ASER Z Samuel

ASER Z Samuel Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ASER Z Samuel, Religious Center, Harer gahe, Hawassa.

Neway Beyene Teshome
Orthodox Tewahedo Christian | Ethiopia ✝️
Finance & Banking Professional
Siinqee Bank – Boke T'ko
By the grace of God, striving to live in faith, uphold truth, and serve the Church, community, and nation with e

 “ሥላሴ” የሚለው ቃል “ሠለሰ” ሦስት አደረገ ካለው የግዕዝ ግሥ የተገኘ ሲሆን ትርጉሙም ሦስትነት ማለት ነው፡፡ቅድስት ሥላሴ ስንል ለሥላሴ ቅድስት ብለን እንቀጽላለን፡፡ ቅድስት ሥላሴ ማለት...
05/05/2026



“ሥላሴ” የሚለው ቃል “ሠለሰ” ሦስት አደረገ ካለው የግዕዝ ግሥ የተገኘ ሲሆን ትርጉሙም ሦስትነት ማለት ነው፡፡

ቅድስት ሥላሴ ስንል ለሥላሴ ቅድስት ብለን እንቀጽላለን፡፡ ቅድስት ሥላሴ ማለት ልዩ ሦስትነት ማለት ነው፡፡ ይህም ሦስት ሲሆኑ አንድ፣ አንድ ሲሆን ሦስት ስለሚሆኑ ልዩ ሦስትነት ተብሏል፡፡ ሥላሴ የሚለውን ቃል ለመጀመሪያ ጊዜ ያለና የሚኖረውን አምላክ ለመግለጽ የተጠቀመው የአንጾኪያው ቅዱስ ቴዎፍሎስ በ169 ዓ.ም ነው፡፡ በኒቅያ ጉባዔም 318ቱ ሊቃውንት አጽንተውታል፡፡ ሊቃውንቱ በቅዱሳት መጻሕፍት የተመሰከረውን የእግዚአብሔርን ፍጹም አንድነትና ልዩ ሦስትነት ለእኛ በሚረዳ ቋንቋ ገለጡት እንጂ አዲስ ትምህርት አላመጡም፡፡ ምስጢረ ሥላሴ ማለት የአንድነት የሦስትነት ምስጢር ማለት ነው፡፡ ምሥጢር መባሉም በእምነት የተገለጠ፣ ያለ እምነትም የማይመረመር ስለሆነ ነው፡፡

ይኸውም አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ በስም፣ በአካል፣ በግብር ሦስት ሲሆኑ በባሕርይ በሕልውና፣ በመለኮት ደግሞ አንድ ናቸው፡፡ እንደዚህ ባለ ድንቅ ነገር አንድ ሲሆኑ ሦስት፣ ሦስት ሲሆኑ አንድ ይባላሉና፣ ይህም ልዩ ሦስትነት ረቂቅ እና በሰው አእምሮ የማይመረመር ስለሆነ ምስጢር ይባላል፡፡ ስለዚህም አንድ አምላክ፣ ሦስቱ አካላት ብለን እናምናለን፡፡ ሥላሴ ሦስት ናቸው ስንል እንደ አብርሃም፣ እንደ ይስሐቅ እንደ ያዕቆብ የተነጣጠለና በክብርም ሆነ በዘመን የሚበላለጥ የሚቀዳደም ማለታችን አይደለም፡፡ ሦስት ሲሆኑ አንድ ናቸው እንጂ፡፡ አንድ ናቸውም ስንል ከሰው ሁሉ ቀዳሚ ሆኖ እንደተፈጠረው እንደ አዳም ሦስትነትን የሚጠቀልል መቀላቀል ማለታችን አይደለም፡፡ አንድ ሲሆኑ ሦስት ናቸው እንጂ እንዲል ቅዳሴ ማርያም፡፡

