የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ገዳም ሰንበት ት/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Kolfe
  • የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ገዳም ሰንበት ት/ቤት

የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ገዳም ሰንበት ት/ቤት egziabher hayal new

32 _ የአገልግሎት አመታትየሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ገ/ሰንበት ት/ቤት በየዓመቱ በልደትና በትንሳኤ ነዳያንን ጾም እያስፈሰከ ቆይቶል::ከዚህ በተጨማሪ ህመም የሚያጋጥማቸውንና ልዩ ድጋፍ...
13/04/2026

32 _ የአገልግሎት አመታት

የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ገ/ሰንበት ት/ቤት በየዓመቱ በልደትና በትንሳኤ ነዳያንን ጾም እያስፈሰከ ቆይቶል::

ከዚህ በተጨማሪ ህመም የሚያጋጥማቸውንና ልዩ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸውን ነዳያን በማሳከምና ድጋፍ በማድረግ ላይ ይገኛል::

የ2018 ዓ.ም የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ነዳያንን ለማስፈሰክ ሰፊ ቅድመ ዝግጅት ሲያደርግ ቆይቶል::

የእግዚአብሔር ፈቃድ ሆኖ በዛሬው ዕለትም ከ1000 በላይ ነዳያንን ጾም አስፈስከናል

በአገልግሎቱ በርካታ አባላት ተሳትፈዋል

ለዚህ ትልቅ አገልግሎት በገንዘብ ,በጉልበት, በአይነት ለተራዱት ሁሉ በእግዚአብሔር ስም እናመሰግናለን::

የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ገዳም ሰንበት ት/ቤት

13/04/2026

with CameraFi Live

የሰሙነ ሕማማት ሐሙስ ፩ኛ. ጸሎተ ሐሙስ ይባላል።  ይኸውም:-ኅብስቱን ለውጦ ሥጋ መለኮት፥ወይኑንም ደመ መለኮት ባደረገ ጊዜ ስለ ጸለየ እና እንዲሁም በዮሐንስ ምዕራፍ ፲፯ ላይ ያለውን በመጸ...
09/04/2026

የሰሙነ ሕማማት ሐሙስ

፩ኛ. ጸሎተ ሐሙስ ይባላል።
ይኸውም:-ኅብስቱን ለውጦ ሥጋ መለኮት፥ወይኑንም ደመ መለኮት ባደረገ ጊዜ ስለ ጸለየ እና እንዲሁም በዮሐንስ ምዕራፍ ፲፯ ላይ ያለውን በመጸለዩ ነው።

፪ኛ. ትእዛዘ ሐሙስ ይባላል።
ይኸውም:-የደቀ መዛሙርቱን እግሮች ካጠበ በኋላ “እናንተም እንዲሁ አድርጉ፤”ብሎ በማዘዙ እና በጌቴሴማኔ ጴጥሮ ስን፥ዮሐንሰን፥ያዕቆብን “ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ፤”የሚል ትእዛዝ ስለ ሰጣቸው፤ እንዲሁም:-ሥርዓተ ቁርባንን አሳይቶ “ከመዝ ግበሩ ተዝካርየ፤”ብሎ በማዘዙ ነው።

፫ኛ. የነፃነት ሐሙስ ይባላል።
ይኸውም ጌታ ደቀ መዛሙርቱን:-“ከእንግዲህ ባሮች አለላችሁም፥ወዳጆች ግን ብያችኋለሁ፤”ያለውን በማሰብ ነው።

፬ኛ. ኅፅበተ ሐሙስ ይባላል።
ይኸውም:-በዚህ ዕለት የደቀ መዛሙርቱን እግሮች በማጠቡ ነው።

፭ኛ. አረንጓዴው ሐሙስ ይባላል።
ይኸውም አረንጓዴ በሆነ የአትክልት ሥፍራ መጸለዩን ለማስታወስ ነው።

፮ኛ. የአዲስ ኪዳን ሐሙስ ይባላል።
ይኸውም ጽዋውን አንስቶ “ይህ የአዲስ ኪዳን ደሜ ነው፤”በማ ለቱ ነው።ትርጉሙም ሥጋውና ደሙ የአዲስ ሕግ የወንጌል፥የአዲስ ርስት የመንግሥተ ሰማይ መጥኛ መሆኑን የሚያመለክት ነው።

የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ገዳም ሰንበት ት/ቤት
08/04/2026

የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ገዳም ሰንበት ት/ቤት

ረቡዕ የምክር ቀን ይባላል፡፡ የአይሁድ ሊቃነ ካህናት ጸሐፍት በጌታችን ላይ የሞት ፍርድ ለመወሰን፣ እንዴት እንደሚይዙት ምክር የጀመሩበት ቀን ነው፡፡ በዚህ ዕለት የጌታ ምክረ ሞት ተፈጸመ፡፡...
08/04/2026

ረቡዕ የምክር ቀን ይባላል፡፡ የአይሁድ ሊቃነ ካህናት ጸሐፍት በጌታችን ላይ የሞት ፍርድ ለመወሰን፣ እንዴት እንደሚይዙት ምክር የጀመሩበት ቀን ነው፡፡ በዚህ ዕለት የጌታ ምክረ ሞት ተፈጸመ፡፡ በዚህ ምክራቸው ጭንቀት የፈጠረባቸው ወቅቱ የፋሲካ በዓላቸው የሚከበርበት በመኾኑ ብዙ ሕዝብ በጌታችን ትምህርት የተማረኩ፣ ተአምራቱን የሚያደንቁ ስለነበሩ ሁከት እንዳይፈጠር በመስጋት ነበር፡፡ በዚህ ጭንቀት ላይ ሳሉ ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ የኾነው የአስቆሮቱ ይሁዳ በመካከላቸው ተገኝቶ የምክራቸው ተባባሪ በመሆን ጭንቀታቸውን አስወግዶላቸዋል /ማር.፲፬፥፲/፡፡ ሄዶም ከካህናት አለቆችና ከታላላቆች ጋር እርሱን አሳልፎ እንዲሰጣቸው ተነጋገረ” እንዲል፡፡ /ሉቃ. ፳፪፥፩/፡፡ በዚህም መሠረት ይህቺ ዕለት የአይሁድ ሊቃነ ካህናትና ጸሐፍት ፈሪሳውያን ጌታ ኢየሱስን እንዴት መያዝ እንዳለባቸው ምክር የመከሩበት፣ ምክራቸውንም ያጸኑበትና ሰቅለው ይገድሉት ዘንድ የወሰኑበት ቀን በመሆኑ የአይሁድ የምክር ቀን ተብላ ትጠራለች፡፡
የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ገዳም ሰንበት ት/ቤት

ሦስተኛይቱ ዕለት በግእዝ ሠሉስ ትባላለች፡፡ዕለተ ሠሉስ ማለትም ሦስተኛ ማለት ነው፡፡ ሦስተኛ መባሏም እግዚአብሔር ፍጥረት መፍጠር ከጀመረባት ከዕለተ እሑድ ጀምሮ ስለሚቆጠር ነው፡፡ ይህች ዕለ...
08/04/2026

ሦስተኛይቱ ዕለት በግእዝ ሠሉስ ትባላለች፡፡ዕለተ ሠሉስ ማለትም ሦስተኛ ማለት ነው፡፡ ሦስተኛ መባሏም እግዚአብሔር ፍጥረት መፍጠር ከጀመረባት ከዕለተ እሑድ ጀምሮ ስለሚቆጠር ነው፡፡ ይህች ዕለት በአማርኛ የሰኞ ማግስት እንደ ማለት ነው፡፡ እንደ ባሕረ ሐሳብ መምህራን ማክሰኞ ጥንተ ቀመር ነው፡፡ ይህች ዕለት በቤተክርስቲያን ምስጢራው ስያሜዎች አሏት፡፡ ይህ ዕለት ጌታችን ሰኞ በተናገረውና ባደረገው ተአምር ላይ አይሁድ ጥያቄ ያቀረቡበት እርሱም መልስ በመስጠት ያስተማረበት ቀን ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ‹‹የጥያቄ እና የትምህርት ቀን›› በመባል ይታወቃል፡፡
የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ገዳም ሰንበት ት/ቤት

