ማህበረ ናታኒም በኩየራ ደ/ኃ/ቅ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን

  • Home
  • Ethiopia
  • Kuyera
  • ማህበረ ናታኒም በኩየራ ደ/ኃ/ቅ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን

ማህበረ ናታኒም በኩየራ ደ/ኃ/ቅ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ማህበረ ናታኒም በኩየራ ደ/ኃ/ቅ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን, Religious organisation, Kuyera.

06/02/2026

ጥር 27 የማንዘነጋው የማንረሳው ቀን

  በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ታላቅ አባት የሆኑት እና በቤተክርስቲያኗ የገዳማት መምሪያ የበላይ ኃላፊ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዕንባቆም ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ። የቅዱስ ሲ...
26/01/2026



በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ታላቅ አባት የሆኑት እና በቤተክርስቲያኗ የገዳማት መምሪያ የበላይ ኃላፊ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዕንባቆም ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ። የቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤት ዛሬ እንዳስታወቀው፣ የብፁዕነታቸው ሥርዓተ ቀብር ነገ ጥር 19 ቀን 2018 ዓ.ም በተማሩበት፣ በመነኮሱበትና ለረጅም ዓመታት ባገለገሉበት በታላቁ ደብረ ሊባኖስ ገዳም ይፈጸማል።

ብፁዕ አቡነ ዕንባቆም በኢትዮጵያ እና በኢየሩሳሌም በሚገኙ የኢትዮጵያ ገዳማት ከፍተኛ መንፈሳዊ አገልግሎት ያበረከቱ ሲሆን፣ በቤተክርስቲያኗ ውስጥ በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች ላይ በመመደብ ተልእኮአቸውን ሲወጡ ቆይተዋል።

ብፁዕ አቡነ ዕንባቆም (በቀድሞ ስማቸው ጸባቴ ተክለ ሐዋርያት ባሳዝነው) የተወለዱት በሰሜን ሸዋ ዞን፣ በደብረ ብርሃን አውራጃ፣ በነዋሪ ወረዳ ልዩ ስሙ ከያዱር በዓለ ወልድ በሚባል አካባቢ ነው። መንፈሳዊ ትምህርታቸውን በደብረ ብሥራት ዜና ማርቆስ ገዳም የጀመሩ ሲሆን፣ በሰቃ መድኃኔ ዓለም ገዳም ከታላቁ ምሁር መምህር አባ ዘካርያስ ኃይለ ማርያም (የአሁኑ ብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ) ዘንድ የቅኔና የትርጓሜ መጻሕፍትን፣ እንዲሁም ሥርዓተ ቅዳሴና ሰዓታትን ተምረዋል።

በደብረ ሊባኖስ ገዳም በመግባት ከየኔታ መርዓዊ ሣህለ ሚካኤል ጾመ ድጓን ከነቃል ትምህርቱ የቀሰሙ ሲሆን፣ መንፈሳዊ እውቀታቸውን ለማስፋት ወደ ጎጃም እና ጎንደር በመሄድ የቅኔ ትምህርታቸውን አጠናክረዋል። በደብረ ሊባኖስ ገዳም የዝማሬ መዋሥዕት ትምህርትን የተከታተሉ ሲሆን፣ በገዳሙ የማኅበር አባልነት በመግባትም በአርድእትነት፣ በቅዳሴ እና በተለያዩ አገልግሎቶች ተሳትፈዋል።

ብፁዕነታቸው በደብረ ሊባኖስ ገዳም በነበራቸው ቆይታ የመጻሕፍተ ሐዲሳትን ትርጓሜ ከመምህር ብርሃኑ ወልደ ሥላሴ እና ከመምህር ገብረ ሕይወት ገብረ ኢየሱስ ተምረው አጠናቀዋል። የምንኩስና፣ የቅስና እና የቁምስና ማዕረግን ከተቀበሉ በኋላ፣ በ1994 ዓ.ም በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ መልካም ፈቃድ የደብረ ሊባኖስ ገዳም አስተዳዳሪ (ጸባቴ) ሆነው ተሾመዋል። በዚህ ኃላፊነት ላይ እያሉ በገዳሙ ውስጥ በርካታ የልማት ስራዎችን አከናውነዋል።

