Ethiopian Catholic Church Vicariate of Jimma Bonga

Ethiopian Catholic Church Vicariate of Jimma Bonga Catholic Church Vicariate of Jimma -Bonga,Ethiopia

በኢኢትዮጵያ   ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን በጅማ ቦንጋ ሃገረስብከት የሺሾእንዴ ቢጣ ወሺ ቀጠና የ3ኛ ሩብ ዓመት ጉባኤ አካሄደ።   ግንቦት 15/2018 ዓ/ም(ጅማ-ቦንጋ ሀገረስብከት )በኢኢትዮ...
23/05/2026

በኢኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን በጅማ ቦንጋ ሃገረስብከት የሺሾእንዴ ቢጣ ወሺ ቀጠና የ3ኛ ሩብ ዓመት ጉባኤ አካሄደ።
ግንቦት 15/2018 ዓ/ም(ጅማ-ቦንጋ ሀገረስብከት )

በኢኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን በጅማ ቦንጋ ሃገረስብከት የሺሾእንዴ ቢጣ ወሺ ቀጠና የ3ኛ ሩብ ዓመት ጉባኤ አካሄደ።

ጉባኤው የተካሄደው በሸዳ ቅ/ሚካኤል ቁምስና ነው ።

በጉባኤው የቀጠና መሪ ካህን ክቡር አባ አድማሱ ገብሬ ፕሮግራሙን በፀሎትና ቡራኬ የከፈቱ ሲሆን የቁምስናው መዘምራን በአዲስ ለህትመት ካዘጋጁ መዝሙር ወስጥ በዝማሬ ጉባዔውን አድምቀዋል።

ክቡር አባ አድማሱ ገብሬ ክርስቶስን መምሰል በሚል ርዕስ መንፈሳዊ ትምህርት አቅርበዋል።

"ክርስቲያኖችም ለመጀመሪያ ጊዜ ክርስቲያን ተብለው የተጠሩት በአንጾኪያ እንደሆነና ይህንን ከመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል:- የሐዋ ሥራ 11:28; 26:28; 1ኛ ጴጥ 4:16 በመጥቀስ ።"አስተንትኖ ሰጥተዋል ።

በመቀጠልም ክቡር አባታችን እኛ ክርስቲያኖች ክርስቲያን የሚለውን ሥም ያገኘነው ከራሱ ከክርስቶስ ስለሆነ እሱ የሚወደውን በመዉደድ ያልፈቀደውን ባለማድረግ መኖር ግዴታ እንደሆነ በአፅንኦት አሳስበዋል ።

ክርስቲያን ክርስቶስን ከመሰለ በምንም ጉዳይ ውሸት መነጋገር እንደሌለበት ከቆላስያስ 3:9_10 ያለዉን ክፍል በመጥቀስ ጥልቅ ትምህርት ስጥተዋል ።

መ/ር ገረመው ገ/የሱስ ስለሞዲዮ ሰማዕታት የተለያዪ የልማት ሥራዎችን በማስመልከት ቀጠናችን በሥሩ ያሉትን ቤተክርስቲያን እና ፀሎት ቤቶችን በማስተባበር ካሰባሰበ ገንዘብ ወጪ በማድረግ የቡና እርማትና ኩትኳቶ ሥራ እየተሠራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

የቀጠናው ገንዘብ ያዥ የሆኑት መ/ር መስፍን መሮ ስለቤተክርስቲያን ልማትና ስለሚገጥማት ተግዳሮቶች አጭር ሰነድ አቅርበዋል።

በጉባኤ ዕለትም መ/ር ገረመው እና መ/ር መስፍን ከቀጠና ኮሚቴ በተጨማሪ የካታክስትነት ስራውን እንዲሠሩ በጉባኤ ፊት እውቅና ተሰጥቷል።

በአጠቃላይ የጉባኤው ታዳሚዎች ከላይ በቀረበው መንፈሳዊ ትምህርትና የዉይይት አጀንዳዎች ጠለቅ ያለ ዉይይትና የጋራ መቋጫ ተደርጎ ጉባኤው በምስጋና: በቡራኬ እንዲሁም በመዝጊያ ፀሎት ተቋጭቷል።
በቆጭቶ ተረፈ
ከሺሺንዳ

