13/04/2026
32 _ የአገልግሎት አመታት
የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ገ/ሰንበት ት/ቤት በየዓመቱ በልደትና በትንሳኤ ነዳያንን ጾም እያስፈሰከ ቆይቶል::
ከዚህ በተጨማሪ ህመም የሚያጋጥማቸውንና ልዩ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸውን ነዳያን በማሳከምና ድጋፍ በማድረግ ላይ ይገኛል::
የ2018 ዓ.ም የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ነዳያንን ለማስፈሰክ ሰፊ ቅድመ ዝግጅት ሲያደርግ ቆይቶል::
የእግዚአብሔር ፈቃድ ሆኖ በዛሬው ዕለትም ከ1000 በላይ ነዳያንን ጾም አስፈስከናል
በአገልግሎቱ በርካታ አባላት ተሳትፈዋል
ለዚህ ትልቅ አገልግሎት በገንዘብ ,በጉልበት, በአይነት ለተራዱት ሁሉ በእግዚአብሔር ስም እናመሰግናለን::
የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ገዳም ሰንበት ት/ቤት