ብሕንሳ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

  • Home
  • Ethiopia
  • Hossana
  • ብሕንሳ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

ብሕንሳ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት ሚዲያ EOTC Archdiocese of Hadiya and Silte በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ የሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት
(1)

14/09/2026

ሙሉዉን የሰላም ሽማግሌዎች ከሕዝበ ክርስቲያኑ ጋር ያደረጉትን ውይይት በብሕንሳ ሚዲያ በቅርብ ቀን ይጠብቁ

+++++++++++++++++++++++
መስከረም 4 ቀን 2019 ዓ/ም(ብሕንሳ ሚዲያ/ሆሳዕና)
+++++++++++++++++++++++

የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ በዓለ ልደቱ በሆሣዕና ላልሺፋ ወንጌላዊ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን በድምቀት ተከበረ።+++++++++++++መስከረም 4 ቀን 2019 ዓ.ም(ብሕንሳ ሚዲያ ሆሣዕና )++...
14/09/2026

የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ በዓለ ልደቱ በሆሣዕና ላልሺፋ ወንጌላዊ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን በድምቀት ተከበረ።

+++++++++++++
መስከረም 4 ቀን 2019 ዓ.ም(ብሕንሳ ሚዲያ ሆሣዕና )
+++++++++++++

© በአባቶችሽ ፈንታ

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ልዩ ጽ/ቤትና የውጭ ጉዳይ መምሪያ የሥራ ሓላፊዎችና ሠራተ...
14/09/2026

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ልዩ ጽ/ቤትና የውጭ ጉዳይ መምሪያ የሥራ ሓላፊዎችና ሠራተኞች ርእሰ ዓውደ ዓመት በማስመልከት ከቅዱስነታቸው ቡራኬና የሥራ መመሪያ ተቀበሉ።

በመርሐ ግብሩ የሁለቱ የሥራ ክፍሎች ተወካይ ባደረጉት ንግግር የዓመቱን ሥራ በቅዱስነታቸው ቡራኬ መጀመራቸው ታላቅ ዕድል መሆኑን አስታውሰው፤ "የቅዱስነትዎን የዕለት ከዕለት አባታዊ የሥራ መመሪያ እየተቀበልን በማገልገል፤ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንን ከነሙሉ ክብሯ ለማሻገር እንችል ዘንድ ቡራኬዎና ጸሎትዎ አይለየን…" ሲሉ በመንፈሳዊ የልጅነት አክብሮት ጠይቀዋል።

ብፁዕ ወቅዱስነታቸውም "ዘመነ ማርቆስ ከነበርካታ ችግሮቹ በማለፉ እግዚአብሔርን እናመሰግናለን፤ የጀመርነውን ዘመነ ሉቃስ መልካም ዓመት ያድርግልን፤ እናንተም ይህንኑ አስባችሁ እንኳን አደረስዎ ለማለት በመቅረባችሁ አመሰግናለሁ፤ የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤትና የውጭ ጉዳይ መምሪያ ሰላም፣ ፍቅር፣ መተሳሰብና መከባበር የሰፈነበት መሆኑ የሚያስደስት ሲሆን በአዲሱ ዘመንም ይህንኑ የሥራ መንፈስ አጠናክራችሁ በመቀጠል፤ የተሰጣችሁን ታላቅ የቤተክርስቲያን ሓላፊነት በሐቀኝነት፣ በቅንነትና በታማኝነት እየተናበባችሁ ልትወጡ ይገባል…" ሲሉ የሥራ መመሪያ ሰጥተዋል።

የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት እና የውጭ ጉዳይ መምሪያ ሀገር አቀፍ እና ዓለም አቀፍ ዐበይት ተግባራት የሚከናወኑባቸው ታላላቅ የቅድስት ቤተክርስቲያናችን ተቋማት መሆናቸው ይታወቃል።
ያረካል አድማሱ

© EOTCTV

በሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት በሶሮ ወረዳ ቤተክህነት የጊምቢቹ መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያንና የጃጁራ ደብረ መንክራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን 51 ሰልጣኞች በ...
13/09/2026

በሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት በሶሮ ወረዳ ቤተክህነት የጊምቢቹ መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያንና የጃጁራ ደብረ መንክራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን 51 ሰልጣኞች በደቡብ አፍሪካ ያሉ አባቶችና ወንድሞች ድጋፍ ለአንድ ወራት ሲሰጥ የነበረው የክረምት መንፈሳዊ ኮርስ ሰልጣኞች ስልጠና የምርቃት መርሐግብር ተካሄደ።

++++++++++++++++++++++++++
መስከረም 3 ቀን 2019ዓ.ም (ብሕንሳ ሚዲያ ሆሣዕና)
++++++++++++++++++++++++++

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት በሶሮ ወረዳ ቤተክህነት የጊምቢቹ መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያንና የጃጁራ ደብረ መንክራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን 51 ሰልጣኞች በደቡብ አፍሪካ ያሉ አባቶችና ወንድሞች ድጋፍ ለአንድ ወራት ሲሰጥ የነበረው የክረምት መንፈሳዊ ኮርስ ሰልጣኞች ስልጠና የምርቃት መርሐግብር በሶሮ ወረዳ ቤተክህነት በጃጁራ ደብረ መንክራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ተካሂዷል።

በመርሐ ግብሩ ላይ ላዕከ ወንጌል ቀሲስ ስብሐቱ በፍቃዱ የወረዳ ቤተክህነቱ ዋና ሥራአስኪያጅ፣መምህር ተመስጌን ገብረ ስላሴ መምህር ተሻለ ማቴዎስ ፣ መምህር ምስጋኑ በየነ፣ተመራቂ ተማሪዎች፣ምዕመናንና ምዕመናት ተገኝተዋል።

በሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት በአመካ ወረዳ ቤተክህነት በኢቢቾ ጽርሐ አርያም ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን እና በጊቤ ወረዳ ቤተክህነት ሶዳ ደብረ ምህረት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን 98 ሰ...
13/09/2026

በሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት በአመካ ወረዳ ቤተክህነት በኢቢቾ ጽርሐ አርያም ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን እና በጊቤ ወረዳ ቤተክህነት ሶዳ ደብረ ምህረት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን 98 ሰልጣኞች በደቡብ አፍሪካ ያሉ አባቶችና ወንድሞች ድጋፍ ለአንድ ወራት ሲሰጥ የነበረው የክረምት መንፈሳዊ ኮርስ ሰልጣኞች ስልጠና የምርቃት መርሐግብር ተካሄደ።

++++++++++++++
መስከረም 3 ቀን 2019ዓ.ም (ብሕንሳ ሚዲያ ሆሣዕና)
++++++++++++++++++++++++++

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት በአመካ ወረዳ ቤተክህነት በኢቢቾ ጽርሐ አርያም ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን እና በጊቤ ወረዳ ቤተክህነት ሶዳ ደብረ ምህረት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን 98 ሰልጣኞች በደቡብ አፍሪካ ያሉ አባቶችና ወንድሞች ድጋፍ ለአንድ ወራት ሲሰጥ የነበረው የክረምት መንፈሳዊ ኮርስ ሰልጣኞች ስልጠና የምርቃት መርሐግብር በየአድባራቱ ተካሂዷል።

በመርሐ ግብሩ ላይ መምህር ሕይወት ፎራ የስልጠናው አስተባባሪ ኮሚቴዎች ፀሐፊ፣ሊቀ ኅሩያን ቀሲስ አባይነህ አድማሱ፣ ዲያቆን ኢያሱ ደጉ፣መምህር ገዘኻኝ እሸቱ፣ተመራቂ ተማሪዎች፣ምዕመናንና ምዕመናት ተገኝተዋል።

በሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት በሚሻ ወረዳ ቤተክህነት በዋስገበታ ደብረ በረከት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን 87 ሰልጣኞች በደቡብ አፍሪካ ያሉ አባቶችና ወንድሞች ድጋፍ ለአንድ ወራት ሲሰጥ ...
13/09/2026

በሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት በሚሻ ወረዳ ቤተክህነት በዋስገበታ ደብረ በረከት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን 87 ሰልጣኞች በደቡብ አፍሪካ ያሉ አባቶችና ወንድሞች ድጋፍ ለአንድ ወራት ሲሰጥ የነበረው የክረምት መንፈሳዊ ኮርስ ስልጣኖች ስልጠና የሀገረ ስብከቱ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማ/መምሪያ ሃላፊ በተገኙበት የምርቃት መርሐግብር ተካሄደ።