ሐምሌ 9 ቀን 1997 ዓ.ም በተደረገው የጳጳሳት ምርጫ የደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት ጳጳስ ሆነው የተመረጡት ብፁዕ አቡነ ዕንባቆም፣ ቀጥሎም በኢየሩሳሌም የኢትዮጵያ ገዳማት ሊቀ ጳጳስ በመሆን አገልግለዋል። ህይወታቸው እስካለፈበት ጊዜ ድረስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የገዳማት መምሪያ የበላይ ኃላፊ ሆነው በማገልገል ላይ ነበሩ።

የብፁዕነታቸው ህልፈት ለቤተክርስቲያኗ እና ለምእመናን ታላቅ ኀዘን መሆኑ ተገልጿል። ሥርዓተ ቀብራቸው ነገ በደብረ ሊባኖስ ገዳም በታላቅ ክብር ይፈጸማል።

የቅዱስ ገብርኤል ወዳጆች በያለንበት ከክፉ ነገር ከድንገተኛ አደጋ ወጥቶ ከመቅረት ይሰውራችሁ ይሰውረን የልባችንን መሻት ይሙላልን በያለንበት ጥበቃው አይለየን አይለያችሁ አሜን!!!የተወደዳችሁ...
09/01/2026

የቅዱስ ገብርኤል ወዳጆች በያለንበት ከክፉ ነገር ከድንገተኛ አደጋ ወጥቶ ከመቅረት ይሰውራችሁ ይሰውረን የልባችንን መሻት ይሙላልን በያለንበት ጥበቃው አይለየን አይለያችሁ አሜን!!!

የተወደዳችሁ ከየትኛውም ዓለም የምትገኙ የቅዱስ ገብርኤል ወዳጆች የ2018 ዓ.ም ጥምቀት በዓል እጅግ በደመቀ ሁኔታ ከመቼውም ጊዜ በላይ በተሻለና በሚያስደስት መልኩ ለማክበር ከታህሳስ መጀመሪያ ጀምሮ እንቅስቃሴ ላይ መሆናችን ይታወቃል፡፡

ሆኖም በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ የምተገኙ ውድ የአካባቢው ተወላጆች ከዚህ በፊት ላለፉት ዓመታት በአካባቢው በሚገኙ በጎ አድራጊዎች ድጋፍ የጥምቀት ማውረጃ ቀይ ምንጣፍ፣ሰረገላና ሌሎች ለበዓሉ ድምቀት የሚሆኑ ቁሳቁሶችን በመግዛት በተሻለ አስተምህሮ ስናከብር መቆየታችን ይታወቃል።

ስለሆነም ከዚህ ቀደም ስንጠቀምባቸው የነበሩት ቁሳቁሶች ከጊዜ እርዝማኔ የተነሳ አገልግሎት መስጠት ስላቆሙ አዲስ ግዥ እንዲደረግ ተገደናል።

በመጨረሻም ለዚህ ለተቀደሰ ተግባር ማለትም
👉 ለቀይ ምንጣፍ መግዣ
👉ለማጥመቂያነት የሚያገለግል ወተር ፓምፕ እና ለሌሎች ጥቃቅን ቁሶች መግዣ የሚሆን የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ የበረከቱ ተሳታፊ ትሆኑ ዘንድ ባላችሁበት ተጋብዛችኋል።

ለተጨማሪ መረጃ👇👇👇
0916517638
0923890328
0922243759

👉በተጨማሪም በውስጥ መስመር ይፃፉልን።
በምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት በሻሸመኔ ወረዳ ዳግማዊ ቁልቢ የኩየራ ደ/ሀ/ቅ/ገ/ቤ/ን ህዝብ ግኑኝነት
የኩየራ ፈልቻ ደብር ገነት ቅድሰት ማርያም ቤተክርሰቲያን ሰንበት ት/ ቤት
ZeBete Michael