  #ማስታወቂያ ለስራ ፈላጊዎች በካቶሊክ ቤተክርስቲያን ቦንጋ  #አሪዮ ሌርንንግ ኢንስቲትዩት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ብቁ መምህራንን አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል።ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ ...
18/05/2026


#ማስታወቂያ ለስራ ፈላጊዎች

በካቶሊክ ቤተክርስቲያን ቦንጋ #አሪዮ ሌርንንግ ኢንስቲትዩት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ብቁ መምህራንን አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል።

ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ ፦የመጀመሪያ ድግሪ በመምህርነት የተመረቀ ሁኖ የማስተማር ስነ-ዘዴ (Pedagogy )ስልጠና የወሰደ/የወሰደች።

የስራ ልምድ፦ሦስት አመት እና በላይ

ብዛት ፥16

ተፈላጊ የትምህርት መስኮች ፦ካፊ-ኖኖ ፣አማርኛ ፣እንግሊዘኛ ፣ሒሳብ ፣ታሪክ፣ጂኦግራፊ ፣ስነ-ዜጋ፣ሰውነት ማጎልመሻ፣አይ ሲቲ፣ባዮሎጂ ፣ኢኮኖሚክስ፣ኬሚስትሪ እና በፊዚክስ የትምህር አይነት ከታወቀ የመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋም የተመረቀ/የተመረቀች።

#በአስተዳደር ዘርፍ -1 . #በህዝብ አስተዳደር የመጀመሪያ ድግሪ እና 3 ዓመት የስራ ልምድ ያለው ያላት

#ቤተ-መጻሕፍት ባለሙያ .. በዘርፋ ከታወቀ ዩንቨርስቲ የመጀመሪያ ድግሪ እና 3 ዓመት

#ላብራቶሪ ቴክኒሽያን ብዛት 1... #በባዮሎጂ እና ተያያዠ የትምህርት መስኮች የመጀመሪያ ድግሪ እና 3 ዓመት የስራ ልምድ ያለው።

ደመወዝ ፦በስምምነት

የመመዝገቢያ ቦታ፦ ቦንጋ አሪዮ ሊርንንግ እንስቲቱተ በአካል በመቅረብ መመዝገብ ይችላሉ።

በተጨማሪም አመልካቾች መሉ መረጃቸውን /CV/ ወደ PDF በመቀየር ከታች ኢ-ሜይል መረጃቸውን መላክ ይችላሉ።
[email protected].

የምዝገባ ቀን፦ይህ ማስታወቂያ ከተለቀቀበት ቀን ጀምሮ እስከ ግንቦት 29 ሲሆን አመልካቾች ግንቦት 30 በትምህርት ተቋሙ መገኘት አለባቸው።

በካቶሊክ ቤተክርስቲያን #አሪዮ ካቶሊክ ሌርንንግ እንስቲትዩት ።
[email protected]

 #ግንቦት 6/2018    #ዜና ዕረፍትበኢትዮጰያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ጅማ-ቦንጋ ሀገረስብከት አበራ በቆ ቅዱስ ጊዮርግስ ቤተ ክርስቲያን.ቁምስና አገልጋይ የነበሩ ካታክስቴ ጴጥሮስ  ወል...
14/05/2026

#ግንቦት 6/2018

#ዜና ዕረፍት

በኢትዮጰያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ጅማ-ቦንጋ ሀገረስብከት አበራ በቆ ቅዱስ ጊዮርግስ ቤተ ክርስቲያን.ቁምስና አገልጋይ የነበሩ ካታክስቴ ጴጥሮስ ወልደጊዮርጊስ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ።