++++++++++++++++++++++++++
መስከረም 3 ቀን 2019ዓ.ም (ብሕንሳ ሚዲያ ሆሣዕና)
++++++++++++++++++++++++++

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት በሚሻ ወረዳ ቤተክህነት በዋስገበታ ደብረ በረከት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን 87 ሰልጣኞች በደቡብ አፍሪካ ያሉ አባቶችና ወንድሞች ድጋፍ ለአንድ ወራት ሲሰጥ የነበረው የክረምት መንፈሳዊ ኮርስ ስልጣኞች ስልጠና የሀገረ ስብከቱ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማ/መምሪያ ሃላፊ መጋቤ ሃይማኖት ቀሲስ ወርቃፈራው ስዮም በተገኙበት የምርቃት መርሐግብር በሚሻ ወረዳ ቤተክህነት በዋስገበታ ደብረ በረከት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ተካሂዷል።

በዕለቱም በክቡር መጋቤ ሃይማኖት ቀሲስ ወርቃፈራው ስዮም ትምህርት የተሰጠ ሲሆን፣በስልጠናው ዙርያ ሰፊ ማብራርያ በመስጠት፣ይህ ስልጠና በገጠሪቱ ቤተክርስቲያን የወንጌል አገልግሎት ተደራሽ እንዲሆን የብፁዕነታቸው የዘውትር አባታዊ መመሪያ መሆኑን ገልጸው፣ የወንጌል አገልግሎት በገጠሪቷ ቤተክርስቲያን እንዲስፋፋና ተደራሽ እንዲሆን፣ ተቀማጭነታቸው በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ አባቶችና ወንድሞች አመስግነዋል ።
በመርሐ ግብሩ ላይ ክቡር መጋቤ ሃይማኖት ቀሲስ ወርቃፈራው ስዮም፣ መ/ር ዳንኤል አበበ የደቀ መዛሙርቱ አሰልጣኝ ፣ጌታቸው ኤርጉዶ የደብሩ ሰበካ ጉባኤ ም/ ሰብሰቢ፣ተመራቂ ተማሪዎች፣ምዕመናንና ምዕመናት ተገኝተዋል።

13/09/2026

የክረምት መንፈሳዊ ሥልጠና ለአራት ተከታታይ ዓመታት የተከታተሉ የዋስገበታ ደብረ በረከት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ተመራቂ ደቀመዛሙርት

+++++++++++++++++++++
መስከረም 3 ቀን 2019 ዓ.ም(ብሕንሳ ሚዲያ ሆሣዕና )
+++++++++++++++++++++

በሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት በሌሞ ወረዳ ቤተክህነት በሹርሞ ደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን 26 ሰልጣኞች በደቡብ አፍሪካ ያሉ አባቶችና ወንድሞች የበጀት ድጋፍ ለአንድ ወራት ሲሰ...
13/09/2026

በሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት በሌሞ ወረዳ ቤተክህነት በሹርሞ ደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን 26 ሰልጣኞች በደቡብ አፍሪካ ያሉ አባቶችና ወንድሞች የበጀት ድጋፍ ለአንድ ወራት ሲሰጥ የነበረው የክረምት መንፈሳዊ ኮርስ ስልጣኖች ስልጠና የሀገረ ስብከቱ ምክትል ስራ አስኪያጅ በተገኙበት የምርቃት መርሐግብር ተካሄደ።

++++++++++++++
መስከረም 3 ቀን 2019ዓ.ም (ብሕንሳ ሚዲያ ሆሣዕና)
++++++++++++++

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት በሌሞ ወረዳ ቤተክህነት በሹርሞ ደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን በደቡብ አፍሪካ ያሉ አባቶችና ወንድሞች የበጀት ድጋፍ ለአንድ ወር ሲሰጥ የነበረው የክረምት መንፈሳዊ ኮርስ ስልጣኖች ስልጠና ፣የሀገረስብከቱ ምክትል ስራአስኪያጅ ክቡር መጋቤ ጥበብ ቀሲስ ወርቁ ተክሌ በተገኙበት የምርቃት መርሐግብር በሌሞ ወረዳ ቤተክህነት በሹርሞ ደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ተካሂዷል።