የአእላፋት ዝማሬ ወደ የአእላፋት ቅዳሴ ሊያድግ ነው:: ጃንደረባው ሚድያ | ታኅሣሥ 2018 ዓ.ም. አዲስ አበባ ኢትዮጵያ* የአእላፋት ዝማሬ በዋዜማው ዋዜማ እንዲካሔድ ተወስኖአል* የአእላፋት...
07/01/2026

የአእላፋት ዝማሬ ወደ የአእላፋት ቅዳሴ ሊያድግ ነው::

ጃንደረባው ሚድያ | ታኅሣሥ 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

* የአእላፋት ዝማሬ በዋዜማው ዋዜማ እንዲካሔድ ተወስኖአል
* የአእላፋት ዝማሬ ቀን የአእላፋት ቅዳሴ ቀን ይሆናል::
* የቅዳሴ ተሰጥዎ ትምህርት ዐቢይ ጾም ላይ ይጀምራል

3ኛው የአእላፋት ዝማሬ በመስቀል አደባባይ በተሳካ ሁኔታ ተካሔደ:: የጠቅላይ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅና የሸገር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የማኅበራት ምዝገባና ክትትል መምሪያና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ ፣ የአዲስ አበባ የሐዲያና ሥልጤ አህጉረ ስብከቶች ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ በተገኙበት በዚህ ዝማሬ ላይ የየመምሪያው ኃላፊዎች ፣ የጉባኤ መምህራን ፣ ሰባኪያንና ዘማርያን እንዲሁም በመቶ ሺህዎች የሚቆጠሩ ምእመናን ታድመዋል::

የአእላፋት ዝማሬው በጃን እስጢፋኖስ በመሐረነ አብ ጸሎት የተጀመረ ሲሆን ጸሎተ ወንጌል ደርሶ የዕለቱ ወንጌል በብፁዕ ሥራ አስኪያጁ ተነብቦ የሰርክ ኪዳን ደርሶአል:: በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቴሌቪዥን ዋና ሥራ አስኪያጅ ቀሲስ ዶ/ር አካለ ወልድ ተሰማ የተመራው ጉባኤው በብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ ቃለ ምዕዳን ተከፍቶአል::

ብፁዕነታቸው በመልእክታቸው "ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ከጥንት ጀምሮ በቅዱስ ያሬድ ዜማ በሊቃውንት ድርሰት በዓለ ልደትን ከዋዜማው በመነሣት ሌሊቱን በቅኔ ማኅሌትና በሥርዓተ ቅዳሴ ሐዋርያዊ ትውፊትን ጠብቃ በዝማሬ ስታከብር ኖራለች ዛሬም እያከበረች ትገኛለች፡፡ ይኽንኑ ፍጹም መንፈሳዊ የሆነ የተቀደሰ ትውፊት መሠረት በማድረግ፣ በጌታችን ልደት በዓልምእመናን በተለይም ወጣቶች ከመንፈሳዊ ሥርዓት ውጭ በአልባሌ ቦታዎች ቀኑንና ሌሊቱን እንዳያሳልፉ፣ መዝሙራትን አጥንተው፣ ከዋክብት ብሩሃንን ሆነው የጌታችንን ልደት በምስጋና ለመቀበል መሰባሰባቸው የሚያስመሰግንና በረከትን የሚያሰጥ የተቀደሰ ተግባር ነው" ብለዋል::

የአእላፋት ዝማሬ መድረክ በጥንታዊው የክብ ቤተ ክርስቲያን ቅርፅ የተሠራ ሲሆን በደመራ ቦታው ላይ ደግሞ የቤተልሔም ግርግምን የልደት የብራና ሥዕል በማድረግ ምእመናን ወደ ተወለደበት ሥፍራ ሕሊናቸውን እንዲመልሱ የሚያደርግ ሆኖአል::