ስርዓተ ቀብራቸው አበራ በቆ ቅዱስ ጊዮርግስ ቤተ- ክርስቲያን ተፈጽሟል ።

"መልካሙን ውጊያ ተዋግቸዋለሁ፤እምነቴን ጠብቃለሁ፤ከእንግዲህ ወዲህ ጻድቅ ፈራጅ የሆነ ጌታ በዚያ ቀን ሲሸልመኝ የጽድቅ አክሊል አዘጋጅቶ ይጠብቀኛል"።2ኛጢሞ ፥ም.4 ፥7-8

በኢትዮጰያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ጅማ-ቦንጋ ሀገረስብከት አበራ በቆ ቅዱስ ጊዮርግስ ቤተ ክርስቲያን.ቁምስና አገልጋይ የነበሩ ካታክስቴ ጴጥሮስ ወልደጊዮርጊስ /ጊዮርግስ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ።

ካታክስት ጴጥሮስ ከአባታቸው ከአቶ ወ/ጊዮርግስ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ ማርጌሪታ በ1954 ዓ/ም በካፋ ዞን በሺሾ እንዴ ወረዳ በበቆ ቀበሌ ተወለዱ።

ለትምህርት ካላቸው ፍላጎት ወደ ደቂያ በመጓዝ እስከ 8ኛ ክፍል ትምህርታቸውን ተከታትለዋል።

በወቅቱ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ባለመኖሩ ምክንያት ትምህርታቸውን በማቋረጥ በግብርና ስራ ተሰማርተዋል።

ቢሆንም ባገኙት እውቀት በቀለም አብዮት ዘመቻ ጊዜ የመሠረተ ትምህርት በማስተማር ብዙዎችን ያስተማሩ አባት መሆናቸውን የህይወት ታሪካቸው ያስረዴል።

ካታክስት ጴጥሮስ በእምነት ሕይወታቸው ጠንካራ የነበሩ ሲሆን አሁን በአገልግሎት ያሉትን ጨምሮ ብዙዎችን ትምህርተ ክርስቶስ ፣ቅዱስ ቁርባን፤ምስጥረ ተክሊል በማስተማር ለቁም ነገር ያበቁ አባት ነበሩ።

ካታክስት ጴጥሮስ የወንጌሌ ትምህርት በሚያስተምሩበት ጊዜ የመሰደድ እና እስራት ያጋጠማቸው ቢሆንም ካላቸው ጽኑ እምነት የተነሳ እስከ ህልፈተ ሕይወታቸው ድረስ ኃይማኖታቸውን አቆይተዋል።

ስርዓተ ቀብራቸው በመገኘት ስርዓተ ፍትሀት የመሩት ክቡር አባ ሉቃስ ወ/ሚካኤል እንዳሉት ካታክስት ጴጥሮስ ለእምነታቸው ሲሉ ብዙ መስዋዕት የከፈሉና በቤተ ክርስቲያናችን ብዙ ፍሬ ያፈሩ የወንጌል አስተማሪ ነበሩ ብለዋል።

የዕለቱን ቃለ ሕይወት ያሰሙት የቁምስና ቆሞስ ክቡር አባ ሀብታሙ አቱሞ በበኩላቸው ለአጥንቶች እስትፋንስ የሰጠ አምላክ እና አልዓዛርን ከሞት ያስነሣ አምላክ ከሞት በኋላ ሕይወት እንዳለ ማሳያ ነው ብሎል።

ክቡር አባ ሀብታሙ ካታክስት ጴጥርስ ሕይወታቸውን በሙሉ ለቤተክርስቲያን የሰጡ አባት ናቸው ብለዋል።

የካታክስት የቅርብ ጎደኛ ብራዘር ማቴዎስ ወልደሰንበት ካታክስት ጴጥሮስ ለእምነታቸው የቆሙ ፣የዋህና እና ጠንካራ ክርስቲያን መሆናቸውን መስክረዋል ።

ካታክስት ጴጥሮስ ከቤተ ክርስቲያን አገልግሎት በተጨማሪ የቀበሌ ማህበራዊ ሸንጎ፣መሬት አስተዳደር እና ሌሎች ቦታዎች ማህበረሳባቸው እንዳገለገሉ የሕይወት ታሪካቸው ያሳያል።