ሰኞ - መርገመ በለስ                        መ/ር ጌታቸው በቀለሁለተኛይቱ ዕለት በግእዝ ሰኑይ(ሠኑይ) ስትባል በአማርኛ ደግሞ ሰኞ ትባላለች፡፡ ሰኑይ ሁለተኛ ዕለት ማለት ነው፡...
08/04/2026

ሰኞ - መርገመ በለስ
መ/ር ጌታቸው በቀለ

ሁለተኛይቱ ዕለት በግእዝ ሰኑይ(ሠኑይ) ስትባል በአማርኛ ደግሞ ሰኞ ትባላለች፡፡ ሰኑይ ሁለተኛ ዕለት ማለት ነው፡፡ “ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ከሁለት ቀናትም በኋላ ከዚያ ወጥቶ ወደ ገሊላ ሔደ” እንዲል /ዮሐ.፬፥፵፫/፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ሠኑይ ሰነየ-አማረ ከሚለው ግሥ የወጣ ሲኾን፤ ሠኑይ ማለት ያማረ ማለት ነው፡፡ ይኽም “እግዚአብሔር የሠራውን ፍጥረት ሁሉ ያማረ እንደ ኾነ አየ” እንዲል፤ ዕለቲቱ ለፍጥረታት ሁለተኛ ቀን ስለኾነች ዕለተ ሰኑይ ስትባል የተፈጠረባትን ፍጥረት መልካምነት ለመግለጥ ደግሞ ዕለተ ሠኑይ ተብላለች /ዘፍ.፩፥፳፩/፡፡
የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ገዳም ሰንበት ት/ቤት

የሰንበት ት/ቤታችን የጎልማሶች ጉባኤ አባል የሆነችው ወ/ሮ ወይንሸት ዓለሙ ከዚህ አለም ድካም አርፋለችእህታችን በሰንበት ት/ቤታችን በአመራርነት በልዩ ልዩ ንዑሳን ክፍላት ያገለገለች እና በ...
07/04/2026

የሰንበት ት/ቤታችን የጎልማሶች ጉባኤ አባል የሆነችው ወ/ሮ ወይንሸት ዓለሙ ከዚህ አለም ድካም አርፋለች

እህታችን በሰንበት ት/ቤታችን በአመራርነት በልዩ ልዩ ንዑሳን ክፍላት ያገለገለች እና በገዳማችን የሰበካ ጉባኤ አስተዳደር ፅ/ቤት በእስታትስቲክ ክፍል ለረጅም አመታትም በቅንነት አገልግላለች

የቀብር ስነ-ስርዓት ዛሬ ማክሰኞ 29/07/2018 ዓ.ም ከቀኑ በ 8:00 ሰዓት በብርሃናተ ዓለም ጴጥሮስ ወጳውሎስ ይፈፀማል

መኖሪያ አድራሻ ዊንጌት አደባባይ ጊዮን በረኪና አካባቢ ነው

የሰ/ብ/ቅ/ጳ/ገ/ሰ/ት/ቤት በእህታችን ህልፈት የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን እየገለጽን አምላከ ቅዱሳን እግዚአብሔር ነፍሷን ከአብርሃም ከይስሐቅ ከያዕቆብ አጠገብ ያሳርፍልን ለቤተሰቦችዋ እና ወዳጅ ዘመዶችዋ መጽናናትን እንመኛልን::

እንኳን ለሆሳዕና በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን 🌿 ሆሳዕና በአርያም🌿"ሆሳዕና" ማለት "አሁን አድን" ማለት ነው። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በትሕትና በአህያ ውርንጭላ ላይ ተ...
05/04/2026