በዕለቱም በክቡር መጋቤ ጥበብ ቀሲስ ወርቁ ተክሌ ትምህርት የተስጠ ሲሆን፣በስልጠናው ዙርያ ሰፊ ማብራርያ በመስጠት፣ይህ ስልጠና በገጠሪቱ ቤተክርስቲያን የወንጌል አገልግሎት ተደራሽ እንዲሆን የብፁዕነታቸው የዘውትር አባታዊ መመሪያ መሆኑን ገልጸው፣ የወንጌል አገልግሎት በገጠሪቷ ቤተክርስቲያን እንዲስፋፋና ተደራሽ እንዲሆን፣ ተቀማጭነታቸው በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ አባቶችና ወንድሞች አመስግነዋል ።

ክቡር ስራአስኪያጁ በመልዕክታቸው ለዚህ ስልጠና መሳካት ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የሀዲያና ስልጤ ሀገረስብከት ሊቀ ጳጳስ የአንበሳውን ድርሻ እንደተወጡ በመግለጽ ፣እንዲሁም መቀመጫውን በደቡብ አፍሪካ ያሉ አባቶችና ወንድሞች ፣ በዚህ መርሐ ግብር ላይ የተሳተፉትን ሰልጣኞችንም አሰልጣኞችንም በሙሉ በማመስገን መርሐግብሩ በጸሎት ፍጻሜውን አግኝቷል።

በዕለቱ በመልአከ ብርሃን ቀሲስ አለማየሁ ተሰማ የሹርሞ ደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ አስተዳዳሪ፣ለተመራቂ ተማሪዎች ሰርተፍኬት የሰጡ ሲሆን ፣በአጠቃላይ በወሰዱት ኮርስ ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡት ሽልማትና የብፁዕነታቸውን አባታዊ ቡራኬና መልዕክት በመጋቤ ጥበብ ቀሲስ ወርቁ ተክሌ የሀገረስብከቱ ዋና ስራአስኪያጅ ተላልፏል።

በመርሐ ግብሩ ላይ ክቡር መጋቤ ጥበብ ቀሲስ ወርቁ ተክሌ፣የሀገረስብከቱ ምክትል ስራአስኪያጅ፣ በመልአከ ብርሃን ቀሲስ አለማየሁ ተሰማ የሹርሞ ደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ አስተዳዳሪ፣መ/ር ተክለኢየሱስ ኤርቃሎ የደብሩ ስብከተ ወንጌል ክፍል ኃላፊ ፣አሰልጣኞችና ተመራቂ ተማሪዎች ተገኝተዋል።

የክረምት መንፈሳዊ  ሥልጠናን ለአምስት ተከታታይ ዓመታት የተከታተሉ የሌራ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን እና ቀጫ ደብረ ኃይል ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ደቀመዛሙርት ተመረቁ።+...
13/09/2026

የክረምት መንፈሳዊ ሥልጠናን ለአምስት ተከታታይ ዓመታት የተከታተሉ የሌራ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን እና ቀጫ ደብረ ኃይል ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ደቀመዛሙርት ተመረቁ።

+++++++++++++++++++++++++++++++++++++
መስከረም 3 ቀን 2019 ዓ.ም(ብሕንሳ ሚዲያ/ሆሳዕና )
++++++++++++++++++++++++++++++++

በሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት በምዕራብ አዘርነት በርበሬ ወረዳ ቤተክህነት በሚገኙት የሌራ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስና የቀጫ ደብረ ኃይል ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን በየክረምቱ ለሁለት ወራት እንደ ዘንድሮ ለአንድ ወር ለአምስት ተከታታይ ዓመታት ትምህርትና ሥልጠና ሲከታተሉ የቆዩ ደቀመዛሙርት ተመርቀዋል።

የሥልጠናው ዋና አስተባባሪና የሀገረ ስብከቱ ዋና ፀሐፊ ሊቀ ትጉሃን ትግስቱ ሀንዳጉ ይህ መርሐግብር በብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ አባታዊ መመሪያ ሰጪነት የዛሬ 2014 ዓ/ም በደቡብ አፍሪካ ደርባን ማኅበረ ቅዱስ ገብርኤል የተጀመረ መሆኑን አንስተው እስካሁን በሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት በ22 ማዕከላት ለአራት ተከታታይ ዓመታት በየክረምቱ ለሁለት ወራት በትጋት፣ በትዕግሥትና በጽናት የተከናወነ የትምህርትና የሥልጠና ጉዞ ውጤት መሆኑ ተገልጿል።

