Full Gospel Believers' Church, Hawassa

Full Gospel Believers' Church, Hawassa Welcome to the official page of Hawassa Full Gospel Believers' Church. Talk to the Church, put your prayer requests and be part of it.

01/05/2026

ሙዚቀኞቹ ክፍል 2
ዛሬ ከቀኑ 9 ሰዓት
በሐዋሳ ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን ዩቱብ ቻነል

የወንድሞቻቸን የፍሬሁን ኃይለየሱስ እና የድሉ መርዶኪዮስ ድንቅ የሕይወት ጉዞ የምንዳስስበት የአውደ ሕይወት ክፍል 2 ይለቀቃል። ይጠብቁን!

በዚህ ቃል ተጽናኑመጋቢ ዘሩባል ሙሉጌታ በሀዋሳ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን ሚያዝያ 18/2018 ዓ.ም እሁድ ጥዋት በሁለት ፈረቃ የተካሄደው የጉባኤ አምልኮ ፕሮግራም በዕለቱ በነበረው ...
26/04/2026

በዚህ ቃል ተጽናኑ
መጋቢ ዘሩባል ሙሉጌታ

በሀዋሳ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን ሚያዝያ 18/2018 ዓ.ም እሁድ ጥዋት በሁለት ፈረቃ የተካሄደው የጉባኤ አምልኮ ፕሮግራም

በዕለቱ በነበረው የቃል አገልግሎት መጋቢ ዘሩባል ሙሉጌታ 1ተሰ.1፤10 1ተሰ 2:1 1ተሰ 3: 12-13 1ተሰ 4: 13-18 1ተሰ 5:23 ያለውን ክፍል መሰረት በማድረግ “በዚህ ቃል ተጽናኑ” በሚል ርዕስ ቀጥለው በቀረቡት ነጥቦች ላይ የእግዚአብሔርን ቃል አስተምረዋል።

1ተሰ.1፤9-10
ቁጥር 9 እና 10ን አያይዘን ስንመለከታቸው የክርስትናን ሙሉ ጉዞ ወይም "የለውጥ እርምጃዎችን" ቁልጭ አድርገው ያሳዩናል። ጳውሎስ በእነዚህ ሁለት ጥቅሶች ውስጥ የእውነተኛ አማኝን ማንነት በሦስት ደረጃዎች ያስቀምጠዋል። እነዚህም መመለስ፣ ማገልገል እና መጠባበቅ ናቸው፡

1ኛ ተሰ 2:19
ተስፋችን ወይስ ደስታችን ወይስ የትምክህታችን አክሊል ማን ነው? በጌታችን በኢየሱስ ፊት በመምጣቱ እናንተ አይደላችሁምን?

ጥቅሱን ከቀደሙት (1፡9-10) ጋር ስናያይዘው፡
-በምዕራፍ 1 ላይ፡ አማኞቹ ጌታን እንዲጠባበቁ መከራቸው።
-በምዕራፍ 2 ላይ፡ እርሱ ደግሞ ጌታ ሲመጣ እነርሱን እንደ አክሊል ይዞ ለመቅረብ እንደሚናፍቅ ገለጸ።
ባጭሩ፡ ለአንድ ክርስቲያን ከእግዚአብሔር ቀጥሎ ትልቁ ደስታውና ክብሩ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት አብሮአቸው የሚጓዙት ወንድሞቹና እህቶቹ ናቸው።

1ተሰ 3:12-13
ጳውሎስ አማኞች ለጌታ ምፅዓት እንዴት መዘጋጀት እንዳለባቸው በሁለት ዋና ዋና ነገሮች ያስቀምጠዋል፡ ፍቅር እና ቅድስና። እነዚህን ሁለት ቁልፍ ነጥቦች እንደሚከተለው እንመልከታቸው፡፡

1. የፍቅር መብዛት ጳውሎስ "ፍቅራችሁን ያብዛ ይጨምርም" ሲል በሁለት አቅጣጫ ነው፡ እርስ በእርሳችሁ፡ በቤተክርስቲያን ውስጥ ያለ ፍቅር። ለሁሉም የሚሆን፡ ከቤተክርስቲያን ውጭ ላሉት (ለማያምኑት ጭምር) የሚተርፍ ፍቅር።
2. የልብ መጽናትና ቅድስና ፍቅር ለምን ያስፈልጋል? ለሚለው ጥያቄ መልሱ እዚህ ይገኛል። ፍቅር ልብን ለቅድስና ያዘጋጃል።

የታላቁ ቀን ተስፋ ጥቅሱ የሚያበቃው "ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከቅዱሳኑ ሁሉ ጋር ሲመጣ" በማለት ነው።
ጳውሎስ በየምዕራፉ መጨረሻ ላይ (ምዕ. 1፣ 2 እና 3) የጌታን መምጣት መጥቀሱ ትልቅ ትርጉም አለው። የአሁኑ ፍቅራችንና ቅድስናችን ትርጉም የሚኖረው በዚያ ቀን በጌታ ፊት ስንቆም ነው።

