Life Foundation Church, መሠረተ ሕይወት ቤተክርስቲያን Hawassa

  • Home
  • Ethiopia
  • Hawassa
  • Life Foundation Church, መሠረተ ሕይወት ቤተክርስቲያን Hawassa

Life Foundation Church, መሠረተ ሕይወት ቤተክርስቲያን Hawassa Meserete Hiwot Church is one of an influential Congregation in Hawassa city.

The church launched the ministry in the year 2007 by the man of God Pastor Simetiru Taye located in the beautiful city of southern Ethiopia, Hawassa. Meserete HIwot Church is founded and launched the official ministry in the year 2007 by the man of God Pastor Simetiru Taye in the beautiful city of southern Ethiopia, Hawassa. The church was known as God's Army Church until it changed it's name by the year Sep 2016.

ሰፊ እርሻ!“ከምንገምተው ሁሉ በላይ.. ኤፌ. 3፡20 እኛ አገልጋዮች ለወንጌል መተላለፍያ መንገዶች እጅግ የጠበበ ልብ ካለን፤ ይልቁኑ በስራችን ያሉ ሰዎች ምን ያህል ይጠቡ ይሆን? ስለ ወንጌ...
27/01/2022

ሰፊ እርሻ!
“ከምንገምተው ሁሉ በላይ.. ኤፌ. 3፡20
እኛ አገልጋዮች ለወንጌል መተላለፍያ መንገዶች እጅግ የጠበበ ልብ ካለን፤ ይልቁኑ በስራችን ያሉ ሰዎች ምን ያህል ይጠቡ ይሆን? ስለ ወንጌል ያለን ግንዛቤ በጣም አናሳ ከሆነ፣ እግዚአብሔር በመንግሥቱ ስራ ዉስጥ ሊጠቀምብን ያዘጋጀውን መንገድ ሁሉ እንዘጋለን።ይህ ብቻ ሳይሆን የእግዚአብሄርን ስራ በተከፈተላቸው እድል የሚሰሩትን አንተባበርም፤ ይልቁኑ እንቃወማለን፣እንቅፋት እንሆናለን። ሁሉን አቀፍ አብያተ ክርስቲያናት በምድራቸው ላይ ለመላሁ የሰው ልጆች አገልግሎት ይሰጣሉ ።አገልግሎታችን ሁለንተናዊ ሲሆን ሰዎችን ሁሉ በእግዛብሄር አይን እየተመለከትን መሆኑን ያሳያል።ስለዚህ ቤተ ክርስቲያን ሁሉንም የሰው ልጅ ፍላጎቶች ታገለግላለች እና በሁሉም የህብረተሰብ ደረጃ ግለሰቦች፣ ቤተሰቦች፣ ማህበረሰቦች፣ ብሔሮች፣ ዉስጥ ራስዋን ትገልጣለች።ጨው ቀለም፣ ዘር ፣ደረጃ የለውም በየትኛውም ገባታ ውስጥ እሱ አለ።ያን የጨውነት ሚና ትጫወት ዘንድ ይሄንን ችሎታ ለቤተክርስትያን መሰጠቱን ሁላችንም አገልጋዮች እናውቃለን እያልን ይሆን????።
F C Hawassa
F C Hawassa
F C Hawassa

Thanks to my co-workers
01/01/2022

Thanks to my co-workers

ሌላ ኢየሱስ የለምሌላ ኢየሱስ፣ሌላ መስቀል፣ሌላ ፀጋ የለም፡፡ ሁሉም አንድ ጊዜ በመሆን ተጠናቋዋል፡፡ክርስትያናዊ ኑሮ የሚገነባው በመስቀል ላይ በተሰራልን ስራ እንጂ እኛ በምንሞካክረው ሽርፍራ...
01/01/2022

ሌላ ኢየሱስ የለም
ሌላ ኢየሱስ፣ሌላ መስቀል፣ሌላ ፀጋ የለም፡፡ ሁሉም አንድ ጊዜ በመሆን ተጠናቋዋል፡፡ክርስትያናዊ ኑሮ የሚገነባው በመስቀል ላይ በተሰራልን ስራ እንጂ እኛ በምንሞካክረው ሽርፍራፊ የፅድቅ ሙከራዎች አይደለም፡፡ሀጥያት ከተሰቀለ እነሆ ሁለት ሺ አመታት አለፈ፣ፅድቅ ከነገሰም እንዲሁ፡፡ነፃ የወጣው ትውልድ ዛሬም በራሱ ልምምድ፣ ውድቀት፣ መነሳት፣ እየዳከረ ከሆነ፤ አይኖቹን ወደ መስቀሉ ያነሳ ዘንድ ይገባዋል፤ሁሉም ነገር "ተፈፀመ" የሚለውን በደም የተፃፈ ዘለአማዊ ለሰው ዘር ሁሉ የተላለፈ ትኩስ መልክት ያነባልና፡፡