ሦስተኛው የአእላፋት ዝማሬ በብፁዕ ሥራ አስኪያጁ አብሣሪነት በይፋ የተከፈተ ሲሆን በጃን እስጢፋኖስ ዲያቆናት ወረብ ተከፍቶ ዐሥራ አምስት መዝሙራት ተዘምረዋል:: በሁለተኛ ዙር ከዲያቆናት "መድኃኒነ ተወልደ ነዋ" የሚል ወረብ በማስከተል ዐሥራ አምስት መዝሙራት ተዘምረው በበኩረ መዘምራን ኪነ ጥበብ ወልደ ቂርቆስ "እንደ ቸርነትህ" ጸሎት ተደርጎ በሰላም ተጠናቅቆአል:: የአእላፋት ዝማሬው ላይ የታደሙት ምእመናን ቁጥራቸው ከተጠበቀው በላይ ቢሆንም የጸጥታ አካላትን ባስደነቀ ፍጹም ሰላማዊ መንፈስና በእርጋታ ወደየ በአታቸው ሔደዋል:: በዕለቱ የታደሙ ምእመናን የጧፍ መባቸውን ለታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም ገዳም ሠጥተዋል::

የኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ ዘንድሮ በመስቀል አደባባይ ያካሔደውን የአእላፋት ዝማሬ በድኅረ ሁነት ውይይቱ በጥንቃቄ የገመገመ ሲሆን እግዚአብሔር ቢፈቅድ የአእላፋት ዝማሬን ወደ አእላፋት ማሕሌትና የአእላፋት ቅዳሴ ለማሳደግ ሲያወርግ የነበረውን ጥረት በ2019 ዓ.ም. የአእላፋት ዝማሬ ላይ ዕውን ለማድረግ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንንና ብፁዓን አባቶችን በማማከር ድምዳሜ ላይ ደርሶአል::

የአእላፋት ዝማሬ በመስቀል አደባባይ ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደ መካሔዱ የታየው አዲስ ነገር የአደባባዩ ጠባይ ፣ የተሳታፊው ብዛት ፣ ሰልፍና ፍተሻው የሚወስደው ታሳቢ ሆኖ ጸሎትና ዝማሬው ብቻ አምስት ሰዓታትን የሚወስድ መሆኑ ፣ ሕዝቡ ከአደባባዩ ለመውጣት የሚፈጅበት ጊዜ ከአክፍሎትና ወደየአጥቢያው ለመድረስ ከሚደረግ ጉዞ ጋር አዳጋች እንደሚሆን ተስተውሎአል::

በዚህ ምክንያት ፈቃደ እግዚአብሔር ቢሆን ከቀጣይ ዓመት ጀምሮ የአእላፋት ዝማሬ አንድ ቀን ቀድሞ በዋዜማው ዋዜማ እንዲደረግና በዋዜማው ዕለት ደግሞ የአእላፋት ቅዳሴ ዘመቻ እንዲጀመር ተወስኖአል:: ይህ መደረጉም ማሕሌት የሚቆሙ ምእመናን ከአእላፋት ማግሥት ዕረፍት አድርገው እንዲቆሙ ፣ ወደ ቅዱስ ላሊበላና ወደ ሌሎች ቅዱሳት መካናት ጉዞ የሚያደርጉም ተሳትፈው በማግሥቱ በረራዎች እንዲሔዱ እንዲሁም ልደትን በቅዳሴ አሳልፈው የማያውቁም በዋዜማው ዝማሬ መንፈሳቸው ለቅዳሴ እንዲዘጋጅ ያበረታታል::

የኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ ጃን ቅዳሴ በተሰኘው ፕሮጀክቱ አማካኝነት ቅዳሴ ለማስተማር ትምህርታዊ ቪድዮ ከመማሪያ ሞጁል ጋር ዝግጅቱን ያጠናቀቀ ሲሆን የአእላፋት ሳምንት ዐውደ ርእይ ላይ በ3D Model የቅዳሴ ትዕይንት ለብዙኃን ማስጎብኘቱም ይታወቃል:: ከመጪው ዐቢይ ጾም ጀምሮ ይህንን የቅዳሴ ተሰጥኦ ትምህርት ለምእመናን በይፋ የሚጀምር ሲሆን በ2019 ዓ.ም. በአእላፋት ዝማሬ ላይ የታደመውን ሕዝብ ያህል በየአጥቢያው በቅዳሴ ላይ ተገኝቶ የዝማሬውን ድምፅ በተሰጥዎ ድምፅ እንዲደግም ለማድረግ ዕቅድ ተይዞአል:: ጃን ቅዳሴ ከ፳፬ቱ የኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ ፕሮጀክቶች አንዱ ሲሆን እስከ አሁን ድረስ ሦስት ዙር የቅዳሴ ተሰጥዎ ተማሪዎችን አስተምሮ አስመርቆአል:: በተቋማት ደረጃ የቅዳሴ ተሰጥዎ ለመማር ጥያቄ ላቀረቡ የሙያ ማኅበራትም እንዲሁ ከሥራ ሰዓታቸው ጋር የተስማማ የመማሪያ መርሐ ግብር ነድፎ በማስተማር ላይ እንደሚገኝ የጃን ቅዳሴ ሰብሳቢ ዲያቆን ኃይለ ኢየሱስ ተሻለ ገልጸዋል::

በመስቀል አደባባይ የተካሔደውን ሦስተኛውን የአእላፋት ዝማሬ ከቀደሙት ሁለት የአእላፋት ዝማሬዎች እጅግ የሚበልጥ ቁጥር ያላቸው ምእመናን የታደሙበት ሲሆን በኦንላይን ደግሞ ሚልዮኖች ተመልክተውታል:: የEOTC TV ፣ ሀገሬ ቲቪ ፣ አርትስ ቲቪ ፣ ቃና ቲቪ ፣ ፋና ቲቪ ፣ ኢቢሲ ፣ አሶሽየትድ ፕሬስ ፣ BBC ፣ ሮይተርስ ፣ ዶቼቬሌ ፣ ቪዮሪ ቲቪ ፣ ስፖትኔክ ሬድዮ ለሦስተኛው የአእላፋት ዝማሬ ሽፋን የሠጡ ሚድያዎች ናቸው::



አዲስ አበባ መስቀል አደባባይ!...የአእላፋት ዝማሬ
06/01/2026

አዲስ አበባ መስቀል አደባባይ!...
የአእላፋት ዝማሬ

''የቅድስት ኪዳነ ምህረት ድንቅ ተአምራዊ ምስል መታየቱ ተሰማ'' በፈረንጆቹ አድስ አመት አድስ ነገር '' በቆላድባ ከተማ የታየው አስደናቂ ተአምር!ምስራቅ ደንቢያ በዛሬው ዕለት በምስራቅ ደ...
02/01/2026

''የቅድስት ኪዳነ ምህረት ድንቅ ተአምራዊ ምስል መታየቱ ተሰማ'' በፈረንጆቹ አድስ አመት አድስ ነገር '' በቆላድባ ከተማ የታየው አስደናቂ ተአምር!

ምስራቅ ደንቢያ በዛሬው ዕለት በምስራቅ ደንቢያ ወረዳ ቆላድባ ከተማ የከተማው እንብርት" ተብሎ በሚጠራው አካባቢ፣ በአንድ ግዙፍ ዋርካ ዛፍ ላይ የቅድስት ኪዳነ ምህረት ድንቅ ተአምራዊ ምስል መታየቱ ተሰማ።

ክስተቱን ለየት የሚያደርገውና የብዙዎችን ትኩረት የሳበው ቀደም ብሎ የነበረው ሁኔታ ነው። በከተማው እየተከናወነ ባለው የኮሪደር ልማት ምክንያት፣ በአስፓልቱ ዳር የሚገኘው ይህ ዋርካ እንዲቆረጥ ታቅዶ ነበር።

ሆኖም ግን በቀን ስራው ተጀምሮ ዋርካውን ለመቁረጥ ሙከራ ቢደረግም፣ ለመቁረጫነት የሚያገለግሉ ቁሳቁሶች በተደጋጋሚ እየተሰበሩ ስራውን ማከናወን አልተቻለም።

