02/07/2026
በሀዲያ ምድር ላይ በአስደናቂ ሁኔታ የእግዚአብሔር አሰራር በሚደንቅ መንገድ ከታየበት ቤተክርስቲያን መካከል አንዷ የጊምቢቹ ሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን ናት በ1980ዎቹ አከባቢ በሀድያ ምድር "ሀ" ብሎ የሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን የተጀመረው በዚሁ በጊምቢቹ ከተማ ነበር ከዚያ በመቀጠል ነው የሆሳዕና ሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን የተተከለችው፤ ቤተክርስቲያኗ ለሀድያ ምድር ሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን በሙሉ እናት ናት። በወቅቱ በዚህች የጊምቢቹ የሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን ላይ ለማመን የሚከብዱ ተዓምራት ይሆን ነበር ሰዎች ገና የቼርቹ በር ስደርሱ አንዳንዶች በመንፈስ ቅዱስ ተሞልቶ ሰዎች ተሸክሞ ወደ ውስጥ ያስገቡ ነበር፤ አጋንንት ያለባቸው ሰዎች ማንም ሳያወራ ገና በር ጋ ስደርሱ መንፈሱ ይጮኽ ነበር፤ ብዙ ሰዎች ከጨለማ ወደ ብርሃን መጥቷል፤ በጣም ብዙ አንካሶች፣ ዕውሮች፣ መስማትና ማውራት የማይችሉ ሰዎች ይፈወሱም ነበር።
ቤተክርስቲያን ከእሁድ መደበኛ ፕሮግራም ሌላ ከሰኞ እስከ አርብ የማለዳ ጸሎት አላት በዚህ ፕሮግራም ሰው ለማካፈል ገና ፕሮግራሙ ሳይጀምር ከሌሊቱ10:00 መጥቶ አዳራሹን ሞልቶ ከዚያም አልፎ በዚያ ሌሊት በውጭ ተንበርክኮ ፕሮግራም መሪ ሳያቆም አስደናቂ የጸሎት ጊዜ ይሆን ነበር። ማለዳ ማለዳ የሚከፈቱ መዝሙሮች ከአማኞች አልፎ ሌሎችም ጭምር ሸምድዶ እንዲዘምሩ ምክንያት ሆኖም ነበር።
ወደዚያ ቤተክርስቲያን እግር ጎራ ብሎ በመንፈስ ቅዱስ ሳይሞላ ማውጣት በጭራሽ አይታሰብም።
በተጨማሪ እሮብ የፈውስ ፕሮግራም አለ በዚህ ፕሮግራም ላይ የሚገርመው ሰው ከተለያዩ የሃገርቱ አከባቢዎች ይመጡ እንደነበር ዛሬም በሰዓቱ የነበሩ የቤተክርስቲያኑ አማኞች ይነገራሉ ድንቅ የሆነ የእግዚአብሔር እጅ ይሰራ ነበር። በነገራችን ላይ በኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ታሪክ በአስደናቂ ጸጋ ከተገለጡ አገልጋዮች መሃል አንዱ የነበረው አገልጋይ አለምነህ ጀምበሩ ተደጋጋሚ ወደዚህ ቤተክርስቲያን ይመጣ ነበር ያንንም ያደረገው በቤተክርስቲያኑ የነበረው የእግዚአብሔር ክብር ነበር።
ከዚህ ቤተክርስቲያን ዛሬ በተለያዩ ዓለማት ሆነ በኢትዮጵያ እያገለገሉ ያሉ ድንቅ አገልጋዮች ተነስተዋል ቤተክርስቲያኗ ያደረገችው አስደናቂ ስራ ዛሬም ምስክር ሆኖ ይኖራል።
እስቲ ስለዚህች ቤተክርስቲያን ያለችውን ሀሳብ ኮሜንት ላይ ጻፉ በተለይ ስለ ቤተክርስቲያኗ ትዝ የሚላችሁን ነገር