23/05/2026
በኢኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን በጅማ ቦንጋ ሃገረስብከት የሺሾእንዴ ቢጣ ወሺ ቀጠና የ3ኛ ሩብ ዓመት ጉባኤ አካሄደ።
ግንቦት 15/2018 ዓ/ም(ጅማ-ቦንጋ ሀገረስብከት )
በኢኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን በጅማ ቦንጋ ሃገረስብከት የሺሾእንዴ ቢጣ ወሺ ቀጠና የ3ኛ ሩብ ዓመት ጉባኤ አካሄደ።
ጉባኤው የተካሄደው በሸዳ ቅ/ሚካኤል ቁምስና ነው ።
በጉባኤው የቀጠና መሪ ካህን ክቡር አባ አድማሱ ገብሬ ፕሮግራሙን በፀሎትና ቡራኬ የከፈቱ ሲሆን የቁምስናው መዘምራን በአዲስ ለህትመት ካዘጋጁ መዝሙር ወስጥ በዝማሬ ጉባዔውን አድምቀዋል።
ክቡር አባ አድማሱ ገብሬ ክርስቶስን መምሰል በሚል ርዕስ መንፈሳዊ ትምህርት አቅርበዋል።
"ክርስቲያኖችም ለመጀመሪያ ጊዜ ክርስቲያን ተብለው የተጠሩት በአንጾኪያ እንደሆነና ይህንን ከመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል:- የሐዋ ሥራ 11:28; 26:28; 1ኛ ጴጥ 4:16 በመጥቀስ ።"አስተንትኖ ሰጥተዋል ።
በመቀጠልም ክቡር አባታችን እኛ ክርስቲያኖች ክርስቲያን የሚለውን ሥም ያገኘነው ከራሱ ከክርስቶስ ስለሆነ እሱ የሚወደውን በመዉደድ ያልፈቀደውን ባለማድረግ መኖር ግዴታ እንደሆነ በአፅንኦት አሳስበዋል ።
ክርስቲያን ክርስቶስን ከመሰለ በምንም ጉዳይ ውሸት መነጋገር እንደሌለበት ከቆላስያስ 3:9_10 ያለዉን ክፍል በመጥቀስ ጥልቅ ትምህርት ስጥተዋል ።
መ/ር ገረመው ገ/የሱስ ስለሞዲዮ ሰማዕታት የተለያዪ የልማት ሥራዎችን በማስመልከት ቀጠናችን በሥሩ ያሉትን ቤተክርስቲያን እና ፀሎት ቤቶችን በማስተባበር ካሰባሰበ ገንዘብ ወጪ በማድረግ የቡና እርማትና ኩትኳቶ ሥራ እየተሠራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
የቀጠናው ገንዘብ ያዥ የሆኑት መ/ር መስፍን መሮ ስለቤተክርስቲያን ልማትና ስለሚገጥማት ተግዳሮቶች አጭር ሰነድ አቅርበዋል።
በጉባኤ ዕለትም መ/ር ገረመው እና መ/ር መስፍን ከቀጠና ኮሚቴ በተጨማሪ የካታክስትነት ስራውን እንዲሠሩ በጉባኤ ፊት እውቅና ተሰጥቷል።
በአጠቃላይ የጉባኤው ታዳሚዎች ከላይ በቀረበው መንፈሳዊ ትምህርትና የዉይይት አጀንዳዎች ጠለቅ ያለ ዉይይትና የጋራ መቋጫ ተደርጎ ጉባኤው በምስጋና: በቡራኬ እንዲሁም በመዝጊያ ፀሎት ተቋጭቷል።
በቆጭቶ ተረፈ
ከሺሺንዳ