1ተሰ.4፤13-18
1ኛ ቆሮ 15፤51-52

በነዚህ ጥቅሶች ላይ ሐዋሪያው ጳውሎስ ልንጽናናበት ስለምንችልበት ስለ ጌታችን፣ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዳግም ምጽአት የጻፈውን እንገኛለን።
ይህ ክፍል በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስለ "ንጥቀት" (The Rapture) እና ስለ ክርስቲያኖች ተስፋ እጅግ ግልጽና ዝርዝር መረጃ የሚሰጥበት ታላቅ ስፍራ ነው። ጳውሎስ ይህንን የጻፈው የሚወዷቸውን ሰዎች በሞት አጥተው ለሚያዝኑና "የሞቱት ቅዱሳን ዕጣ ፈንታ ምን ይሆን?" ብለው ለሚጨነቁ የተሰሎንቄ አማኞች ነው።

1.የሞት አዲስ ትርጉም፡ "መተኛት" (ቁጥር 13-14) አንቀላፍተው ያሉቱ፡ ጳውሎስ ለክርስቲያን ሞትን "መተኛት" (Sleep) በማለት ይጠራዋል። ይህ የሚያሳየው ሞት የመጨረሻ አለመሆኑንና የመነሻ ጊዜ እንዳለው ነው። ተስፋ ያለው ሐዘን፡ ክርስቲያን አያዝንም ማለት አይደለም (ያዝናል)፤ ነገር ግን እንደ ዓለም ሰዎች "ተስፋ ቢስ" ሆኖ አያዝንም።
መሠረቱ፡ ተስፋችን የተመሠረተው በኢየሱስ ሞትና ትንሳኤ ላይ ነው። እርሱ ስለተነሳ፣ በእርሱ ያመኑትም እንደሚነሱ እርግጠኞች ነን።

2. የጌታ ዳግም ምጽአት ቅደም ተከተል
ጌታ ሲመጣ የሚከናወኑ ክስተቶች በቅደም ተከተል ተቀምጠዋል፡
የጌታ መውረድ፡ ጌታ ራሱ በታላቅ ድምፅ (በትእዛዝ፣ በመላእክት አለቃ ድምፅና በእግዚአብሔር መለከት) ከሰማይ ይወርዳል።
የሙታን ትንሳኤ፡ በክርስቶስ ያመኑና የሞቱት አስቀድመው ይነሳሉ።
የሕያዋን መለወጥ፡ በዚያን ጊዜ በምድር ላይ በሕይወት ያሉ አማኞች ሳይቀድሙ ከትንሳኤው በኋላ ይከተላሉ።
መነጠቅ (Rapture): ሁለቱም ወገኖች (ከመቃብር የተነሱትና በሕይወት ያሉት) በአንድነት ጌታን በአየር ለመቀበል በደመና ይነጠቃሉ።
የዘላለም አንድነት፡ "ሁልጊዜ ከጌታ ጋር እንሆናለን" የሚለው ታላቅ የምስራች ይፈጸማል።

3. "ጌታን በአየር ለመቀበል" (ቁጥር 17)
እዚህ ጋር "መቀበል" የሚለው ቃል ጥንታዊ ትርጉም አለው። በአንድ ሀገር ንጉሥ ወይም ታላቅ ሰው ወደ አንዲት ከተማ ሲመጣ፣ የከተማዋ ነዋሪዎች ከከተማው ወጥተው ንጉሡን በአክብሮት ይቀበሉታል፤ ከዚያም አብረውት ወደ ከተማዋ ይገባሉ።
እኛም ጌታን በአየር የምንቀበለው ለዘላለም ከእርሱ ጋር ለመሆን ወደ ቤታችን (መንግሥተ ሰማያት) አብረን ለመግባት ነው።

4. የተጽናኑበት "ቃል" (ቁጥር 18)
ጳውሎስ "በዚህ ቃል ተጽናኑ" ይላል።
መጽናኛው "ሞት አያገኘንም" የሚል ሳይሆን፣ "ሞት ቢመጣም እንኳ ጌታ ሲመጣ እንነሳለን፣ እንገናኛለን፣ ከጌታም ጋር ለዘላለም እንኖራለን" የሚለው ነው። እነዚህ ጥቅሶች ከታላቁ የሐዋርያው ጳውሎስ መልእክት 1ኛ ቆሮንቶስ ምዕራፍ 15 የተወሰዱ ጥልቅ መንፈሳዊ ትርጉም ያላቸው ቃላት ናቸው። ይህ ክፍል በተለይ ስለ ሙታን ትንሣኤ፣ ስለ ክርስቲያናዊ ተስፋ እና ሞት በክርስቶስ ድል ስለመነሳቱ የሚያበስር የምስራች ነው።