ካታክስት ጴጥሮስ ዕለት ረቡዕ ግንቦት 5/2018ዓ.ም በተወለዱ በ64 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።

ካህናት፣ካታክስቶች፣መዘምራን ወዳጅ ዘመድ በተገኙበት እስከ ህልፈተ ሕይወታቸው ያለፈበት ድረስ ባገለገሉበት አበራ በቆ ቅዱስ ጊዮርግስ ቤተ- ክርስቲያን ተፈጽሟል ።

የኢትዮጵያ የካቶሊካዊት ቤተ-ክርስቲያን ጅማ ቦንጋ ሀገረስብከት ለቁምስናው ምዕመናን፣ለቤተሰቦቻቸው እና ወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን ይመኛል።

12/05/2026
ውድ ካቶሊካዊያን እና በጎ ፍቃድ ያላችሁ ሁሉ በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ጅማ-ቦንጋ ሀገረስብከት ጅማ ልደታ ማሪያም ወጣቶች ቁጥር 5 የመዝሙር አልበም ማስመረቃቸው ይታወሳል ። በመሆ...
10/05/2026

ውድ ካቶሊካዊያን እና በጎ ፍቃድ ያላችሁ ሁሉ በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ጅማ-ቦንጋ ሀገረስብከት ጅማ ልደታ ማሪያም ወጣቶች ቁጥር 5 የመዝሙር አልበም ማስመረቃቸው ይታወሳል ።
በመሆኑም ከታች በተቀመጠው ቴሌግራም ቦት በመግባት እና በመግዛት ወጣቶቹን እንድታበረቷቸው በመዝሙሮቹም ተባረኩ እንላለን ።
https://t.me/BemsganaYetemolahBot

የልደታ ማርያም ዓመታዊ ክብረበ ዓል በታላቅ መንፈሳዊ ሥነ-ሥርዓት ተከበረ      ግንቦት 1/2018ዓ.ምበኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን በእምድብር ሀገረስብከት በየሮር ልደታ ማርያም እን...
09/05/2026

የልደታ ማርያም ዓመታዊ ክብረበ ዓል በታላቅ መንፈሳዊ ሥነ-ሥርዓት ተከበረ
ግንቦት 1/2018ዓ.ም
በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን በእምድብር ሀገረስብከት በየሮር ልደታ ማርያም እንዲሁም በመቃና ልደታ ማርያም ቤተክርስቲያን በታላቅ መንፈሳዊ ሥነ-ሥርዓት ተከበረ።
ይህ ግንቦት ወር የልደታ ማርያም ወር እንደመሆኑ ሕዝበ ክርስቲያኑ ወሩን ሙሉ በቤተክርስቲያን ፣ በቤት ውስጥ ፣ በየጸሎት ቤት መቁጠርያ ጸሎት እንዲያደርስብፁዕ አባታችን አሳስበዋል
እንደዚሁም በመቃና ልደታ ማርያም መሥዋዕተ ቅዳሴውን ያሳረጉት ክቡርአባ ሀብቴ(የብፁዕ አባታችን እንደራሴ) የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ልደት፦ስናከብር እያንዳንዳችን ክርስትያኖች እግዚአብሔር የሚሰጠን ጥሪ፣ ጸጋ እንዴት እናዳምጠው እንዴት እንረዳው። በሚል የእግዚአብሔርን ቃል አካፍለዋል።
Source-Catholic Eparchy of Emdeber

በኢትዮጰያ  ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ጅማ ቦንጋ ሀገረስብከት የልደታ ማርያም ዓመታዊ ክብረ በዓል በታላቅ መንፈሳዊ ስነስርአቶች ተከበረ።  ግንቦት 1/2018፦(ጅማ-ቦንጋ ሀገረስብከት)በኢትዮ...
09/05/2026

በኢትዮጰያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ጅማ ቦንጋ ሀገረስብከት የልደታ ማርያም ዓመታዊ ክብረ በዓል በታላቅ መንፈሳዊ ስነስርአቶች ተከበረ።