የሥላሴ አንድነትና ሦስትነት በሰው ምሳሌ ይገለጻል፡፡ ሰው በነፍሱ ሦስትነት አለው፡፡ ይኸውም ልብነት፣ ቃልነት፣ ሕይወትነት ነው፡፡ በልብነቷ አብ፣ በቃልነቷ ወልድ፣ በሕይወትነቷ መንፈስ ቅዱስ ይመስላሉ፡፡ የነፍስ ልብነቷ፣ ቃልነቷን፣ ሕይወትነቷን ከራሷ ታስገኛለችና፡፡ ቃልና ሕይወት ከአንዷ ልብ ስለተገኙ በከዊን ወይም በመሆን ልዩ እንደሆኑ በመናገርም ይለያሉ፡፡ እንዲሁም አብ ወልድን በቃል አምሳል ወለደው፣ መንፈስ ቅዱስንም በእስትንፋስ አንጻር አሰረጸው፡፡ ነፍስ ስትገኝ በሦስትነቷ በአንድ ጊዜ ተገኘች አንዷ ልብነቷ ቀድሞ ቃልነቷና እስትንፋስነቷ በኋላ አልተገኙም፡፡ ሥላሴም አንዱ ከአንዱ ሳይቀድሙ ተገኝተዋልና፡፡

በአሚነ ሥላሴ ያጽናን🙏🙏🙏

ተንሥአ (ተነሥቷል) ሉቃ 24፥6ነገረ ክርስቶስን በስተማርን ጊዜ ኹሉ ቅዱሳን መላእክትን እንዘክራቸዋለን። ኢየሱስ ክርስቶስን ተጸነ፣ ተወለደ፣ ተሰደደ፣ ከስደት ተመለሰ እያሉ ብሥራትን ያመጡ፣...
05/05/2026

ተንሥአ (ተነሥቷል) ሉቃ 24፥6

ነገረ ክርስቶስን በስተማርን ጊዜ ኹሉ ቅዱሳን መላእክትን እንዘክራቸዋለን።

ኢየሱስ ክርስቶስን ተጸነ፣ ተወለደ፣ ተሰደደ፣ ከስደት ተመለሰ እያሉ ብሥራትን ያመጡ፣ በሚጾምበት ጊዜ ቀርበው ያገለገሉ ማቴ 4፤ በሰርግ ቤት ሳለ መጥተው ሰማይ ዙፋንህ ምድር የእግርህ መረገጫ ስትሆን በተናቀች ጎጆ በሰርግ ቤት መገኘትህ ምን ይደንቅ? ብለው ያደነቁት (ሃ.አ.ዘቅዱስ ኤፍሬም)፤ የእኛን መከራ ሊቀበል ጊዜው በመድረሱ በጸሎተ ሐሙስ ሲጸልይ "አባት ሆይ ይኽች ጽዋዕ ከእኔ ትለፍ..." በሚል ጊዜ ከሰማይ መጥተው ያበረቱት (ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለም) በማለት የሰገዱት) ሉቃ 22፤ ጎኑ በጦር በተወጋ ጊዜ በወርቅ ጽዋዕ ቀድተው ዓለምን የረጩት፣ በተነሣም ጊዜ "ተነሥቷል በዚህ የለም" ብለው ምሥራችን የሰበኩት፣ ወደ ሰማይ ሲያርግ ሲሔድ እንዳያችሁት እንዲሁ ይመጣል ብለው ለደቀ መዛሙርቱ የመሠከሩ፣ ዳግመኛም ሲመጣ መለከት እየነፉ "ቅዱስ እግዚአብሔር ቅዱስ ኃያል ቅዱስ ሕያው ዘኢይመውት... ንቃህ መዋቲ" በማለት አዋጅ የሚናገሩ መላእክተ ብሥራት (አብሣሪ መላእክት) ናቸው። የኢየሱስን ሥጋ ሽቱ ቀብተው ለመሰናበት ፎቅሩ ሲያንገበግባቸው አድረዋልና ገና ሳይነጋ ገሥግሠው ፍለጋ ሒደው ሥጋውን አጥተው የመቃብሩን ባዶ መሆን ተመልክተው ሲጨነቁ ለነበሩ ሴቶች፦

" ? ፤ ተዘከራ ዘይቤለክን በገሊላ ሀለዎ ለወልደ እጓለ እመሕያው ይግባእ ውስተ እደ ሰብእ፤ ወይሰቅልዎ፤ ወይቀትልዎ፤ ወይትነሣእ በሣልስት ዕለት ። "ሕያውን ከሙታን መካከል ስለ ምን ትፈልጋላችሁ ? #አንድም ስለምን ትሹታላችሁ? ተነሥቷል እንጂ በዚህ የለም ። የሰው ልጅ በኃጥአን እጅ ተላልፎ ሊሰጥና ሊሰቀል፣ ሊገደል በሦስተኛውም ቀን ሊነሣ ግድ ነው እያለ ገና በገሊላ ሳለ ለእናንተ እንደ ተናገረ አስቡ ።"ሉቃ 24:5-7 አሏቸው።