የጥቅሶቹን ዋና ዋና ነጥቦች በዚህ መልኩ ማየት ይቻላል፡-

1. የለውጥ ምስጢር (ቁጥር 51-52)
ጳውሎስ "ምስጢር" የሚለው ቃል ቀደም ብሎ ያልታወቀ አሁን ግን የተገለጠ እውነትን ለማሳየት ነው። "ሁላችን አናንቀላፋም" ሲል ሁሉም አማኞች ክርስቶስ ሲመጣ ሞተው አይገኙም፤ በሕይወት ያሉ ይኖራሉ። "በቅጽበተ ዓይን" የሚለው አገላለጽ ለውጡ በጣም ፈጣንና ድንገተኛ መሆኑን ያሳያል። የሚለወጠው ግን ለባሹ (ሰውነታችን) እንጂ ማንነታችን አይደለም። ምድራዊውና ደካማው አካላችን ወደ ሰማያዊና ብርቱ አካልነት ይለወጣል።

2. የማይበሰብስ ማንነት (ቁጥር 53-54)
እዚህ ጋር ጳውሎስ "ሊለብስ ይገባዋል" የሚል ጠንካራ ቃል ይጠቀማል። ምድራዊ አካላችን ለበሽታ፣ ለድካም እና ለሞት (ለሙስና) የተጋለጠ ነው። ትንሣኤ ግን ይህንን ሟች አካል ወደማይሞት፣ በስባሹን አካል ወደማይበሰብስ የመቀየር መለኮታዊ ሂደት ነው። "ሞት ድል በመነሳት ተዋጠ" የሚለው ቃል የሞት ፍጻሜ መድረሱንና በሕይወት መሸነፉን ያውጃል።

3. የሞት መሸነፍ (ቁጥር 55-56)
ጳውሎስ ሞትን እንደ ግዑዝ ነገር ፊት ለፊት ይሞግተዋል። "መውጊያህ የት አለ?" ሞት ቀደም ሲል የሰው ልጅን የሚያስፈራና የሚያቆስል "መውጊያ" ነበረው። የሞት መውጊያ ኃጢአት ነው፡ ሞት ወደ ዓለም የገባው በኃጢአት ምክንያት ነው፤ ኃጢአት ባይኖር ሞት ስልጣን አይኖረውም ነበር። የኃጢአት ኃይል ሕግ ነው፡ ሕግ ባይኖር ኃጢአት መሆኑ አይታወቅም ነበር። ሕግ የሰውን በደለኛነት ቁልጭ አድርጎ ስለሚያሳይ ኃጢአት በሕግ ፊት ኃይል አገኘች።

ቁጥር 57፡ "ነገር ግን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ድል መንሣትን ለሚሰጠን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን።"
ይህ ጥቅስ የድሉን ምንጭ በግልጽ ያሳያል፡-
የድሉ ባለቤት፦ ድሉ የሰው ልጅ በራሱ ጥረት ያመጣው ሳይሆን "እግዚአብሔር የሚሰጠን" ስጦታ ነው።
መካከለኛው፦ ድሉ የተገኘው "በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል" ነው። እርሱ ሞትን ድል አድርጎ ስለተነሳ፣ የእርሱ ትንሣኤ የእኛም ድል ሆነ።
ምላሹ፦ አማኙ ይህንን ታላቅ የምስራች ሲሰማ የሚሰጠው ምላሽ "ምስጋና" ነው። ፍርሃት በምስጋና ተተካ ማለት ነው።

ቁጥር 58፡ "ስለዚህ፥ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፥ ድካማችሁ በጌታ ከንቱ እንዳይሆን አውቃችኋልና የምትጸኑ፥ የማይናወጡም፥ የጌታም ሥራ ሁልጊዜ የሚበዛላችሁ ሁኑ።"
ይህ ጥቅስ "ስለዚህ" በሚል ቃል ይጀምራል። ትንሣኤ ስላለና ሞት ስለተሸነፈ አማኙ ዛሬ በሚኖርበት ሕይወት ውስጥ ሦስት ነገሮችን እንዲያደርግ ይመክራል፡-
መጽናት ፦ በእምነትና በትምህርት ላይ ጸንቶ መቆም። የትንሣኤ ተስፋ ያለው ሰው በጊዜያዊ መከራ አይሸነፍም።
አለመናወጥ (Unshakable)፦ ከውጭ በሚመጣ የሐሰት ትምህርት ወይም የዓለም ተጽዕኖ ፈቀቅ አለማለት።
የጌታን ሥራ ማብዛት ፦ ትንሣኤ ስላለ አገልግሎታችንና ድካማችን "ከንቱ" (ትርጉም የሌለው) አይደለም። በምድር የምናደርገው መልካም ነገር ሁሉ የዘላለም ዋጋ አለው።
ባጭሩ ሲጠቃለል ቁጥር 51-56፦ ነገ የሚሆነውን ተስፋ (የአካል መለወጥና የሞት መሸነፍ) ይነግሩናል።
ቁጥር 57-58፦ ዛሬ ልንኖርበት የሚገባውን ተግባር (ምስጋና፣ ጽናትና አገልግሎት) ያሳዩናል።
ሞት ድል ስለተነሳ፣ በምድር ላይ የምንደክመው ድካም ሁሉ ፍሬ እንዳለው ማወቃችን ትልቅ ብርታት ነው።
ማጠቃለያ ይህ ክፍል ለአማኞች ትልቅ መጽናኛ ነው። ሞት የመጨረሻው ምዕራፍ ሳይሆን ወደ ማይበሰብስ ሕይወት መሻገሪያ መሆኑን ያረጋግጣል። በክርስቶስ ትንሣኤ አማካኝነት የሞት መውጊያ ተሰብሯል፣ መቃብርም ድል ተነስቷል።
Follow Us
◽️ YouTube
https://is.gd/FGBCHawassaYoutube
◽️Facebook
https://fb.me/FGBCHawassa
◽️Instagram
https://ig.me/FGBCHawassa
◽️Telegram
https://t.me/FGBCHawassa

