St Peter And Paul Catholic Church Jajura

St Peter And Paul Catholic Church Jajura Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from St Peter And Paul Catholic Church Jajura, Religious organisation, Hossana.

 !እንኳን ለክርስቶስ ንጉስ በዓል እና ለዓለም ካቶሊክ ወጣቶች ቀን በሠላም አደረሰን።በሆሳዕና ሀገረ ስብከት በጃጁራ ቅዱሳን ጴጥሮስ እና ጳውሎስ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን በየዓመቱ የሚደረገው...
15/12/2025

!

እንኳን ለክርስቶስ ንጉስ በዓል እና ለዓለም ካቶሊክ ወጣቶች ቀን በሠላም አደረሰን።

በሆሳዕና ሀገረ ስብከት በጃጁራ ቅዱሳን ጴጥሮስ እና ጳውሎስ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን በየዓመቱ የሚደረገው እግዚአብሔር ከሰጠው ለእሱ በምስጋና እና በፍቅር መልክ የሚሰጠው የእህል አሥራት ማስገባት ሥራ በዛሬው ዕለት ማለትም ታህሣሥ 5/2018ዓ/ም ተከናውኗል።

በፈጣሪ በመታመን ደረቅ ዘር በመሬት ጥሎ ያንን የፍጥረታት ጌታ እግዚአብሔር በዝናቡም በፀሐዩም ተንከባክቦ ልፋታቸውን ፍሬ አድርጎ ሲሰጥ እሱን በበረከቱ ማመስገን መቻል መታደልም ጭምር ነው። ይህ ተግባር በቁምስናው እጅግ ልዩ ከሆኑ ቀናት ወይንም በዓላት አንዱ ነው።

ቅዱስ ቃሉም እንደሚል ''በቤቴ ውስጥ መብል እንዲሆን አሥራቱን ሁሉ ወደ ጎተራ አግቡ፤ የሰማይንም መስኮት ባልከፍትላችሁ፥ በረከትንም አትረፍርፌ ባላፈስስላችሁ በዚህ ፈትኑኝ፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር።''
ት.ሚል 3፥10
ምንም እንኳን ያለንበት ጊዜ የኑሮ ሁኔታ አስቸጋሪ ቢሆንም የእግዚአብሔር ቤት ጎተራ ጎድሎ የእኛ የሞላ መሆን ሰጪውን መርሳት ይሆናል በሚል እኛም የእኛ የሆነውም ሁሉ የእርሱ ነው በማለት እና ለእርሱ መስጠት ማጉደል ሳይሆን መባረክ በማለት በፍቅር ለእግዚአብሔር ቃል ታዘው የሚያደርጉት መሆኑ እጅግ አስደሳች ነው።

በዚህ ቀን(በዓል) ሌላው አስደሣች ኩነት የሚሆነው የእህል አሥራት ፈንታ በማሳቸው ዘርተው የማያስገቡ ምዕመናንም አቅማቸው በፈቀደው ልክ በገንዘብ በማድረግ የሰጣቸውን ፈጣሪ በመስጠት ያመሰግናሉ።

የእህል አሥራት ማስገባት በዛሬ ዕለት በዋናነት የተደረገ ቢሆንም ለቀጣይ 2 እና 3 ሣምንታትም ያልደረሱ ምዕመናን ማስገባታቸውን ይቀጥላሉ።

እግዚአብሔር ከሰጣቸው ለእርሱ በምስጋና አሥራት ያቀረቡትን ምዕመናንን ሰጪው ራሱ በበረከቱ ሁሉ ይባርካቸው፡ ይህን መልካሙን ነገራቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉም መንፈሳዊ አቅማቸውን ያጎልብት፣ ፍቅርና አንድነቱን ያብዛላቸው!🙏

Issitakkam luwwa moollan yesuusinaa
Awwaaddakkam awwaadom moollan yesuusinaa
Yitakku'uuyyi issehe manninatte ihoobee'isaa
Moollanni iyeesuus irifo'o uwwoo'isaa

: ይህንን ፅሑፍ ደርሷችሁ የሚታነቡ ሁሉ የዚህ ልጥፍ ዓላማ - ምን አልባት ይህ መጠነኛ ተሞክሮ ለሌሎች ቤተክርስቲያናት (ካቶሊክም ሆነ ሌሎችም) አወንታዊ ሞራል እና ትምህርት ከሆነ በሚል እንጂ ለታይታና መገበዝ እንዳልሆነ፡ ባልወከልም ቤተክርስቲያኒቷን በራሴ ጊዜ ወክዬ አበክሬ በታላቅ ትህትና አሳስባለሁ🙏። ከዚያ የዘለለ ነገር አይጠቅመንምና።

