15/12/2025
!
እንኳን ለክርስቶስ ንጉስ በዓል እና ለዓለም ካቶሊክ ወጣቶች ቀን በሠላም አደረሰን።
በሆሳዕና ሀገረ ስብከት በጃጁራ ቅዱሳን ጴጥሮስ እና ጳውሎስ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን በየዓመቱ የሚደረገው እግዚአብሔር ከሰጠው ለእሱ በምስጋና እና በፍቅር መልክ የሚሰጠው የእህል አሥራት ማስገባት ሥራ በዛሬው ዕለት ማለትም ታህሣሥ 5/2018ዓ/ም ተከናውኗል።
በፈጣሪ በመታመን ደረቅ ዘር በመሬት ጥሎ ያንን የፍጥረታት ጌታ እግዚአብሔር በዝናቡም በፀሐዩም ተንከባክቦ ልፋታቸውን ፍሬ አድርጎ ሲሰጥ እሱን በበረከቱ ማመስገን መቻል መታደልም ጭምር ነው። ይህ ተግባር በቁምስናው እጅግ ልዩ ከሆኑ ቀናት ወይንም በዓላት አንዱ ነው።
ቅዱስ ቃሉም እንደሚል ''በቤቴ ውስጥ መብል እንዲሆን አሥራቱን ሁሉ ወደ ጎተራ አግቡ፤ የሰማይንም መስኮት ባልከፍትላችሁ፥ በረከትንም አትረፍርፌ ባላፈስስላችሁ በዚህ ፈትኑኝ፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር።''
ት.ሚል 3፥10
ምንም እንኳን ያለንበት ጊዜ የኑሮ ሁኔታ አስቸጋሪ ቢሆንም የእግዚአብሔር ቤት ጎተራ ጎድሎ የእኛ የሞላ መሆን ሰጪውን መርሳት ይሆናል በሚል እኛም የእኛ የሆነውም ሁሉ የእርሱ ነው በማለት እና ለእርሱ መስጠት ማጉደል ሳይሆን መባረክ በማለት በፍቅር ለእግዚአብሔር ቃል ታዘው የሚያደርጉት መሆኑ እጅግ አስደሳች ነው።
በዚህ ቀን(በዓል) ሌላው አስደሣች ኩነት የሚሆነው የእህል አሥራት ፈንታ በማሳቸው ዘርተው የማያስገቡ ምዕመናንም አቅማቸው በፈቀደው ልክ በገንዘብ በማድረግ የሰጣቸውን ፈጣሪ በመስጠት ያመሰግናሉ።
የእህል አሥራት ማስገባት በዛሬ ዕለት በዋናነት የተደረገ ቢሆንም ለቀጣይ 2 እና 3 ሣምንታትም ያልደረሱ ምዕመናን ማስገባታቸውን ይቀጥላሉ።
እግዚአብሔር ከሰጣቸው ለእርሱ በምስጋና አሥራት ያቀረቡትን ምዕመናንን ሰጪው ራሱ በበረከቱ ሁሉ ይባርካቸው፡ ይህን መልካሙን ነገራቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉም መንፈሳዊ አቅማቸውን ያጎልብት፣ ፍቅርና አንድነቱን ያብዛላቸው!🙏
Issitakkam luwwa moollan yesuusinaa
Awwaaddakkam awwaadom moollan yesuusinaa
Yitakku'uuyyi issehe manninatte ihoobee'isaa
Moollanni iyeesuus irifo'o uwwoo'isaa
: ይህንን ፅሑፍ ደርሷችሁ የሚታነቡ ሁሉ የዚህ ልጥፍ ዓላማ - ምን አልባት ይህ መጠነኛ ተሞክሮ ለሌሎች ቤተክርስቲያናት (ካቶሊክም ሆነ ሌሎችም) አወንታዊ ሞራል እና ትምህርት ከሆነ በሚል እንጂ ለታይታና መገበዝ እንዳልሆነ፡ ባልወከልም ቤተክርስቲያኒቷን በራሴ ጊዜ ወክዬ አበክሬ በታላቅ ትህትና አሳስባለሁ🙏። ከዚያ የዘለለ ነገር አይጠቅመንምና።
ፈጣሪ ይባርከን!!🙏🙏
Bereket Amanuêl