የሀዋሳ ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን
የሚዲያ አገልግሎት
ሚያዝያ 19 /2018 ዓ.ም

እነሆ አምላካችሁ! ወንጌላዊ አበራ ላጲሶ   በሀዋሳ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን ሚያዝያ 11/2018 ዓ.ም እሁድ ጥዋት በሁለት ፈረቃ የተካሄደው የጉባኤ አምልኮ ፕሮግራም በዕለቱ በነበ...
19/04/2026

እነሆ አምላካችሁ!
ወንጌላዊ አበራ ላጲሶ

በሀዋሳ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን ሚያዝያ 11/2018 ዓ.ም እሁድ ጥዋት በሁለት ፈረቃ የተካሄደው የጉባኤ አምልኮ ፕሮግራም

በዕለቱ በነበረው የቃል አገልግሎት ወንጌላዊ አበራ ላጲሶ ትንቢተ ኢሳያስ 40:1-31 ያለውን ክፍል መሰረት በማድረግ “እነሆ አምላካችሁ!” በሚል ርዕስ ቀጥለው በቀረቡት ነጥቦች ላይ የእግዚአብሔርን ቃል አስተምረዋል።

የኢሳያስ መፅሐፍ ማዕካለዊ ሀሳቡ የእግዚአብሔር ምህረትና ፍርድ የሚል ነው። ምዕራፍ 1--39 የእግዚአብሔር ፍርድ፣ ምዕራፍ 40--66 የእግዚአብሔር ምህረት የሚዳስስ ነው።

የምዕራፍ 40 ዋና ሀሳብ ደግሞ የታላቁን አምላክ የእግዚአብሔርን ምህረት ማወጅ ነው፥ ያም ምህረት በአጋልጋዮቹ በኩል የሚመጣ ነው። በፋርስ ንጉስ በቂሮስና በመከረኛው አጋልገይ በመሲሁ በኩል።

የኢሳያስ መፅሐፍ ምዕራፍ 40፣ 31 ቁጥሮች አሉት። በምዕራፉ አምላካችሁ እና እግዚአብሔር የሚል ቃል ተደጋግሞአል።
ምዕራፉን በአራት ከፍለን እንመለከታለን

1. መልዕክቱ(1-8)።

የመልዕክቱ ይዘት ምንድ ነው?
መልዕክቱ ፦ ለእሥራኤል በኃጢአቱዋ ምክንያት ለ70 ዓመታት በባቢሎን የምትቆይበት ጊዜ እንደሚያበቃና የእግዚአብሔርን ምህረት ለመቀበል ማለትም ወደ ሀገራቸው ለመመለስ እንዲዘጋጁ፥ የምሥራች ያበስርላቸዋል። ወቅቱም የአሦር ግዛት አክትሞ የባቢሎን መንግሥት እያንሠራራ ያለበት ወቅት ሲሆን ይሁዳ ገና አልተማረከችም ነበር፥
ምዕራፍ 40:2 የአምላካቸውን ምህራትና ይቅርታ ያውጀል።
ምዕራፍ 40:3 የህዝቡንም ኃለፍነት ከባቢሎን ለመመለስ ለአዲስ ኪደን ደግሞ በመሲሁ በኩል የሚመጣውን የእግዚአብሔርን ምህረት ለመቀበል ተዘጋጁ የሚል መልዕክት አለው፤ እግዚአብሔር ሊያድናቸው እየመጣ እንደሆነ ይነግራቸዋል።

2. መልዕክተኛው(9-11)።
መልዕክተኛው ነቢዩ ኢሳያስ ነው። መልዕክተኛው በእግዚአብሔር ለመረጣት ከተማ ለፅዮን መልካም ዜና ከፍ ባለ ድምፅ ተናገር ተብሎአል።
እነሆ አምላካችሁ!! "Behold Your God" ብለህ ጩኽ!! አምላካችሁ ሊያድናችሁ ይመጣል(40:9)። በጣም እርግጠኛ ሆኖ ነው የሚናገረው። ምክንያቱም ምዕራፍ 6 የእሥራኤልን አምላክ ከፍ ባለ ዙፋኑ ተቀምጦ አይቶአል።
ስለዚህ አምላካችው ለህዝቡ ሊያደርግ ያለውን ትድግናና እንክብካቤ ከፍ አድርጎ ያበሥራል።

