባለው ኃጢአት የለም። ኃጢአትና አመጽ ሁለት ጊዜ ይቅር አይባልም። ስለዚህ በአንድ ጊዜ በአዳምና በክርስቶስ መሆን እንደማይቻል በአንድ ጊዜ አዲስ ፍጥረትና ኃጢአተኛ መሆን አይቻልም።

 ስለ ራሳችን ከሰማናቸው የተሳሳቱ አመለካከቶች አንዱ ሰው ደካማ ነው፣ ይህን ማድረግ፣ እንደዚህ መሆን አይችልም. . . የሚል ነው። እኔ ደግሞ ዛሬ ስለ እውነተኛ ማንነትህ ትክክለኛውን እውቀ...
23/04/2024


ስለ ራሳችን ከሰማናቸው የተሳሳቱ አመለካከቶች አንዱ ሰው ደካማ ነው፣ ይህን ማድረግ፣ እንደዚህ መሆን አይችልም. . . የሚል ነው። እኔ ደግሞ ዛሬ ስለ እውነተኛ ማንነትህ ትክክለኛውን እውቀት እነግርሃለሁ። እግዚአብሔር ሁሉን እንድትችል እንጂ የሆነ ነገር እንድትችል የሆነ ነገር ደግሞ እንዳትችል አድርጎ አልፈጠረህም። ብርቱና ጠንካራ እንጂ ደካማ አድርጎ አልፈጠረህም። የሰው አላዋቂ እንጂ ደካማ የለም። ባላወቅህበት ነገር እስክታውቅ ድረስ እንደ ደካማ ልትቆጠር ትችላለህ። ይህ ማለት ግን ለመስተካከል የሚከብድ ከአቅም በላይ የሆነ ብልሽት አጋጥሞሃል ማለት አይደለም። ለሌሎች ደካማ ሆነህ የታየህበትን ጉዳይ ማሸነፍ ትችላለህ። እንዴት ካልከኝ መልሱ ቀላል ነው። ደካማ ባስባሉህ ነገሮች ላይ ብቻ ማተኮርህን ተው። አቅምና ብርታትህን ገድቦ የያዘውን የተሳሳተ እውቀት ለውጥ። ያን ጊዜ ወደ ታላቅነት መንበር መመለስ ትችላለህ። በሙሉ አቅምህ ነገሮችን ማስኬድ ያልቻልከው ተረግመህ ወይም የአርባ ቀን እድል ሳይሆን አለማወቅ ነው። የሰው አላዋቂ እንጂ ደካማ የለውምና ስለ ማንነትህ ማመን፣ ማወቅ፣ ማሰብ የሚገባህን ብታውቅ ብርቱ ከምትላቸው ሰዎች የሚለይህ አንዳች ነገር የለም። የማንነትህን የመጨረሻ አቅም ሰብሰብ አድርገህ መጠቀም ከቻልክ አሁን ያለውን ብቻ ሳይሆን ወደፊት የሚመጣውንም ችግር መዋጥና ማስቀረት ትችላለህ።

Address

Nazareth, Shewa
Nazareth
2695

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when The Firstborn Assembly Church posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to The Firstborn Assembly Church:

Share