ግንቦት 1/2018፦(ጅማ-ቦንጋ ሀገረስብከት)

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን በጅማ ቦንጋ አገረስብከት በጅማ ልደታ ማርያም ካቴድራል ዓመታዊው የልደታ ማርያም ክብረ በዓል በታላቅ መንፈሳዊነት ስነስርአቶች ተከብሯል።

የዕለቱን ስርዓተ ቅዳሴ የመሩት የሀገረስብከቱ ጳጳስ እንደራሴ እና ሐዋርያዊ ጽህፈት ቤት አስተባባሪ ክቡር አባ ሳሙኤል ዮሐንስ ለመላው ካቶሊካዊያን እንኳን አደረሳችሁ ፤አደረሰን ሲሉ መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል።

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማሪያም አማላጅነት እና ፍጹም እናትነት እና ፈጣሪ ጥበቃ ታክሎ ለዚህች ዕለት በመብቃታችን ልናመሰግን ይገባል ብለዋል።

ዕለቱን ስብከተ ወንጌል ክቡር ክፍሌ አለማየሁ ያሳረጉ ሲሆን ስለ እናታችን ቅድስት ድንግል ማሪያም ጸጋ እና ስላስገኘችው ዘላለማዊ በረከት ላይ ያተኮሩ ጥልቅ መልዕክቶችን በአስተምህሮአቸው አመላክተዋል።

እንኳን አደረሰን አደረሳችሁ መልዕክትም አስተላልፈዋል።

የቁምስናው ቆሞስ ክቡር አባ አለማየሁ ሀይሌ ይህ በዓል እንድደምቅ ያገዙ ካህናት፣ደናግላን እንድሁም በሀገር ውስጥ እና ከባህር ማዶ የሚኖሩ ወገኖችን አመስግነዋል።

የዘንድሮውን ክብረበዓል ልዩ ያደረገው የቁምስናው ወጣቶች 5ኛ የመዝሙር አልበማቸው ያስመረቁበት በመሆኑ ተጨማሪ መባረክ ነው ተብሏል።

የቁምስናው ወጣቶች አገልግሎት ዘመናቸው እንድባረክ የተመኙት አባ ሀይሌ ቦንጋ ኪዳነምህረት ቁምስና ወጣት መዘምራኖችን እንድሁም ከተለያዩ አከባቢዎች የመጡ ወጣቶችን አመስግነዋል።

መሉ ስነስርዓቱ በሰላም ካቶሊክ ዩቲዩብ ገጽ ቀጥታ የተላለፈ ሲሆን ጣቢያው ለወንጌል ተደራሽነት ለሚያደርጋቸው አገልግሎትም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ስነስርዓቱ ያመለጣችሁ ካቶሊካዊያን እና በጎ ፍቃድ ያላችሁ በተከታዩ ሊንክ ገብታችሁ መመልከት ትችላላችሁ።
https://www.youtube.com/live/JekyC3lWI-s?si=Thq9PIyDpmdMpDoG
ፎቶ፦ ሰላም ካቶሊክ ቴቪ

"የባሪያይቱን ውርደት ሰምቷልና እነሆም ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይሉኛል።''ሉቃ 1፣48    ግንቦት 1/2018 ፦(ጅማ-ቦንጋ ሀገረስብከት )በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን በጅማ ቦንጋ ሀገ...
09/05/2026

"የባሪያይቱን ውርደት ሰምቷልና እነሆም ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይሉኛል።''ሉቃ 1፣48

ግንቦት 1/2018 ፦(ጅማ-ቦንጋ ሀገረስብከት )

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን በጅማ ቦንጋ ሀገረ ስብከት በሺሾ እንዴ ቢጣ ወሺ ቀጠና የጉሬች ልደታ ማሪያም ዓመታዊ ክብረ በዓል ተከበረ።

የዕለቱን መስዋዕተ ቅዳሴ የመሩት ክቡር አባ ሀብታሙ አቱሞ-በአዳም በሰው ልጆች ላይ የመጣውን ኃጥያት ማሪያም የዓለም መድኃኒት የሆነውን ጌታችን እየሱስ ክርቶሰን በንጽህና በመውለድ እኛንና እግዚአብሔርን አስትርቃለች ብሏል።