3. ገለፃ፣ ማብራርያ(12-26)
ገለፃው የእሥራኤልን አምላክ ኃይል፣ ሥልጣንና የመለኮት ባህርዩን ይዘረዝራል። እግዚአብሔር ዓለምን በሙሉ ማለትም የብሱን፣ ባህሩንና ዩኒቨርሱን የፈጠረ ብቻ ሳይሆን ደግፎ የያዘ፤ ጠብቆ ያቆየና አስተዳዳሪ እንደሆነ በአፅንኦት ይናገራል(40:9)።
ስለዚህ እሱ ከማንም ከምንም ሊወዳደር የማይችል ብለኛ አምላክ መሆኑን በጠንካራ ድምፀት ይናገራል(18_2፣26)።

እሥራኤል ሆይ አምላክሽ በየብስ፣ በባህር፥ በዩኒቨርስና በፍጥረት ሁሉ ላይ ሥልጣን ያለው አምለክ ስለሆነ ለህዝቡ በወደደ መንገድ ትድግናን ያደርጋል(40:12-26)።
ለእሥራኤል ያለው መልዕክት፥ በአጭሩ እናስቀምጥ ካልን ፦ልጆችሽ ከምርኮ ሀገር ይመለሳሉ የሚል ነው(401-31)።

4. የህዝቡ ሁኔታ እና የምዕራፉ ማጠቃለያ (27-31)።
ለምን እንዲህ ትላለህ? ከሚለው የእግዚአብሔር ንግግር ህዝቡ እግዚአብሔርን በተሳሳተ መንገድ የተረዱ ይመስላሉ። ለዚህም ይሆናል ባህርያቱን የሚዘረዝርላቸው።
- ህዝቡ የመርሳትና የመተው ስሜት እያስተናገዱ ያሉ ይመስላሉ(49:14-16)።

እና ከዚህ በመነሳት ህዝቡን
ከማጉረምረም ወጥታችሁ አምላካችሁን ታመኑት፤ እሱን በተሳሳተ መንገድ አትረዱት የሚል መልዕክት ያስተላልፋል።

ይህ ምዕራፍ ኢሳያስ ምዕራፍ 40 ለኛ ምን መልዕክት አለው?

1: በግል ህይወታችን ቢሆን በሀገራችን እና በዓለማችን ከእግዚአብሔር እውቀት ውጭ የሆነ ምንም ነገር የለም( 40:28)
ሆኖ ያለፈ፣ እየሆነ ያለ እና ሊሆን ያለ ነገር በሙሉ እግዚአብሔር የሚያውቀው ነገር ነው። በመሆኑም በእግዚአብሔር እንታመን።

2: እግዚአብሔር አምላክ ፃዲቅ ፈራጅ ብቻ ሰይሆን መሃሪና ይቅር ባይ አምላክ እንደሆነ እንረዳለን ( 40:2- 11)።

3: የኃይል ሚዛን በነጋስታት እጅ ሳይሆን በአምላካችን በእግዚአብሔር እጅ ላይ መሆኑን (40:23 ምሳሌ 21:1)።

4: ኃይል ችሎታና ሥልጣን የሱ የሆነ ከማንም፣ ከምንም ጋር የማይወዳደር ብቸኛ አምላክ እግዚአብሔር ብቻ እንደሆነ (40:18-22/ 25-26)።

ስለዚህ በሱ ለይ እንረፍ። እሱ ሳይፈቅድ በህይወታችንም ይሁን በዓለማችን ለይ ምንም ነገር ሊሆን አይችልም፤ ያለውም አይቀርም፤ ያላለውም አይሆንም።
በተለያያ ምክንያት በማጉረምረም ውስጥ ያለን፤ እሱ ሁሉንም ነገር በራሱ ጊዜ ስለሚሠራ፤ በፅናት እሱን እንጠብቅ።
- አምላካችን ሊያድነን ይመጣል፤ ለደካማም ሀይል ይሰጣል። ጌታ ይባርካችሁ።

Follow Us
◽️ YouTube
https://is.gd/FGBCHawassaYoutube
◽️Facebook
https://fb.me/FGBCHawassa
◽️Instagram
https://ig.me/FGBCHawassa
◽️Telegram
https://t.me/FGBCHawassa

የሀዋሳ ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን
የሚዲያ አገልግሎት
ሚያዝያ 11 /2018 ዓ.ም

የተነሣው ያስነሣናል መጋቢ ተስፋዬ ጋቢሶበሀዋሳ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን ሚያዝያ 4/2018 ዓ.ም እሁድ ጥዋት  የተካሄደው የጌታችን፣ የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ መታ...
12/04/2026

የተነሣው ያስነሣናል
መጋቢ ተስፋዬ ጋቢሶ

በሀዋሳ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን ሚያዝያ 4/2018 ዓ.ም እሁድ ጥዋት የተካሄደው የጌታችን፣ የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ መታሰቢያ ፕሮግራም