ኃይልን በሚሰጠኝ በክርስቶስ ሁሉ ማድረግ እችላለሁ። ፊልጵ 4:13እምነትህ የተነነ ያህል ባዶነት የሚሰማህ ጊዜ ይኖራል። ብቸኝነት ድካም ፣ፍርሀት ፣አጋዠ ማጣት ሌሎችም በሚታገሉህ ጊዜ በሀዘን...
30/12/2021

ኃይልን በሚሰጠኝ በክርስቶስ ሁሉ ማድረግ እችላለሁ። ፊልጵ 4:13

እምነትህ የተነነ ያህል ባዶነት የሚሰማህ ጊዜ ይኖራል። ብቸኝነት ድካም ፣ፍርሀት ፣አጋዠ ማጣት ሌሎችም በሚታገሉህ ጊዜ በሀዘን ልትዋጥ ትችላለህ ።ነገር ግን በእነዚህ ጊዚያት፣የኪዳን አምላክ ኀይልን ያስታጥቅሀል በከበቡህ ነገሮች ሁሉ ላይ የበላይነትን ትጎናፀፋለህ ። በነዚህ መንገዶች ስታልፍ፣እርሱን በመከተል ከጨከንክ፣ አይወጣም ከሚባል ረግረግ ጭቃ ዉስጥ መንጭቆ ያወጣሀል። እሱ በህይወታችሁ በጣም አስቸጋሪ ከሆኑባችሁ ጊዜዎች አርቆ ወደ ከፍታ ይመራችኋል።
ስለዚህ እመኑት።ፍርሃታችሁን እና ጭንቀታችሁን አስረክቡት ፀጋውን በህይወታችሁ ውስጥ እንዲሰራ ፍቀዱለት። ያኔ ነው ሀይልን በሚሰጠኝ በክርስቶስ ሁሉን አደርጋለሁ ማለት የምንችለው።

28/12/2021

ለክብሩ
1ኛ ቆሮንቶስ 10፡31
እንግዲህ የምትበሉ ወይም የምትጠጡ ብትሆኑ ወይም ማናቸውን ነገር ብታደርጉ ሁሉን ለእግዚአብሔር ክብር አድርጉት።
በምድር ቆይታችንን ከጥቂት እስከ ትልቅ ፤ከሚታወቅ እስከማይታወቅ፤ እንቅስቃስያችን ሁሉ ለእርሱ ክብርን የሚያመጣ መሆኑን መረዳት አስፈላጊው የህይወታችን መሰረት ነው።ከእንቅልፋቸው ያልነቁ ብዙዎች የሀይማኖት ካባ በማጥለቅ ንፁሁን ምንጭ በማይታደሰው አእምሮዋቸው አቆሽሸውታል። መንፈሳዊነትን ከመፀለይ ፤ከመዘመር፤ ጥራዝ ነጠቅ የመፀሀፍ ቅዱስ ጥቅሶችን በመጠቃቀስ ላይ ብቻ አድርገው ደምድመውታል። ስራቸውን፤ውሎዋቸውን አለማዊ በማድረግ ብዙዎቹ እየተፀየፉት ነው።ሆኖም ግን ይኖሩበታል። አማኝ ግን በሁሉም የህይወት ደረጃ ከፍ ባለ የመለኮት ህግ በመመራት ሁሉን ነገር ለእግዚአብሄር ክብር ያደርጋል።

መልካሙን ስራ!ኤፌሶን 2: 10  እኛ ፍጥረቱ ነንና፤እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን።ስራ ለመፈለግ ሳይሆን ስራ ለመስ...
27/12/2021