ፈጣሪ ይባርከን!!🙏🙏
Bereket Amanuêl

ከኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን የጳጳሳት ጉባኤ የተላለፈ የኀዘን መግለጫ  | የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን የጳጳሳት ጉባኤ ጥቅምት አጋማሽ 2018 ዓ.ም. በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሀረ...
04/11/2025

ከኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን የጳጳሳት ጉባኤ የተላለፈ የኀዘን መግለጫ

| የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን የጳጳሳት ጉባኤ ጥቅምት አጋማሽ 2018 ዓ.ም. በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሀረርጌ ሚደግዱ አስተርዮ ማርያም ካቶሊክ ቤተክርስቲያን አካባቢ በተፈጸመው ግድያ የካቶሊካውያን ሕይወት ማለፉንና ንብረት መቃጠሉን በታላቅ ሀዘን ሰምተናል።

በተጨማሪም በኦሮሚያ ክልል በአርሲ ዞን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እና የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ምዕመናን ላይ ተመሳሳይ ግድያ መፈጸሙን ተቋማቱ ባወጡት መግለጫ ሰምተናል።

ቤተክርስቲያናችን ይህን አይነቱን ኢ-ሰብዓዊ ተግባር አጥብቃ ታወግዛለች፤ በመሆኑም የዜጎችን ሰላም እና ደህንነት ለማረጋገጥ መንግስት አስቀድሞ አስፈላጊውን የሕግ ማስከበር ሥራ እንዲሠራ ቤተክርስቲያናችን ጥሪዋን ታቀርባለች።

የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን የጳጳሳት ጉባኤ በዚህ እጅግ አሳዛኝ ተግባር ሕይወታቸውን ላጡ ወገኖቻችን ዘለዓለማዊ እረፍትን ያገኙ ዘንድ እየጸለየች የተሰማንን ሀዘን ለመላው ካቶሊካውያን፣ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን፣ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት፣ ለመላው ኢትዮጵያውያን እና ለተጎዱ ቤተሰቦች ፈጣሪ እውነተኛ መጽናናት እንዲሰጥልን ከልብ እንመኛለን፡፡

 |የድሆች አገልጋዮች እህቶች ማኅበር 50ኛ የወርቅ ኢዮቤልዩ ክብረ በዓል ተከበረ።  #መስከረም 24 ቀን 2017 ዓ.ም. የድሆች አገልጋዮች እህቶች ማኅበር 50ኛ የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓል እና...
04/10/2025

|የድሆች አገልጋዮች እህቶች ማኅበር 50ኛ የወርቅ ኢዮቤልዩ ክብረ በዓል ተከበረ።

#መስከረም 24 ቀን 2017 ዓ.ም. የድሆች አገልጋዮች እህቶች ማኅበር 50ኛ የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓል እና የሁለት እህቶች የመጀመሪያ እና የመጨረሻ መሐላ ተካሄደ።

#50ኛ የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓል እና የእህት አይናለም ተፈራ የመጀመሪያ መሐላ እንዲሁም የእህት አመለወርቅ ማኬቦ የመጨረሻ መሐላ የተካሄደው የድሆች አገልጋዮች እህቶች ማኅበር በኢትዮጵያ አገልግሎቱን በጀመረበት በሆሳዕና ሀገረ ስብከት በጃጁራ ቅዱሳን ጴጥሮስ እና ጳውሎስ ቁምስና ነው።

#የክብረ በዓሉን እና የመሐላ መሥዋዕተ ቅዳሴውን ያሳረጉት የሆሳዕና ሀገረ ስብከት ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ስዩም ፍራንሷ የድሆች አገልጋዮች እህቶች ማኅበር በሰበካው ላደረጉት እና ለሚያደርጉት ሥራ ሁሉ አመስግነዋል።

#በድሆች አገልጋዮች እህቶች ማኅበር 50ኛ የወርቅ ኢዮቤልዩ እና የሁለት እህቶች መሐላ መሥዋዕተ ቅዳሴ ብፁዕነታቸውን እና የሆሳዕና ሀገረ ስብከት የበላይ አመራር እና ካህናት፣ የአካባቢው የመንግሥት አመራር አካላት እና የሃይማኖት ተወካዮች፣ የማኅበሩ የበላይ አለቃዎች እና እህቶች ፣ የክኔዋ ተቋም የበላይ ኃላፊዎች፣ ዘማሪያን እና ከቅርብ እና ከሩቅ የመጡ ተጋባዥ እንግዶች እና ምዕመናን በመገኘት በመንፈሳዊ ድምቀት ተከብሯል።

 /የድሆች አገልጋዮች እህቶች ማኅበር የተመሰረተበት 50ኛ ዓመት ዋዜማ በመቁጠሪያ ጸሎት ታሰበ።  #ቀን 23/01/2018 ዓ/ም  #በዓለም አቀፍ በፈረንጆቹ 1951 የተመሰረተው እና በሀገራች...
03/10/2025