በትንሳኤ መታሰቢያ ፕሮግራም ምዕመናን በፀሎት፣ በምስጋና የዝማሬ አምልኮ፣ የእግዚአብሔርን ቃል በመካፈል የጌታ ኢየሱስን ትንሳኤውን በማሰብ የክርስቶስ ኢየሱስን ስም ገናናነት ከፍ በማድረግ አወድሰዋል፤ እግዚአብሔርን ከፍ አድርገዋል።

በዕለቱ በነበረው የቃል አገልግሎት መጋቢ ተስፋዬ ጋቢሶ (1ኛ ቆሮንቶስ 15: 20-22) ን መሰረት በማድረግ "የተነሣው ያስነሣናል “ በሚል ርዕስ ቀጥለው በቀረቡት ነጥቦች ላይ የእግዚአብሔርን ቃል አስተምረዋል።

"አሁን ግን ክርስቶስ ላንቀላፉት በኩራት ሆኖ ከሙታን ተነሥቶአል። ሞት በሰው በኩል ስለ መጣ ትንሣኤ ሙታን በሰው በኩል ሆኖአልና። ሁሉ በአዳም እንደሚሞቱ እንዲሁ ሁሉ በክርስቶስ ደግሞ ሕያዋን ይሆናሉና።"

ከ2000 ዓመታት በፊት፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተነሥቷል። መቃብሩ ባዶ ነው። የተነሣው ክርስቶስ ተመልሶ ለብዙዎች ታይቷል። የትንሣኤው ምስክር ከሆኑት አንዱ ተቃዋሚ የነበረው ሳውል/ ጳውሎስ ነው። (15:3-8)

ትንሣኤውን በምናስብበትና በምናከብርበት ወቅት ለእኛ ለአማኞች የሚኖረውን ትርጉምና አስፈላጊነት አብረን ማሰብ ይኖርብናል። ፋይዳው ይህ ነው። የምናመልከው ሞትን ድል የነሣ የእግዚአብሔር ልጅ ነው። በመሆኑም፣ ከሙታን የተነሣው ኢየሱስ እኛንም ያስነሣናል። ይህን የምንልባቸው ምክንያቶች አሉን:-

1. ያመኑበትን እንደሚያስነሣ አስቀድሞ ተናግሯል። (ዮሐ 11: 23-25) እንዲህም ብሏል :- "ልጅንም አይቶ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወትን እንዲያገኝ የአባቴ ፈቃድ ይህ ነው፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ።” ( 6:40) ይህ "አስነሣዋለሁ" የሚለው ቃል በ44 ና 54 ላይም የተደጋገመ ነው። አሳቡ "በመጨረሻው ቀን እንዳስነሣው" በማለት በ39ኛው ቁጥር ላይ የሚጀምር ነው።

ይህ የተስፋ ቃል ነው። ቃሉም የታመነ ነው። ተስፋን የስጠው እርሱ የታመነ ነው። አይዋሽም።

2. የሞቱትን እስነሥቶ ማስረጃ ስጥቷል። አንዱ ከመቃብር ያወጣው አልዓዛር ነው። (11:43-44) ሌላው የመበለቲቱ ወንድ ልጅ (ሉቃ 7:12-15)፣ ሌላዋ ደግሞ የኢያኢሮስ ሴት ልጅ ነበረች።(ማር 5) ሦስት ናቸው። ይህ በቂ የሆነ ቁጥር ነው። ነገር ሁሉ በሁለት ወይም በሦስት ምስክር ይጸናል ተብሏልና። ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ፣ መለኮት መሆኑን ለማስረዳትም ይህ በቂ ነው።

3. ላንቀላፉት በኩራት ሆኖ ራሱም ከሙታን ተነሥቷል። ይህ ከፍተኛው ምልክትና ማስረጃ ነው። የትንሣኤ እውነታ ብቻ ሳይሆን የመለኮትነቱ ማስረጃ ነው። (ዮሐ 20:1-2፤19፤ 21:14። 1 ቆሮ 15:20) ተከትለውት ለሚነሡ አማኞች ቀዳሚ ሆኖ ተነሥቷል ማለት ነው።

በዚህም ምክንያት፣ የሞት መርዙና መንደፊያው እንዳይሠራ ተደርጓል። ኢየሱስ የኃጢአትን ገዳይ ኃይል አስወግዶልናል። የሲዖልን ድል መንሣት ድል ወደ መነሣት ቀይሮታል።(ቆሮ 15: 55) መቃብር ይዞ ሊያስቀረን እይችልም።

እኛም እርሱን ተከትለን ልንነሣ ተስፋ አለን። ከሙታን የተነሣው እርሱ ያስነሣናል። ታሪካችን በመቃብር የሚደመደም አይሆንም። ከመቃብር ባሻገር ሕይወታችን ይቀጥላል። የሚበሰብሰው አካላችን የማይበሰብሰውን ይለብሳል። ኑሯችን፣ ከተነሣውና ከከበረው ክርስቶስ ጋር በክብር ይቀጥላል።