ሰራተኞቹ "ነገሩ አልሆን አለ" በማለት ትተውት በሄዱበት ጥቂት ሰዓታት ሳይሞላ፣ አመሻሽ ላይ በዋርካው አካል ላይ የኪዳነ ምህረት ድንቅ ምስል ተገልጦ ታይቷል።

በአሁኑ ሰዓት የከተማው ህዝብና ከአካባቢው የመጡ ምዕመናን በቦታው ተገኝተው ይህንን ድንቅ ተአምር እየተመለከቱ ይገኛሉ። ይህ የእግዚአብሔር ስራ እንጂ የሰው አይደለም" በሚል ምስክርነታቸውን እየሰጡ ነው።

ዛፉ ሊቆረጥ ሲል መሳሪያው አልሰራ ማለቱ የነገሩን ድንቅነት ያሳያል፤ አሁን ደግሞ ይኸው እናታችን ተገለጠች" የሚሉ የቆላድባ ከተማ ነዋሪዎች በርክተዋል::

ይህንን ድንቅ ምስክርነት ለወዳጅ ዘመድዎ በማጋራት የአለም ህዝብ እንዲሰማው ያድርጉ!

አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በፃድቁ ስም ለምናመሰግንበት ለኢትዮያዊው ፃዲቅ አቡነ ተክለሀይማኖት የልደት በዓል እንኳን አደረሳችሁ።ጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት በሊቀ መ...
02/01/2026

አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በፃድቁ ስም ለምናመሰግንበት ለኢትዮያዊው ፃዲቅ አቡነ ተክለሀይማኖት የልደት በዓል እንኳን አደረሳችሁ።

ጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት በሊቀ መላእክት በቅዱስ ሚካኤል አብሳሪነት ከአባታቸው ከካህኑ ጸጋ ዘአብና ከእናታቸው ከቅድስት እግዚእ ኀረያ መጋቢት 24 ቀን ተፀንሰው ታኅሣሥ 24 ቀን 1197 ዓ.ም ተወለዱ፡፡ ጻድቁ በተወለዱ በሦስተኛው ቀን ከእናታቸው ዕቅፍ ወርደው ‹‹አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ›› ማለትም ‹‹አንዱ አብ ቅዱስ ነው አንዱ ወልድ ቅዱስ ነው አንዱ መንፈስ ቅዱስ ቅዱስ ነው›› በማለት የፈጠራቸውን አምላክ አመስግነውታል፡፡
ሰላም ለልደትከ ተክለ ሃይማኖት ሐዋርያ፤
ለሰብአ ግብጽ ወኢትዮጵያ፤
ሞገሰ ልደትከ አባ አዕይንቲሃ ርእያ፤
ነፍስየ ትባርኮሙ ወታስተበጽኦሙ ነያ፤
ለጸጋ ዘአብ ወለእግዚእ ኃረያ ፡፡

አባታችን ፃዲቁ አቡነ_ተክለሀይማኖት በዳዊት ፀሎት ከነቢያት ምስጋና ሌሊቱን ሙሉ ይተጉ ነበር በያንዳንዱ መዝሙርም አስር 10 ስግደትን ይሰግዱ ነበር፡፡

በሕዳር 24 ቀን ቅዱስ_ሚካኤል ወደ ላይ ነጠቃቸው አወጣቸው ከሐያ_አራቱ_ካህናተ_ሰማይ ጋር ሐያ አምስተኛ ካህን ሆነው የሥላሴን መንበርን አሐዱ_አብ_ቅዱስ አሐዱ_ወልድ_ቅዱስ አሐዱ_ውእቱ_መንፈስ_ቅዱስ በማለት አጥነዋል

በሐይቅ 10 ዓመት በደብረ ዳሞ 12 ዓመት ኖረዋል አባታችን አቡነ_ተክለሃይማኖት በ1267 ዓ.ም ደብረ ሊባኖስን በአት አድርገው ኖሩ፡፡