ዐራቱም ወንጌላውያን ይኽንን የምሥራች ዘግበውልናል።

“መልአኩም መልሶ ሴቶቹን አላቸው! እናንተስ አትፍሩ የተሰቀለውን ኢየሱስን እንድትሹ አውቃለሁና፤ እንደ ተናገረ ተነሥቷልና በዚህ የለም፤ የተኛበትን ስፍራ ኑና እዩ:: ፈጥናችሁም ሂዱና፡፡ ከሙታን ተነሣ እነሆም ወደ ገሊላ ይቀድማችኋል በዚያም ታዩታላችሁ ብላችሁ ለደቀ መዛሙርቱ ንገሩአቸው›› ማቴ ፳፰ እነርሱም መልአክ ዐይተዋልና እየፈሩ ትንሣኤውን ሰምተዋልና ደስ እያላቸው ለደቀ መዛሙርቱ ይነግሯቸው ዘንድ ፈጥነው ሔደው የክርስቶስን ትንሣኤ አበሠሩ።

“ወደ መቃብሩም ገብተው ነጭ ልብስ የተጎናጸፈ ጎልማሳ በቀኝ በኩል ተቀምጦ አዩና ደነገጡ፡፡ እርሱ ግን አትደንግጡ ፤ የተሰቀለውን የናዝሬቱን ኢየሱስን ትፈልጋላችሁ ፤ ተነሥቷል በዚህ የለም! ነገር ግን ሄዳችሁ ለደቀ መዛሙርቱ #ለጴጥሮስም ወደ ገሊላ ይቀድማችኋል፤ እንደ ነገራችሁ በዚያ ታዩታላችሁ ብላችሁ ንገሩአቸው አላቸው>> ብሎ አስፍሮታል። ማር 14:5

ደግሞ “እነርሱም በዚህ ሲያመነቱ እነሆ ሁለት ሰዎች የሚያንጸባርቅ ልብስ ለብሰው ወደ እነርሱ ቀርበው "ሕያውን ከሙታን መካከል ስለ ምን ትፈልጋላችሁ? ተነሥቷል እንጂ በዚህ የለም። የሰው ልጅ በኀጢአተኞች እጅ ታልፎ ሊስጥና ሊስቀል በሦስተኛውም ቀን ሊነሣ ግድ ነው እያለ ገና በገሊላ ሳለ ለእናንተ እንደ ተናገረ አስቡ" አሉአቸው። ሉቃ 28: 6

"መግደላዊት ማርያም ሁለቱን መላእክት እንዳየችና ከእነርሱም ጋር እንደተነጋገረች ሲገልጽ "ማርያም ግን እያለቀሰች ከመቃብሩ በስተውጭ ቆማ ነበር። ስታለቅስም ወደ መቃብር ዝቅ ብላ ተመ

በቃልኪዳኗ : ለመጠቀም : ትንሽ : ጥርኝ : ውኃ : ብቻ የወላዲተ አምላክ ኪዳነ ምሕረት ከአብርሃም ከዳዊት ቃል ኪዳን ይልቅ የድንግል ማርያም የምሕረት ኪዳን ይበልጣል ።ምክንያቱም እግዚአብ...
05/05/2026

በቃልኪዳኗ : ለመጠቀም : ትንሽ : ጥርኝ : ውኃ : ብቻ

የወላዲተ አምላክ ኪዳነ ምሕረት ከአብርሃም ከዳዊት ቃል ኪዳን ይልቅ የድንግል ማርያም የምሕረት ኪዳን ይበልጣል ።

ምክንያቱም እግዚአብሔርን በቤቱ ካስተናገደው ከአብርሃም ይልቅ ለእግዚአብሔር ቤቱ የሆነች ድንግል ማርያም ትበልጣለችና ።

በእግዚአብሔር ታቦት ፊት ከዘለለው ከዳዊት ይልቅ ለእግዚአብሔር ታቦት የሆነችው ድንግል ማርያም ትበልጣለች የድንግል ቃልኪዳን ከሁሉ ይበልጣልና ።