ዘንድሮም በ22 የተለያዩ የሥልጠና ማዕከላት ይህ የትምህርት ጉዞ የእውቀት ማግኘት ብቻ ሳይሆን፣ የሥነ ምግባር፣ የመንፈሳዊ ዕድገትና የአገልግሎት ዝግጅት ጉዞ መሆኑ የተጠቆመ ሲሆን፣ ተመራቂ ደቀመዛሙርቱ የተማሩትን እውቀት በትሕትና፣ በታማኝነትና በትጋት ለቤተክርስቲያንና ለማኅበረሰብ እንዲያውሉ መልእክት አስተላልፈዋል።

በሌራ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን 26 ደቀመዛሙርት እና በቀጫ ደብረ ኃይል ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን 13 ደቀመዛሙርት በድምሩ 39 ደቀመዛሙርት በሌራ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን በተካሄደው መርሐ ግብር ተመርቀዋል።

ተመራቂ ደቀመዛሙርቱ በአራት ተከታታይ ዓመታት በየክረምቱ ለሁለት ወራት በተካሄደው ሥልጠና በመሳተፍ በትምህርትና በመንፈሳዊ ዝግጅት የቆዩ ሲሆን፣ የዛሬው ምረቃ የዚህን የትምህርት ጉዞ ውጤት የሚያሳይ መርሐ ግብር መሆኑ ተገልጿል።

የሥልጠናው መርሐ ግብር በየዓመቱ መቀጠሉ ደቀመዛሙርቱ በእውቀትና በሥነ ምግባር እንዲጠናከሩ የሚያግዝ መሆኑም የሥልጠና አስተባባሪዎች ለሚዲያ ክፍላችን ገልጸዋል።

በዕለቱም የሀገረ ስብከቱ ዋና ፀሐፊ ሊቀ ትጉሃን ትግስቱ ሀንዳጎ፣ የምዕራብ አዘርነት ወረዳ ቤተክህነት ዋና ሥራአስኪያጅ መጋቤ ሃይማኖት ቀሲስ መድኀን መና፣የደብሩ አስተዳደሪ ቀሲስ እሸቱ ሀ/ማርያም፣የሁለት ማዕከላት አሰልጣኞች፣ሠልጣኞች፣አባቶች ካህናት፣ዲያቆናት፣ ምዕመናንና ምዕመናት ተገኝተዋል ።

በሀዲያና ስልጤ ሀገረ በአመካ ወረዳ ቤተክህነት በጌጃ ደብረ ኃይል ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን በደቡብ አፍሪካ በደርባን ከተማ በሚገኙ አባቶች አስተባባሪነት በሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት ከ2...
13/09/2026

በሀዲያና ስልጤ ሀገረ በአመካ ወረዳ ቤተክህነት በጌጃ ደብረ ኃይል ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን በደቡብ አፍሪካ በደርባን ከተማ በሚገኙ አባቶች አስተባባሪነት በሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት ከ22ቱ የሥልጠና ማዕከላት አንዱ የሆነው በጌጃ ደብረ ኃይል ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን 52 ሠልጣኞች እጅግ ደስ በሚል ሁኔታ ተመርቀዋል።

በመርሐግብሩም የአመከ ወረዳ ቤተክህነት ፀሐፊ ቀሲስ መንግስቱ ኃይሌ ፣የደቀመዛሙርት አሰልጣኝ መ/ር ኤፍሬም ካሣ፣አባቶች ካህናት፣ዲያቆናት፣ተመራቂ ደቀመዛሙርት፣ምዕመናንና ምዕመናት ተገኝተዋል ።

++++++++++++
መስከረም 3 ቀን 2019 ዓ.ም (ብሕንሳ ሚዲያ ሆሣዕና )
++++++++++++

ፎቶ :ተመስገን

Address

Hossana

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ብሕንሳ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to ብሕንሳ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት ሚዲያ:

Shortcuts

Share