ለ22 ዓመት ቆመው በመፀለያቸዉ የአንድ እግራቸው አገዳ ተሠበረ ደቀ መዝሙሮቻቸው በጨርቅ ጠቅልለው ቀበሩት፡፡

በአንድ እግራቸው ለ7 ዓመት በፀሎት ቆሙ በጠቅላላው ለ29 ዓመት በፀሎት ከቆሙ በኋላ በ99 ዓመት ከ10 ወር ከ10 ቀን ነሐሴ 24 ቀን አረፉ አባታችን ባረፉ በ54 ዓመታቸው ለአባታችን ለአቡነ ሕዝቅያስ ተገልፀው አፅማቸው ከደብረ_አስቦ ወደ ደብረ_ሊባኖስ ግንቦት 12 ቀን እንዲፈልስ አድርገዋል፡፡

ለሃይማኖታችን መፅኛ ለሀገራችን አፅር ቅፅር የአባታችን ፀሎት ኃይል ይሁነን ቃል ኪዳኑ ይጠብቀን "አሜን"

አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ_ክርስቶስ እንኳን በሰላም በያላችሁበት ቦታ ለታላቁ አባታችን ለአቡነ ተክለ ሐይማኖት ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ አደረስን ከሃያ አራቱ ካህናተ ስማይ ጋር አባታችን
የሥላሴን_መንበር ያጠኑበት ያመስገኑበት ቀን የበረከትና የረድኤት ቀን ይሁንልን❤
የፃዲቁ በረከት ረድኤት አይለየን አሜን፤፤

ጎንደር በቆላድባ የታየው ተአምር ቀጥሏል — ፀበል ፈለቀ! "የእግዚአብሔር ድንቅ ስራ በቆላድባ ከተማ ተገለጠ!"ትላንት ማታ በጎንደር በምስራቅ ደንቢያ ወረዳ ቆላድባ ከተማ በዋርካው ላይ የታየ...
02/01/2026

ጎንደር በቆላድባ የታየው ተአምር ቀጥሏል — ፀበል ፈለቀ!

"የእግዚአብሔር ድንቅ ስራ በቆላድባ ከተማ ተገለጠ!"

ትላንት ማታ በጎንደር በምስራቅ ደንቢያ ወረዳ ቆላድባ ከተማ በዋርካው ላይ የታየው የቅድስት ኪዳነ ምህረት ተአምራዊ ምስል መላውን ዓለም ሲያስደንቅ መቆየቱ ይታወሳል። አሁን ደግሞ ሌላ እጅግ የሚያስገርም ተጨማሪ ተአምር ተከስቷል!

የእናታችን የኪዳነ ምህረት ምስል በታየበት በዚያው ስፍራ፣ በአሁኑ ሰዓት አስደናቂ ፀበል ፈንድቶ ወጥቷል! * ህዝቡ እየተፈወሰ ነው፦ በቦታው የሚገኘው ህዝብ በፀበሉ እየተጠመቀ ይገኛል፤ እግዚአብሔር በቸርነቱ ድውያንን እየፈወሰ፣ የታመሙትን እየዳሰሰ መሆኑ እየተነገረ ነው።

* በስፍራው ያለው ምዕመን በደስታ እልልታና በምስጋና ድምፅ አካባቢውን ሞልቶታል። "ዛፉን እንዳይቆረጥ መሳሪያ የሰበረች እናታችን፣ ዛሬ ደግሞ ለልጆቿ ፈውስን አፈለቀች" በማለት ህዝቡ ምስክርነቱን እየሰጠ ነው።

* በዋርካው ላይ የቅድስት ኪዳነ ምህረት ምስል በግልጽ ታየ።
* ዛሬ ደግሞ ለብዙዎች መዳኛ የሚሆን ፀበል ፈንድቶ ወጣ!
እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ላይ ድንቅ ነው! ቸርነቱና ምህረቱ ለሁላችንም ይሁን።

ይህንን የእግዚአብሔርን ስራ ለዓለም ሁሉ እንዲደርስ በማድረግ ምስክር ይሁኑ!

Address

Kuyera

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ማህበረ ናታኒም በኩየራ ደ/ኃ/ቅ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share