መልካሙን ስራ!
ኤፌሶን 2: 10 እኛ ፍጥረቱ ነንና፤እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን።
ስራ ለመፈለግ ሳይሆን ስራ ለመስራት ወደዚች ምድር ተልከናል::የምንሰራው የተዘጋጀ ሲሆን አይነቱ መልካም ተብሎ ተገልፅዋል::መልካም ምን ማለት ነው ?ብለን ልንጠይቅ እንችላለን::ይሄ እንግዲህ ለራስ ፥ለቤተሰብ፥ለቤተክርስትያን ጠቃሚ የሆነ ለሁሉ የሚጨምረው ብቃት የያዘ ጥቅል መሆን የሚችል ማለት ነው::ሰው ሁሉ በያለበት መልካሙን ነገር ለሰው ልጆች ጥቅም ቢሰራ አጥብያችን፥ከተማችን ምን ልትመስል እንደምትችል እስቲ አስቡት:የመልካም ተከቃራኒ ክፋት ነው::ክፋት በህሊና ህግ የሚያሰቃይ፥ በሞራል ህግ የሚያሳፍር ፥በምድር ህግ የሚያስጠይቅ፥ በመንፈሳዊ ህግ ያልተሰጠን የስራ አይነተ ነው ::ስለዚህ እንደ አማኝ ባልተሰጠን የፀጋ አይነት ቀኑን ሙሉ ባንተጋ ከፈጣሪ ጋር በሰላም ከወገኖች ጋር በመከበር ለመኖር እንችላለን::ሁላችንም መልካሙ ስራ ላይ ብቻ ብናተኩርስ?

መከራበዚህች ምድር ስትኖር ሰው በመሆንህ ብቻ የሚገጥሙህ የህይወት ውጣ ውረዶች ብዙ ናቸው። ነገሩን እንደ ክርስትያን ከወሰድከው ደግሞ ይብሳል፥ ሆኖም የሚታገልህን የመከራ ታላቅነት በፀሎት መ...
26/12/2021

መከራ
በዚህች ምድር ስትኖር ሰው በመሆንህ ብቻ የሚገጥሙህ የህይወት ውጣ ውረዶች ብዙ ናቸው። ነገሩን እንደ ክርስትያን ከወሰድከው ደግሞ ይብሳል፥ ሆኖም የሚታገልህን የመከራ ታላቅነት በፀሎት መልክ ለእግዛብሄር እያስታወስክ በማጉረምረም ጊዜህን አታባክን፥ ይልቁኑ ከባድ ለምትለው ፈተናህ የእግዛብሄርን ታላቅነት አውራለት።

አዲስ ቀን!!ሌላ ቀን መጥቷል።በእግዚአብሔር ቸርነት ፣ ፀሐይን ከአድማስ በላይ እያየን ነው።ፀሐይ በምትወጣበት ጊዜ፣ጨለማውን አሸንፈን ጉዙዋችንን እንድንቀጥል እድል ተሰጥቶናል።ማናቸውም ጨለማ...
25/12/2021

አዲስ ቀን!!
ሌላ ቀን መጥቷል።በእግዚአብሔር ቸርነት ፣ ፀሐይን ከአድማስ በላይ እያየን ነው።ፀሐይ በምትወጣበት ጊዜ፣ጨለማውን አሸንፈን ጉዙዋችንን እንድንቀጥል እድል ተሰጥቶናል።ማናቸውም ጨለማው እንዲውጠን ፣ከተኛንበት እንዳንነቃ ፣ጉዞዋችን እንዲሰናከል በብርቱ የሚሰሩ ሀይላት በአዱሱ ወቅት ላይ ደምቀን ስንሳፈፍ እያዩ ነው ።በመጨረሻም በእግዚአብሄር ቸርነት፣በማይቀየረው ኪዳኑ ውስጥ በትንሳኤው ሀይል ከተቆፈረልን መቃብር አምልጠናል። በዚህ በአዲሱ ቀን ደስ ይበላችሁ።ምክንያቱም አዲስ ቀን መጥቶልናል እና።

መልካሙን ስራ!ኤፌሶን 2: 10  እኛ ፍጥረቱ ነንና ፤ እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን።ስራ ለመፈለግ ሳይሆን ስራ ለ...
24/12/2021