/የድሆች አገልጋዮች እህቶች ማኅበር የተመሰረተበት 50ኛ ዓመት ዋዜማ በመቁጠሪያ ጸሎት ታሰበ።

#ቀን 23/01/2018 ዓ/ም

#በዓለም አቀፍ በፈረንጆቹ 1951 የተመሰረተው እና በሀገራችንም በ1975 የገባው የድሆች አገልጋዮች እህቶች ማኅበር 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ ዋዜማው አገልግሎቱ በጀመረበት በሆሳዕና ሀገረ ስብከት በጃጁራ ቅዱሳን ጴጥሮስና ጳውሎስ ቁምስና መቁጠሪያ ጸሎት በማድረግ ታስቧል።

#በመቁጠሪያ ጸሎቱ በሀገራችን እና በዓለም የሚገኙ የድሆች አገልጋዮች እህቶች ማኅበር አባላት፣ የጃጁራ ቅዱሳን ጴጥሮስና ጳውሎስ ቁምስና ቆሞስ ክቡር አባ ታረቀኝ ዮሐንስ እና ሌሎች ካህናት እንዲሁም ምዕመናን በመገኘት ማኅበሩን እና ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያንን በማሰብ ተደርጓል።

#በነገው ዕለት ቅዳሜ መስከረም 24 ቀን 2018 ዓ.ም የድሆች አገልጋዮች እህቶች ማኅበር 50ኛ ዓመት ክብረ በዓል የሆሳዕና ሀገረ ስብከት ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ስዩም ፍራንሷ በሚመሩት መሥዋዕተ ቅዳሴ በድምቀት ይከበራል።

#ሰላም ካቶሊክ ቴሌቪዥንም የ50ኛ ዓመት ክብረ በዓል መሥዋዕተ ቅዳሴውን በቀጥታ ስርጭት በቴሌቪዥን እና በዩቱብ የሚያስተላልፍ ይሆናል።

#ለድሆች አገልጋዮች እህቶች ማኅበር እንኳን ለ50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን 🎚️

 የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስብፁዕ አባታችን ካርዲናል ብርሃነየሱስ ሱራፌል የዓመቱ ምርጥ የሃይማኖት አባት በመባል ተመርጠዋል።  በትክክልም ይገበዎታል እንኳን ደስ አልዎት ...
30/09/2025



የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ
ብፁዕ አባታችን ካርዲናል ብርሃነየሱስ ሱራፌል የዓመቱ ምርጥ የሃይማኖት አባት በመባል ተመርጠዋል።

በትክክልም ይገበዎታል እንኳን ደስ አልዎት እኛም ደስ ብሎና

በሆ/ሀ/ስብከት በጃጁራ ቅዱሳን ጴጥሮስ እና ጳውሎስ ካቶሊክ ቤተ-ክርስቲያን የዳመራ በዓል በዚህ መልክ ተከብሮል::🎚️እንኳን ለ2018 ዓ/ም የመስቀል ደመራ በዓል በሠላም አደረሳችሁ አደረሰን...
27/09/2025

በሆ/ሀ/ስብከት በጃጁራ ቅዱሳን ጴጥሮስ እና ጳውሎስ ካቶሊክ ቤተ-ክርስቲያን የዳመራ በዓል በዚህ መልክ ተከብሮል::🎚️

እንኳን ለ2018 ዓ/ም የመስቀል ደመራ በዓል በሠላም አደረሳችሁ አደረሰን።
መልካም የመስቀል በዓል!!✝️

የቁምስናች ፍሬ የሆነው ቢን (ቹቹ) አለበት እግዚአብሔር አመስግኑት 🙏በመገናሴ ቅ/ፍራንሲስኮስ ቁምስና የመገናሴ ካፑቺን አባቶች የቅ/ፍራንሲስኮስ የማኅበራቸው መሥራች የኢየሱስ ችንካሮች በአካ...
18/09/2025

የቁምስናች ፍሬ የሆነው ቢን (ቹቹ) አለበት እግዚአብሔር አመስግኑት 🙏

በመገናሴ ቅ/ፍራንሲስኮስ ቁምስና የመገናሴ ካፑቺን አባቶች የቅ/ፍራንሲስኮስ የማኅበራቸው መሥራች የኢየሱስ ችንካሮች በአካሉ የተሸከመበትን ቀን መስከረም 7 በማስታወስ በየዓመቱ በመገናሴ የሚገኙና ዓመቱን ሙሉ የተመክሮ ሥርዓት ሲፈጽሙ የቆዩ የምንኩስና ሕይወት የጀመሩ ወጣቶች የመጀመሪያ መሐላ ያደርጋሉና ዛሬ መስከረም 07/2018 ዓ.ም. በመገናሴ ቅ/ፍራንሲስኮስ ቁምስና ስድስት ወጣቶች የመጀመሪያ የምንኩስና ሕይወት መጀመሪያ መሐላ አድርገዋል።