እርስዋ ምሕረትን ለማሠጠት የምታስታውሰውን የተገባላትን ኪዳን ብቻ ሳይሆን በብርድ ወራት በጨርቅ የጠቀለለችውን ድንግልናዊ ወተትዋን ያጠባችውን ፣ በስደት ይዛው የተንከራተተችውን ፣ በፊቱ ላይ የወረደውን እንባዋን እያስታወሰች እያማለደች ምሕረትን ስለምታሰጥ ነው ።

በቃልኪዳን ለመጠቀም እንደ መበለቲቱ ትንሽ ዱቄት ትንሽ መልካምነት ያስፈልጋል እግዚአብሔር ትንሹን በቸርነቱ ያበዛዋልና ።

እግዚአብሔርም ምሕረትን ለማድረግ ጥቂት ነገር ይፈልጋል ጥርኝ ዱቄት ጥርኝ ደግነት ጥርኝ ውኃ እንደ በላኤ ሰብእ ከእኛ ይጠበቃል ።

እንደ ሕዝቅያስ ጥርኝ ዕንባ ሲያገኝ ከዳዊት ቃል ኪዳን ጋር ደምሮ ይምረናል ።

እንደ ሙሴ አታጥፋቸው የሚል ጥርኝ ምልጃ ሲያገኝ ከአብርሃም ቃል ኪዳን ጋር ደምሮ ይምረናል ።

ጥርኝ ውኃ ጥርኝ ዕንባ ጥርኝ ደግነት ብቻ አንዳች ጥርኝ መልካምነት ከእኛ ዘንድ ካለ ለእናቱ በገባላት የምሕረት ቃል ኪዳን ይምረናል ይታደገናል።

ጽ ዮ ን : የ ም ድ ር : ሁ ሉ : ደ ስ ታ : ና ት !!!እስራኤልላውያን ከግብፅ ከባርነት ከወጡ በኋላ ጸልየው እንዲድኑባት ሰውተው እንዲከብሩባት ታቦተ ጽዮንን እግዚአብሔር አምላክ ሰጣቸ...
05/05/2026

ጽ ዮ ን : የ ም ድ ር : ሁ ሉ : ደ ስ ታ : ና ት !!!

እስራኤልላውያን ከግብፅ ከባርነት ከወጡ በኋላ ጸልየው እንዲድኑባት ሰውተው እንዲከብሩባት ታቦተ ጽዮንን እግዚአብሔር አምላክ ሰጣቸው በታቦተ ጽዮን እየተማፀኑ አርባ ዘመን ደመና እየጋረደ መና እያወረደ ዐለት እየሰነጠቀ ውኃ ከጭንጫ እያፈለቀ በሰላም ተንከባክቦ መግቦ ምድረ ርስት አግብቷቸዋል ።

ቅጽረ ኢያሪኮን ያፈረሰች ።
የዮርዳኖስን ባሕርን የከፈለች ።
በድፍረት ሊነካት የሞከረ ኦዛንን የቀሠፈች ።
ዳጎን የተባለ የፍልስጤማውያንን ጣዖት ቆራርጣ ያጠፋች ።
በአቢዳራ ቤት ሦስት ወር ተቀምጣ ቤቱን በበረከት የመላች ።
ከብዙ ዘመን በኋላ ወደ ሀገሯ ስትመለስ ነቢየ ዳዊት በደስታ የዘመረላት ።
ንጉሥ ሰሎሞን በወርቅ የተጌጠ ቤተ መቅደስ ሠርቶ በክብር ያኖራት ።
በደብተራ ኦሪት በቅድስተ ቅዱሳን ውስጥ ተቀምጣ ያለች ናት ።

የእግዚአብሔር የክብሩ መገለጫ ታቦት የሆነችው ይህች በንጽሕና በቅድስና የተጌጠችው የእግዚአብሔር ወልድ እናት የሆነችው የአማናዊት ታቦት የቅድስት ድንግል ማርያም ምሳሌ ናት ፡፡