በመሆኑም ሁላችንም የሚሪያምን አማላጅነት ማመንና መዘከር ያስፈልገናል ብሎል።

የዕለቱን ቃለ እግዚአብሔር ያሰሙት ክቡር አባ ይስሐቅ ታደሰ በበኩላቸው የማሪያም ሕይወት ታዛዥ ፣ትህትና፣ንጽህና እና ታማኝነት ስለሆነ ይህንን የማሪያምን ፈለግ መከተል አለብን ብሏል።

ክቡር አባ ይስሐቅ በመቀጠል ማሪያም መልካሙን ያደረገችው በወጣትነት ስለሆነ ወጣቶችም ከተለያዪ ሱስ ነጻ በመሆን የማሪያም ሥነ ምግባር እንድላበሱ ሰፊ ትምህርት ሰጥቶል።

የቁምስና ቆሞስ ክቡር አባ አማኑኤል ሙላቱ በዓሉ ደምቆ እንዲከበር የተባበሩትን ካህናት፣ካታክስቶች፣መዘምራንና ምዕመናን ሁሉ ያመሰገኑ ሲሆን ቅዱስ ቁርባንና ታቦት በመያዝ ኡደት ተደርጎ ስነስርዓቱ ፍጻሜ አግኝቷል ።

ለዓመቱ ያድርሰን ።

09/05/2026

📡 Live | Pax Catholic Television📺 ቀጥታ ስርጭት | ሰላም ካቶሊክ ቲቪ #ቀጥታ #ካቶሊክ #ቅዳሴ #ካቶሊክ #ኢት...

በጅማ የልደታ ማርያም ቁምስና 5ኛ የመዝሙር አልበም አስመረቀ። ሚያዝያ 30 /2018 ዓ.ም፦ (ጅማ -ቦንጋ ሀገረስብከት )በጅማ ቦንጋ አገረ ስብከት የልደታ ማርያም ቁምስና 5ኛውን ''በምስጋ...
08/05/2026

በጅማ የልደታ ማርያም ቁምስና 5ኛ የመዝሙር አልበም አስመረቀ።

ሚያዝያ 30 /2018 ዓ.ም፦ (ጅማ -ቦንጋ ሀገረስብከት )

በጅማ ቦንጋ አገረ ስብከት የልደታ ማርያም ቁምስና 5ኛውን ''በምስጋና የተሞላህ'' የመዝሙር አልበም በድምቀት አስመረቋል።

14 መዝሙሮችን ያቀፈው ''በምስጋና የተሞላህ'' የመዝሙር አልበም ምርቃት በጸሎት በመጀመር በዝማሬ፣ በመዝሙር ኬሮግራፍ፣ በመንፈሳዊ ግጥም እና በምስጋና በድምቀት ተካሒዷል።

በመዝሙር አልበም ምርቃቱ ተገኝተን ያነጋገርናቸው የጅማ ልደታ ማርያም ቁምስና ዘማሪያንም አልበሙን ለማውጣት ብዙ ጥረቶች ያደረጉ መሆኑን በመግለጽ በዚህ ረጅም ጉዞዋቸው እገዛ ላደረጉላቸው ሁሉ ጥልቅ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

የመዝሙር አልበም ምርቃቱ ከዘማሪያኑ በተጨማሪ የጅማ ቦንጋ አገረ ስብከት ጳጳስ እንደራሴ ክቡር አባ ሳሙኤል ዮሐንስ፣ የልደታ ማርያም ቁምስና ቆሞስ ክቡር አባ አለማየሁ፣ በርካታ ካህናት፣ ደናግል፣ ተጋባዥ ዘማሪያን እና ምዕመናን ተገኝተዋል።

ሰላም ካቶሊክ ቴቪ

Address

Jimma

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Catholic Church Vicariate of Jimma Bonga posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Ethiopian Catholic Church Vicariate of Jimma Bonga:

Share