ፍልሰታ ለማርያም በኅዳር 1 ቀን 1950 ዓ.ም ር.ሊ.ጳ ፒዮስ 12ኛ  በ50 ካርዲናሎች ፤ 700 ጳጳሳት ፤ 600,000 ምእመናን ፊት በሮም ከተማ ስለ ፍልሰታ ለማርያም የሚከተለውን ቀኖናዊ...
07/08/2025

ፍልሰታ ለማርያም በኅዳር 1 ቀን 1950 ዓ.ም ር.ሊ.ጳ ፒዮስ 12ኛ በ50 ካርዲናሎች ፤ 700 ጳጳሳት ፤ 600,000 ምእመናን ፊት በሮም ከተማ ስለ ፍልሰታ ለማርያም የሚከተለውን ቀኖናዊ ትምህርት እንዲህ እያሉ እወጁ ። " በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሥልጣን ፣ በቅዱሳን ሐዋርያት ጴጥሮስ ወጳውሎስ ሥልጣን በራሳችንም ሥልጣን ፣ ጸጋን የተሞላች የአምላክ እናት ድንግል ማርያም ፣ ምድራዊ ጉዞዋን እንደጨረሰች በነፍስ ና በሥጋ ወደ ሰማያዊ ክብር እንደ ተወሰደች በእግዚአብሔር የተገለጸ ቀኖናዊ እምነት መሆኑን እንገልጻለን ፣ እናስተምራለን ፣ እናውጃለን ።

እንኳን ለጾመ ፍልሰታ በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን
መልካም የጾምና የጸሎት ጊዜ ይሁንልን

13/07/2025

አዲሱ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛው ማን ናቸው? *****************በቫቲካን ሲቲ ሲደረግ የነበረው የርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ምርጫ ሲጠናቀቅ ካርዲናል ሮበርት ፍራንሲስ ፕሬቮስት 267...
10/05/2025

አዲሱ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛው ማን ናቸው?
*****************

በቫቲካን ሲቲ ሲደረግ የነበረው የርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ምርጫ ሲጠናቀቅ ካርዲናል ሮበርት ፍራንሲስ ፕሬቮስት 267ኛው የሮማን ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሆነው ተመርጠዋል።

የጵጵስና ስማቸውም ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛው ሆኗል። ታዲያ የእርሳቸው መመረጥ በቤተ ክርስቲያኗ ታሪክ የመጀመርያው የአሜሪካ ሰው በመሆን አዲስ ታሪክ ሆኗል።

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛው ውልደታቸው መስከረም 14 ቀን 1955 በአሜሪካ ቺካጎ ኢሊኖይስ ነው።

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ ከፈረንሳይ እና ካናዳ ከሆኑ የካቶሊክ እምነት ተከታይ ቤተሰቦች ነው የተገኙት።

ታዲያ እኚህ አባት በካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ያደጉ ሲሆን በ1982 ደግሞ የመጀመርያውን የክህነት ማዕረጋቸውን ከቅዱስ አውግስቲን ተቀብለዋል።

በሚሲዮናዊነት ወደ ፔሩ በማቅናትም በሥነ መለኮታዊ ዕውቀታቸው ለረጅም ዓመታት ሲያገለግሉ ቆይተዋል።

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛው አሁን 267ኛው የካቶሊክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሆነው ከመመረጣቸው በፊት በቤተክርስቲያኗ ውስጥ ብዙ ስራዎችን የሰሩ ሲሆን በፔሩ የቺክላዮ ኤጲስ ቆጶስ ሆነው አገልግለዋል።

በቆይታ ወደ ሮም የተጠሩት እኚህ አባት በዓለም ላይ ያሉትን ኤጲስ ቆጶሳት የመምረጥ ኃላፊነት ተሰጥቷቸው ቆይተዋል።

በዚህ አገልግሎታቸውም ዓለም አቀፋዊ ክብርን አግኝተዋል።

በካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ባላቸው የሥነ መለኮት እውቀት ብቻ ሳይሆን ስለ ማህበራዊ ፍትሕ በሚያደርጉት ስራ እና በሚሲዮናዊነት ስራቸው ምስጉን መሆናቸው ይመሰከርላቸዋል።

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሆነው ከተመረጡ በኋላ በቅዱስ ጴጥሮስ ባሲሊካ ባደረጉት የመጀመርያው ንግግራቸው "ሰላም ከሁላችሁ ጋር ይሁን " በማለት መልዕክት አስተላልፈዋል።

በቢታንያ ሲሳይ

Address

Hossana

Telephone

+251939260636

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when St Peter And Paul Catholic Church Jajura posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share