የአምላክ ማደሪያ የሆነችው ታቦት ጽዮን ወደ ፍልስጥኤም ሀገር ሔዳ ዳጎንን ሰባብራ እንዳጠፋች ሁሉ አማናዊት የጌታ ታቦት ቅድስት ድንግል ማርያምም ጌታን ይዛ ወደ ግብጽ በተሰደደች ጊዜ የግብጽ ጣዖታትን ሁሉ እየተሰባበሩ እንደወዳደቁና እንደደቀቁ በኢትዮጵያ ሀገራችን በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን ጠላት ካሴረባት ሸፍጥ ሁሉ እግዚአብሔር አምላካችን ይታደጋት

"Tragedy turns into comedy when you watch your own drama and realising it as a mind-created fiction designed to create y...
01/05/2026

"Tragedy turns into comedy when you watch your own drama and realising it as a mind-created fiction designed to create you a sense of identity."
~ Ekhart tolle
በሕይወታችን ውስጥ የሚያጋጥሙን አስቸጋሪ ነገሮች (ትራጄዲ) ወደ ቀልድ (ኮሜዲ) የሚቀየሩት፣ ነገሮቹን ከራሳችን ነጥለን እንደ ተመልካች ማየት ስንጀምር ነው። ያጋጠመን "ድራማ" ሁሉ አእምሯችን እኛነታችንን ለመገንባት የፈጠረው ልብ ወለድ መሆኑን ስንረዳ ነገሩ ቀላላ ይሆንልናል።
የአዕምሮ ድራማ :-አብዛኛውን ጊዜ የምንጨነቅባቸው ነገሮች አዕምሯችን የሚፈጥራቸው ታሪኮች ናቸው። ለምሳሌ፦ "እኔ ሁልጊዜ እድል የለኝም" ወይም "ሁሉም ሰው ይጠላኛል" የሚሉ ሃሳቦች አእምሯችን የፈጠራቸው "ድራማዎች" ናቸው።

የማንነት ስሜት (Identity)፦ አእምሯችን እነዚህን ታሪኮች የሚፈጥረው "እኔ እንዲህ አይነት ሰው ነኝ" የሚል ስሜት እንዲሰጠን ነው። በችግራችን ላይ ተመስርተን ማንነታችንን እንድንገልጽ ያደርገናል።

ከድራማው መውጣት፦ ችግሩን ልክ እንደ ፊልም ተመልካች ሆኖ ማየት (Watch your own drama)። "እኔ ይሄ ችግር ነኝ" ከማለት ይልቅ "አእምሮዬ ይሄን ታሪክ እያወራ ነው" ብሎ ማሰብ ሲቻል ድራማው ይቆማል።ለምን ወደ ኮሜዲ ይቀየራል? አንድን በጣም የሚያስጨንቅ ነገር "ውሸት" ወይም "ልብ ወለድ" መሆኑን ስታውቅ በነገሩ ላይ መሳቅ ትጀምራለህ። ነገሩ ክብደቱን ያጣና እንደ ቀልድ ቀላል ይሆንልሃል።

ባጭሩ፦ በህይወትህ የሚገጥሙህን ፈተናዎች በጣም አክብደህ ከማየት ይልቅ፣ አእምሮህ የፈጠራቸው ታሪኮች መሆናቸውን ተረድተህ በነፃነት እያቸው። ያኔ ስቃዩ ወደ ሰላም ይለወጣል።

ፊደለይ ኢኪ ድንግለይ
28/04/2026

ፊደለይ ኢኪ ድንግለይ

✨ ስለበጎ ሥራ የሚቀበሏቸው መከራት እንደጸጋ እንደ ክብር ይወደዳሉ፡፡ መከራ ለመቀበል የሚወድ ሰው አስቀድሞ እግዚአብሔር ያድነኛል ብሎ ይመን፡፡ ተምሬያለሁ አዋቂ ነኝ ከሚል ሰው ያልተማረ በ...
28/04/2026

✨ ስለበጎ ሥራ የሚቀበሏቸው መከራት እንደጸጋ እንደ ክብር ይወደዳሉ፡፡ መከራ ለመቀበል የሚወድ ሰው አስቀድሞ እግዚአብሔር ያድነኛል ብሎ ይመን፡፡ ተምሬያለሁ አዋቂ ነኝ ከሚል ሰው ያልተማረ በመከራ የተፈተነ ጨዋ ይሻላል፡፡ የምናገኘው ክብር በመከራችን ልክ ነው ከመከራ በኋላ ጸጋ ክብር ይሰጣል፡፡ ስለታበይን ከሰይጣናት ዘንድ የሚመጣብን መከራም አለ፡፡