እስከዚያውም፣ ከሙታን የተነሣው ክርስቶስ፣ ከውድቀትም ከውርደትም ያነሣናል። ከአልጋ ቁራኛ ሳይቀር የማስነሣት ኃይል ዛሬም አለው። የመፈወስ ኃይሉ ከትንሣኤው በኋላም በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ውስጥ ሲሠራ ታይቷልና። (ያዕ 5:14-15)

በመሆኑም፣ የተሰጠን ተስፋ የቅርብም የሩቅም ነው። ከሙታን ተነሥቶ ከፍ ከፍ ያለው ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ለዘላለም ጌታ የሆነ ባለ ሥልጣን ነው። ስለዚህ ክርስቶስ ኢየሱስ ጽኑ የሆነ ተስፋችን ነው።

የመጨረሻው ጠላታችን የሆነውን ሞትን ልንፈራው አይገባንም። ትንሣኤውን ማሰብ ተስፋችንን ያድሰዋል።
የተነሣው ክርስቶስ በእርግጥ ያስነሣናል። ወደ ዘላለሙ ክብርም ያስገባናል። ክብር ለስሙ ይሁን።

Follow Us
◽️ YouTube
https://is.gd/FGBCHawassaYoutube
◽️Facebook
https://fb.me/FGBCHawassa
◽️Instagram
https://ig.me/FGBCHawassa
◽️Telegram
https://t.me/FGBCHawassa

የሀዋሳ ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን
የሚዲያ አገልግሎት
ሚያዝያ 4 /2018 ዓ.ም

ትንሳኤን ከዲያቆናት ጋርየአውደ ሕይወት ልዩ የበዓል ፕሮግራም
12/04/2026

ትንሳኤን ከዲያቆናት ጋር
የአውደ ሕይወት ልዩ የበዓል ፕሮግራም

ወደ ሀዋሳ ሙሉወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን የዩቱብ ቻነል እንኳን ደህና መጡ! በዚህ ቻነል አምልኮ፣ ዝማሬ፣ የእግዚአብሔር ቃል እና ሌሎች አገልግሎቶችን ያገኛሉ። አዳዲስ ቪድ....

የቤተ ክርስቲያኒቱ እንኳን አደረሳችሁ መልዕክት
11/04/2026

የቤተ ክርስቲያኒቱ እንኳን አደረሳችሁ መልዕክት

ወደ ሀዋሳ ሙሉወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን የዩቱብ ቻነል እንኳን ደህና መጡ! በዚህ ቻነል አምልኮ፣ ዝማሬ፣ የእግዚአብሔር ቃል እና ሌሎች አገልግሎቶችን ያገኛሉ። አዳዲስ ቪድ....

https://www.youtube.com/watch?v=5XNUe7hkU3I
11/04/2026

https://www.youtube.com/watch?v=5XNUe7hkU3I

ወደ ሀዋሳ ሙሉወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን የዩቱብ ቻነል እንኳን ደህና መጡ! በዚህ ቻነል አምልኮ፣ ዝማሬ፣ የእግዚአብሔር ቃል እና ሌሎች አገልግሎቶችን ያገኛሉ። አዳዲስ ቪድ....

ነገ እሁድ (ሚያዚያ 4)የጌታችንና የመድሃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ መታሰቢያ ፕሮግራምጠዋት በ2፡00 ሁለቱም ፈረቃ በጋራበዕለቱ አዲስ ለተወለዱ እና ከዚህ በፊት ላልተጸለየላቸው ልጆ...
11/04/2026

ነገ እሁድ (ሚያዚያ 4)
የጌታችንና የመድሃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ መታሰቢያ ፕሮግራም
ጠዋት በ2፡00 ሁለቱም ፈረቃ በጋራ

በዕለቱ አዲስ ለተወለዱ እና ከዚህ በፊት ላልተጸለየላቸው ልጆች ስለሚጸለይ ወላጆች ልጆቻችሁን ይዛችሁ እንድትመጡ ይሁን፡፡

ጩኸት በአዲስ ኪዳን ፤ ለችግሮቻችን እንጩህበፕሮፌሰር ዝናቡ ገብረማርያም    በሀዋሳ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን ሚያዝያ 2/2018 ዓ.ም አርብ ጥዋት  የተካሄደው የጌታችን፣ የመድኃኒ...
10/04/2026

ጩኸት በአዲስ ኪዳን ፤ ለችግሮቻችን እንጩህ
በፕሮፌሰር ዝናቡ ገብረማርያም

በሀዋሳ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን ሚያዝያ 2/2018 ዓ.ም አርብ ጥዋት የተካሄደው የጌታችን፣ የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት መታሰቢያ ፕሮግራም

በስቅለት መታሰቢያ ፕሮግራም ምዕመናን በፀሎት፣ በምስጋና የዝማሬ አምልኮ፣ የእግዚአብሔርን ቃል በመካፈል የጌታ ኢየሱስን ስቃዩን መከራውን በማሰብ እግዚአብሔርን ከፍ አድርገዋል። በፕሮግራሙ መጨረሻም ምዕመናን በአንድነት የጌታ እራት መታሰቢያ ፕሮግራምን ወስደዋል።