መልካሙን ስራ!
ኤፌሶን 2: 10 እኛ ፍጥረቱ ነንና ፤ እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን።
ስራ ለመፈለግ ሳይሆን ስራ ለመስራት ወደዚች ምድር ተልከናል::የምንሰራው የተዘጋጀ ሲሆን አይነቱ መልካም ተብሎ ተገልፅዋል::መልካም ምን ማለት ነው ?ብለን ልንጠይቅ እንችላለን::ይሄ እንግዲህ ለራስ ፥ለቤተሰብ፥ለቤተክርስትያን ጠቃሚ የሆነ ለሁሉ የሚጨምረው ብቃት የያዘ ጥቅል መሆን የሚችል ማለት ነው::ሰው ሁሉ በያለበት መልካሙን ነገር ለሰው ልጆች ጥቅም ቢሰራ አጥብያችን፥ከተማችን ምን ልትመስል እንደምትችል እስቲ አስቡት:የመልካም ተከቃራኒ ክፋት ነው::ክፋት በህሊና ህግ የሚያሰቃይ፥ በሞራል ህግ የሚያሳፍር ፥በምድር ህግ የሚያስጠይቅ፥ በመንፈሳዊ ህግ ያልተሰጠን የስራ አይነተ ነው ::ስለዚህ እንደ አማኝ ባልተሰጠን የፀጋ አይነት ቀኑን ሙሉ ባንተጋ ከፈጣሪ ጋር በሰላም ከወገኖች ጋር በመከበር ለመኖር እንችላለን::ሁላችንም መልካሙ ስራ ላይ ብቻ ብናተኩርስ?

በእግዚአብሔር የሚታመን!መዝ 31:24  በእግዚአብሔር የምታምኑ ሁላችሁ ፥ በርቱ ልባችሁም ይጥና ።መቸም የሰው ልጅ ያለ እየመሰለ የለም::ከውጭ ሆነው ዉጭያዊ ማንነቱን ለሚያዩ ያለ ይመስላል ...
23/12/2021

በእግዚአብሔር የሚታመን!
መዝ 31:24 በእግዚአብሔር የምታምኑ ሁላችሁ ፥ በርቱ ልባችሁም ይጥና ።
መቸም የሰው ልጅ ያለ እየመሰለ የለም::ከውጭ ሆነው ዉጭያዊ ማንነቱን ለሚያዩ ያለ ይመስላል ፥ መኖር ማለት መተንፈስ ፥መብላት ፥መተኛት ከሆነ::አብዛኛው በአጥብያው ያለ የሚያገለግል ይምሰል እንጂ በልቡ ጥላ የሚሆነውን ያስሳል፥ በጌታ ያልረካች ነፍሱን ስራ በማባረር ፥ ገንዘብ በማባረር ሊያረካት ይሞክራል::የትም ሁኑ ፥ምንም ሁኑ መንፈሳዊው አለም አንድ ነገር ይጠይቃል፥ እምነታችሁ እግዛብሄር የሆነ ሌላ ምትመኩበት፥ የምትጠብቁት የሌላችሁ እናንተ በርቱ ይላል:: ለመበርታት የተጠሩ መለኮታዊ አቅም የተዘጋጀላቸው በእግዛብሄር የሚያምኑ እና የሚታመኑ ብቻ ናቸው::

ስለ አንተ አስብዋል!አምላክ ሁሉን የህይወታችንን ምእራፍ ከራሱ አላማ አንፃር ነው የሚመለከተው::በኑሮዋችን ውስጥ ተስፋው ሁሌም የሚያበራ ነው::የምታልፍበት ህይወት:ሁኔታዎች:ሰዎች የሚሉህ ተ...
22/12/2021

ስለ አንተ አስብዋል!
አምላክ ሁሉን የህይወታችንን ምእራፍ ከራሱ አላማ አንፃር ነው የሚመለከተው::በኑሮዋችን ውስጥ ተስፋው ሁሌም የሚያበራ ነው::የምታልፍበት ህይወት:ሁኔታዎች:ሰዎች የሚሉህ ተደማምሮ ግራ ሊያጋባህ ይችላል::ቢሆንም በድንግዝግዝ ውስጥ እንኳን ብትሆን ሰለ እናንተ የማስባትን ሀሳብ እኔ አውቃለሁ ያለውን እግዛብሄር ቃል አስብ ፣አሰላስል፣ አውጅ::
ኤር 29:11

Address

Hawassa, On The Road To Gudumale Park
Hawassa
P.O.BOX924

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Life Foundation Church, መሠረተ ሕይወት ቤተክርስቲያን Hawassa posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Life Foundation Church, መሠረተ ሕይወት ቤተክርስቲያን Hawassa:

Share