☀️ ይህም ክፉ ክፉ ነገር በሚያደርጉብን ሰዎች ላይ ይጥለናል፡፡ የሰው ትዕግሥቱ መከራውን ያርቀዋል፡፡ ትዕግሥት የጸጋ ምክንያት ናት፡፡ እግዚአብሔርን የወደድክ ያህል በመንፈስ ቅዱስ ደስ የሚልህ ደስታ ይበዛል። እግዚአብሔርን መከራውን ታግሠን በማመስገን እንለምነው። መጽሐፈ መነኮሳት [አንቀጽ 22] 🤍

✨ አምላኬ ልዑል እግዚአብሔር ሆይ እንዳንተ ሰላም የሰጠኝ .....እረፍት ያጎናፀፈኝ......በደስታ የማጣጥመው ንፁህ አየር የለገሰኝ....... የለመለመ ህይወት ያደለኝ ካንተ በቀር አንዳች የለም። ❣️ ተመስገን 🙏

🍂 ✨ ደጇን የምወደው ከመታሰብያ ቀኗ ውጪ ባሉት የዘውትር ዕለታት ነው እንደ ልቤ አግኝቼ እንዳወራኋት የሚሰማኝ ሰው ሳይኖር ብቻዋን ሳገኛት ነው ሰሚናት እሷ ለነገራት የ እንጦጦዋ ብዬ አፍሬ...
28/04/2026

🍂 ✨ ደጇን የምወደው ከመታሰብያ ቀኗ ውጪ ባሉት የዘውትር ዕለታት ነው እንደ ልቤ አግኝቼ እንዳወራኋት የሚሰማኝ ሰው ሳይኖር ብቻዋን ሳገኛት ነው ሰሚናት እሷ ለነገራት የ እንጦጦዋ ብዬ አፍሬ አላውቅም ምስክር ነኝ እውነት🤍 እሄዳለሁ እፎይ ብዬ ሰላሜን አግኝቼ ነው የምመለሰው ❤️‍🩹እመቤቴ ሆይ ያላንቺ ህይወትን ማሰብ ይከብደኛል ........ እኔ እና ብዙ በቀሚስሽ ጥላ የሸፈንሽን ልጆችሽ እንወድሻለን። እንዳንቺ የምወደው ማንም የለም በእውነት ከጻድቃንም ቢሆን ወይም ከነቢያት ያንቺን ቦታ የሚተካከል የለም 🥰 ገመናዬ ኪዳነ ምህረት 🥀❤

🤍 ችግር ይሸሻል አንችን ስጠራ
መከራ ይቀላል ካንቺ ሳወራ
ንዒ ንዒ ስል የምትደርሺ ፈጥነሽ
አለሁ የምትዪኝ የልቤን አውቀሽ❣

ምስጢሬን_በምስጢር_የምነግርሽ_ኪዳነምሕረት_ሰሚዬ_ነሽ 💞💝💝💝💝❣️❣️❣️💕💕💕

23/04/2026

I accepted 1 fan badge from ፊደለይ ኢኪ ድንግለይ.

ከክፉ ነገር እየጠበቀ ያሳደገን መላዕክ ❤ቅዱስ ሚካኤል❤️ ህይወታችንን ያማረና የተባረከ ያድርግልን።የቅዱስ ሚካኤል በረከቱ አይለየን!!!! Don't forget to follow my page 🙏...
20/04/2026

ከክፉ ነገር እየጠበቀ ያሳደገን መላዕክ ❤ቅዱስ ሚካኤል❤️ ህይወታችንን ያማረና የተባረከ ያድርግልን።

የቅዱስ ሚካኤል በረከቱ አይለየን!!!!

Don't forget to follow my page 🙏🙏🙏🙏

20/04/2026

With ፊደለይ ኢኪ ድንግለይ – I just got recognised as one of their top fans!

Address

Harer Gahe
Hawassa

Opening Hours

Saturday 09:00 - 17:00
Sunday 09:00 - 17:00

Website

https://www.tiktok.com/@neway_beyene?_r=1&_t=ZS-93NKanLGoR6

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ASER Z Samuel posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share