WCU Apostolic Church fellowships

WCU Apostolic Church fellowships Obey Acts 2%38

  🙌ከFeb/2025 እስከ March/2026 በአንድ አመት ውስጥ በኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን፦81,369 አዳዲስ ነፍሳት ለኃጢአታቸው ስርየት በኢየሱስ ስም ተጠምቀዋል!5,383 ነፍሳት...
14/05/2026

🙌

ከFeb/2025 እስከ March/2026 በአንድ አመት ውስጥ በኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን፦

81,369 አዳዲስ ነፍሳት ለኃጢአታቸው ስርየት በኢየሱስ ስም ተጠምቀዋል!

5,383 ነፍሳት በንስሐ ወደ አባታቸው ጉያ ተመልሰዋል!

54,021 ነፍሳት ለመጀመሪያ ጊዜ በመንፈስ ቅዱስ ተሞልተው በአዲስ ቋንቋ ተናግረዋል!

53,177 ሰዎች ከተለያየ ደዌና በሽታ ተፈውሰዋል!

281 አዳዲስ አጥቢያዎች በሀገረስብከቱ ውስጥ ተከፍተዋል።

ይህን ሁሉ ላደረገው ለአምላካችን ለኢየሱስ ክብርና ምስጋና ውዳሴና ኃይል ከዘላለም እስከ ዘላለም ለእርሱ ይሁን። አሜን!

"ይህን የሠራና ያደረገ፥ ትውልድንም ከጥንት የጠራ ማን ነው? እኔ እግዚአብሔር፥ ፊተኛው በኋላኞችም ዘንድ የምኖር እኔ ነኝ።" (ት/ኢሳ 41፥4)

ምንጭ፦ በ55ኛው AWCF አመታዊ ጉባኤ ላይ የእምነት አባታችን ቢሾፕ ደጉ ከተናገሩት የተወሰደ።

08/05/2026
በእግዚአብሔር ቤት የተተከሉ በምሥጋና ያብባሉ!” (መዝ 92:13)​✍🏽በመጀመሪያ በሁሉ ላይ ጌታ በሆነው በኢየሱስ ክርስቶስ ፍጹም ሰላም፣ ፍቅርና ጸጋ በልባችሁና በቤታችሁ ላይ አብዝቶ እንዲበ...
08/05/2026

በእግዚአብሔር ቤት የተተከሉ በምሥጋና ያብባሉ!” (መዝ 92:13)
​✍🏽በመጀመሪያ በሁሉ ላይ ጌታ በሆነው በኢየሱስ ክርስቶስ ፍጹም ሰላም፣ ፍቅርና ጸጋ በልባችሁና በቤታችሁ ላይ አብዝቶ እንዲበዛ የሁልጊዜም ቅዱስ ምኞታችን ነው።

​ ለአራት እና ለአምስት ዓመታት በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ እና በአከባቢዋ አጥቢያ ቤተክርስቲያን ጥላ ስር በታማኝነት፣ በቅንነትና በፍቅር ሲያገለግሉ የቆዩ የቤተክርስቲያናችን እንቁዎች፤ እነሆ ዛሬ የትምህርት ዘመናቸውን በድል አጠናቅቀው ለታላቅ የምርቃት ማዕረግ በቅተዋል።

​ሆሳዕና እናት ቤተክርስቲያን ለነዚህ የፍቅር ፍሬዎቿ ያላትን ጥልቅ አድናቆት የምትገልጽበት፣ የአገልግሎት ድካማቸውን በክብር የምታክምበትና በቀጣይ የሕይወት ጉዟቸው የእግዚአብሔር ረድኤት እንዳይለያቸው የምርቃት ጸሎት የምታደርግበት ታላቅ የ "Well-Go" የአሸኛኘት ፕሮግራም በታላቅ መንፈሳዊ ዝግጅት በሆሳዕና እናት ቤተክርስቲያን ቅጥር ግቢ በድምቀት ይካሄዳል።
​ ይህ ፕሮግራም የአገልጋይነት ክብር የሚታይበት፣ ልብ የሚነኩ ምስክርነቶች የሚሰሙበት፣ በመንፈሳዊ ዝማሬዎች የምንታደስበትና ለቀጣይ ተረካቢዎች የሕይወት አርአያነት የሚተላለፍበት ልዩ የሰማያዊ በረከት ድግስ ነው።
​ በመሆኑም፣ እያንዳንዳችን በዚህ ታላቅ የበረከት ድግስ ላይ ተገኝተን ለተመራቂ ተማሪዎቻችን የፍቅር አሸኛኘት እንድናረግላቸውና በምርቃታቸው ደስታ ላይ አብረን መካፈል እንድችል በክርስቶስ ፍቅር ተጋብዘናል።
​“ኑ! የምረቃቸውን ደስታ አብረን እናክብር፤ በጸሎትና በምርቃት እንሸኛቸው!
የፊታችን ግንቦት 2 ቀን 2018 ዓመተ ምህረት፤ዕለተ እሁድ ከቀኑ 8:00 ሰዓት ጀምሮ በታላቅ መንፈሳዊ በረከት በሆሳዕና እናት ቤተክርስትያን ቅጥር ግቢ ይካሄዳል..... ሁላችንም በሰዓቱ ተገኝተን የክብሩ ተካፋይ እንድንሆን በክርስቶስ ፍቅር እናሳስባለን።
.... ጅማሬህ ታናሽ ቢሆንም እንኳ ፍጻሜህ እጅግ ይበዛል።
​ የዋቻሞ ዩንቨርስቲ ሐዋርያዊት ቤተክርስትያን የተማርዎች ህብረት አገልግሎት....

" ወደ እርሱ ቅረቡ ያበራላችሁማል፥ ፊታችሁም አያፍርም።"
(መዝሙረ ዳዊት 34:5)

💝
08/04/2026

💝

Address

Hosaena

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when WCU Apostolic Church fellowships posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share