እንኳን ለሆሳዕና በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን

🌿 ሆሳዕና በአርያም🌿

"ሆሳዕና" ማለት "አሁን አድን" ማለት ነው። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በትሕትና በአህያ ውርንጭላ ላይ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ፣ በውስጡ ሦስት ታላላቅ ምስጢራትን ይዞልን መጥቷል፦

፩. የትሕትና መገለጫ
ኪሩቤልና ሱራፌል በግርማ የሚሸከሙት የሰማይና የምድር ንጉሥ፤ ዛሬ ግን በደካማዋ አህያ ውርንጭላ ላይ ተቀመጠ። ይህ ጌታ የእኛን እንስሳዊ ባሕርይ በቅድስናው ሊገራልንና በትሕትናው ሊያክመን መምጣቱን የሚያሳይ የምስጢር ምስጢር ነው።

፪. የሕፃናት ምስጋና
"ከሕፃናትና ከሚጠቡት አፍ ምስጋናን አዘጋጀህ" (መዝ. ፰:፪)። ሊቃውንትና ፈሪሳውያን በክፋት ሲመለከቱት፣ ሕፃናት ግን በንጹሕ ልባቸው አምላክነቱን መሰከሩ። ይህ ምስጢር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ለመግባት እንደ ሕፃናት መሆን (ንጽሕናንና ቅንነትን መያዝ) እንደሚገባ ያስተምረናል።

፫. የዘንባባው ድል
ሕዝቡ የያዙት ዘንባባ ደርቆ የማይጠወልግ (የዘላለም ሕይወት) እና እሾህ የሌለው (የሰላም) ምልክት ነው። ጌታ ሞትን ድል ሊያደርግ ሲመጣ፣ እኛም በልባችን የክፋትንና የጥላቻን ግድግዳ አፍርሰን፣ ሰላሙን እንደ ዘንባባ በልባችን እንያዝ።

🌿 እንኳን ለሆሳዕና በዓል በሰላም አደረሳችሁ! 🌿
የሰላም ንጉሥ ክርስቶስ በልባችን ይንገሥ!

የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ገዳም ሰንበት ት/ቤት

የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ገዳም ሰንበት ት/ቤት
04/04/2026

የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ገዳም ሰንበት ት/ቤት

        በቅድሚያ እንኳን ለሆሳዕና በዓል በሰላም አደረሳችሁ ውድ ክርቲያኖች እየሰራን ያለነው ስራ ሁለተኛውን ምዕራም ተጋምሷል ሆኖም 👉ለኮርኒስ እና ለግርግዳ 4 በ 5 የሆነ ሞራሌ👉ብዛት...
04/04/2026


በቅድሚያ እንኳን ለሆሳዕና በዓል በሰላም አደረሳችሁ ውድ ክርቲያኖች እየሰራን ያለነው ስራ ሁለተኛውን ምዕራም ተጋምሷል ሆኖም
👉ለኮርኒስ እና ለግርግዳ 4 በ 5 የሆነ ሞራሌ
👉ብዛት 500 ፍሬ የአንዱ ዋጋ 400 ብር ነው
ሁሌም እንደምንለው 50 🍋ሎሚ ለአንድ ሰው ሸክም ነው ለ50 ሰው ጌጡ ነው በእግዚአብሔር ቸርነት እና ፈቃድ በእናንተው ድጋፍ ትብብርና ፀሎት እዚህ ደርሷል አሁን የኮርኒሱን ስራ እንዳይቋረጥ ድጋፋችሁን አድርጉልን በአስቸኳይ ሞራሌውንን እንድንሽፍን የድራሻችንን እንወጣ መልካም የሆሳዕና በዓል
"የአቅሜን ለሰንበት ትምህርት ቤቴ"
👉1000736145182
👉ውዴ ተሰማ እና ወይም ቢኒያም ተፈራ
👉 ጊዜአዊ የልማት ኮሚቴ

የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ገዳም ሰንበት ት/ቤት

Address

Kolfe

Telephone

+251910978168

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ገዳም ሰንበት ት/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ገዳም ሰንበት ት/ቤት:

Share