24/10/2021
02/2014 ዓ.ም sanbata... #ቅዱስ ሰንበት... Sabbath...
" እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፥ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤ እነሆም እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ። (የማቴዎስ ወንጌል 28:19-20) " አሁንስ ለምን ትዘገያለህ? ተነሣና ስሙን እየጠራህ ተጠመቅ ከኃጢአትህም ታጠብ።"(የሐዋርያት ሥራ 22:16)
" ከክርስቶስ ጋር አንድ ትሆኑ ዘንድ የተጠመቃችሁ ሁሉ ክርስቶስን ለብሳችኋልና።"(ወደ ገላትያ ሰዎች 3:27) " ወይስ ከክርስቶስ ኢየሱስ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ የተጠመቅን ሁላችን ከሞቱ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ እንደ ተጠመቅን አታውቁምን?"(ወደ ሮሜ ሰዎች 6:3) " ሰረገላውም ይቆም ዘንድ አዘዘ፥ ፊልጶስና ጃንደረባው ሁለቱም ወደ ውኃ ወረዱ፥ አጠመቀውም።"(የሐዋርያት ሥራ 8:38)
#ያመነ የተጠመቀ ይድናል ለቃ, 16:16 በደቡብ ኢትዮጵያ ሰበካ ሰሜን ምሲራቅ ሲዳማ አውራጃ የሰባተኛ ቀን አድቬንትስት ቤ/ክን የተፈጸመ የነብሳት ጥምቀት።
Ethiopia union mission North eastern Sidama district seventh day Adventists church Had babitazed 80 souls Praise lord for all souls gave to eternal life!
በዕለቱ የተጠማቅያን የመጡበት ቦታና ቁጥራቸው። (1, )ዲላ አፋራራ.............11 ( 2,) ሽሾ................12 : (3,) መስንቀላ...........12 (4, ) ሔዳ አላልቻ...........11 (5, )ድንቶ................3 (6, ) ጋጋዋ...................6 (7, )ዱባ.....................6 ( 8, )ቱሎ......................10 ( 9, )ለኩ.......................2 (10, )ፈሮ እድዎ...............4 (11, )ማንኖ አላልቻ. ..........3
አጠቃላይ ድምር =80 ነብሳት በዛሬዋ ቀን ወደ አድስ ህይወት ተቀላቅለዋል።
#ቅዱስ መጽሐፋዊ ጥምቀት የሚባለው ጌታ የሱስ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን በሙሉ ልብ አምኖ በወንዝ መጠመቅን ነው፡፡ ሐዋ. 8፡37-38፡፡ ጌታ የሱስም በተጠመቀ ጊዜ በዮርዳኖስ ወንዝ በዮሐንስ እጅ ተጠመቀ ማር.1፡9፡፡ ከጥምቀት ጋር በተገናኘ ሊስተዋል የሚገባው ጉዳይ፡- 1. ቃሉ ያመነ የተጠመቀም… ይላል፡፡ ማር.16፡16፡፡ ይህም ማለት ሰው ሊጠመቅ የሚችለው ካመነ በኋላ እንጂ ከማመኑ በፊት መጠመቅ የለበትም ነው፡፡ 2. አንድ ሰው በጌታ በየሱስ «አመንኩ» ብሎ ትዕዛዛቱንም ላይጠብቅ/ሊያምፅ «ተጠመኩ» ቢል የማይታዘዝ ሰው ሐሰተኛ ስለሆነ እምነቱም ጥምቀቱም ሐሰተኛ ይሆናል፡፡ ምክንያቱም ቃሉ፡- አውቄዋለሁ እያለ ትዕዛዛቱንም የማይጠብቅ ውሸተኛ ነው እውነትም በእርሱ ውስጥ የለም ይላልና፡፡ 1ኛ ዮሐ.2፡3-4፡፡ ስለዚህ ያ ሰው ቀድሞ ጌታ የሱስን ወደ ውስጡ መጋበዝ አለበት፡፡ ቃሉ፡- እውነትም በእርሱ ውስጥ የለም ይላልና፡፡ እውነት ጌታ የሱስ ነው፡፡
ይህን አውቀን በመንፈስ ቅዱስ ምሪት ሁላ ችንም የጥምቀት ምንነት ተረድተን ተጠምቀን የዘላለሙን ህይወት እንድንወርስ ጌታችን ስለረዳን ስሙ የተመሰገነ ይሁን።
:-Yk from Heda alalich SDA