በዕለቱ በነበረው የቃል አገልግሎት ፕሮፌሰር ዝናቡ ገብረማርያም ዕብ. 5፥ 10 ን መሰረት በማድረግ "ጩኸት በአዲስ ኪዳን፤ ኢየሱስም ጮዃል“ በሚል ርዕስ ቀጥለው በቀረቡት ነጥቦች ላይ የእግዚአብሔርን ቃል አስተምረዋል።

ፕሮፌሰር ዝናቡ በስቅለት መታሰቢያ ፕሮግራም ያስተማሩት ትምህርት በቤተክርስቲያን ባለፉት ተከታታይ ቀናት በነበረው ፆም ፀሎት ፕሮግራም "የችግሮች ሁሉ መፍትሄ ጩኸት ነው ፣ ስለዚህ እንጩኽ" በሚል ርዕስ ሲያስተምሩ የነበረው ትምህርት ማጠቃለያ ነው ።

ጩኸት የድምፅ ከፍታ አይደለም፤ ከፀሎት ጋር ልዩነት አለው ስንል ጩኸት በስሜት ጥንካሬ፣ አጣዳፊነት፣ ጊዜ የማይሰጥ መሆኑ ነው።

ወደ እግዚአብሔር የሚደረግ ጩኸት ሁሉ ፀሎት ነው፤ ፀሎት ሁሉ ግን ጩኸት አይደለም። የምንጮኸው ሰምቶ ወደሚመልስ ወደ እግዚአብሔር ነው(መዝ. 50፥15፤ 22፥5፤ 34፤ 107)

እስራኤላውያን በግብፅ መከራ ሲበዛባቸው ጮኹ - እግዚአብሔር አዳናቸው፤ የኤርትራ ባህር እና ፈርኦን መካከል ሆነው ሲጨነቁ ጮኹ፤ እግዚአብሔር ባህር ከፍሎ አሻገራቸው፤ ውሃ መራራ(ሜራ) ሲሆንባቸው ጮኹ፤ ውሃውን አጣፈጠላቸው፤ ደጋግመው እግዚአብሔርን ሲበድሉና ለጠላት ተላልፈው ተሰጥተው ጠላቶቻቸው ሲያሰወጨንቋቸው ደጋግሞ አዳናቸው( 1 ሳሙ. 12፥8 ፣ ነህ. 9፥27)።

ኢየሱስ በምድር በሥጋ በነበረበት ዘመን ወደ እግዚአብሔር ጮዃል። በጌቴሴማኒ እና ሌሎች ቦታዎችም ኢየሱስ ጮዃል፤ ስለዚህ የእኛን ጩኸት ይሰማል፤ ይመልሳልም( ሉቃ. 18፥7፣ ማር. 14፥32፣ ሉቃ. 22፥40)

አሁን ካለንበትም፣ ወደፊት ከሚመጣውም መከራ የምናልፈው በጩኸት ነው። በእግዚአብሔር ፊት የተጮኸ ጩኸት፣ የፈሰሰ እንባ፣ በእግዚአብሔር ዘንድ አይረሳም፣ አይባክንም፣ አንድ ቀን ምላሽ ያገኛል!

“ሰቆቃዬን መዝግብ፤ እንባዬን በዕቃህ አጠራቅም፤ ሁሉስ በመዝገብህ የተያዘ አይደለምን?” - መዝ. 56፥8 (አዲሱ መ.ት)

“እንባዎችንም ሁሉ ከዓይኖቻቸው ያብሳል... ” - ራእይ 21፥4 "ተፈፀመ" ያለ ጌታ እርሱ ይራራልናል።

የሚያስጮኽ ብዙ ነገር አለ፤ መፍትሄው ወደ እግዚአብሔር መጮኽ ነው። ስለዚህ እንጩኽ! እግዚአብሔር ሰምቶ ይመልሳል! ዛሬ የሚያስጮኸን ነገር አልፎ በሚቀጥለው ዓመት እንድንገናኝ እግዚአብሔር ይርዳን!

Follow Us
◽️ YouTube
https://is.gd/FGBCHawassaYoutube
◽️Facebook
https://fb.me/FGBCHawassa
◽️Instagram
https://ig.me/FGBCHawassa
◽️Telegram
https://t.me/FGBCHawassa

የሀዋሳ ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን
የሚዲያ አገልግሎት
ሚያዝያ 2 /2018 ዓ.ም

https://www.youtube.com/watch?v=H2lTyq0BWyQ
10/04/2026

https://www.youtube.com/watch?v=H2lTyq0BWyQ

ወደ ሀዋሳ ሙሉወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን የዩቱብ ቻነል እንኳን ደህና መጡ! በዚህ ቻነል አምልኮ፣ ዝማሬ፣ የእግዚአብሔር ቃል እና ሌሎች አገልግሎቶችን ያገኛሉ። አዳዲስ ቪድ....

Address

Atote Wanza
Hawassa
P.O.BOX=171

Telephone

+251-462-205433

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Full Gospel Believers' Church, Hawassa posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Full Gospel Believers' Church, Hawassa:

Share