Peace Mission Islamic association

Peace Mission Islamic association This is the official page of peace-mission Islamic association which is based in Ethiopia, Amhara regional state

30 Days until Ramadan!اللهم بلغنا رمضان
18/01/2026

30 Days until Ramadan!

اللهم بلغنا رمضان

ሙሐመድ ﷺየችግሮች ሁሉ መፍትሔ ❤اللَّهُمَّ صل عَلَى مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍإِنَّ اللَّهَ وَمَلَائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى ا...
09/01/2026

ሙሐመድ ﷺየችግሮች ሁሉ መፍትሔ ❤
اللَّهُمَّ صل عَلَى مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ
إِنَّ اللَّهَ وَمَلَائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ ۚ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا
አላህና መላእክቱ በነቢዩ ላይ የአክብሮት እዝነትን ያወርዳሉ፡፡ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በእርሱ ላይ የአክብሮት እዝነትን አውርዱ፡፡ የማክበርንም ሰላምታ ሰላም በሉ፡፡
(አል-አሕዛብ፡ 56)
#ሰለዋት

09/01/2026

የዒልሙ መሐንዲስ - ሸይኽ ሰዒድ አህመድ ሙስጠፋ !

ሸይኽ ሰዒድ አህመድ ሙስጠፋ በ1945 አ.ል በዋድላ ደላንታ ተወለዱ ። የተወለዱባት መንደር ስያሜ አቃዱር ይሰኝ ነበር ። ከአባታቸው አህመድ ሸይኽ ሙስጠፋ እና ከእናታቸው ተዋበች አጋሽ ነበር የተገኙት ።

ገና በለጋ እድሜያቸው በአካባቢያቸው በነበረ የመኖሪያ እና የእርሻ ቦታ እጥረት ምክንያትና የኑሮው ነገር ስላልገራላቸው ከመንደሩ ለቀው እንዲወጡ ግድ ሆነባቸው ። ከመንደራቸው የመኮብለል ጉዳይ ለእናታቸው ወ/ሮ ተዋበች አጋሽ እንዲህ በቀላል የሚታይ አልነበረም ። ከባለቤታቸው ጋር እስከመለያየት አደረሳቸው ። የኑሮ መላ ያስኮበለላቸው የሸይኽ ሰዒድ አባት ፣ ታላቅ ወንድምና አጎታቸው አካባቢውን ለቀው ወደመተከል ያቀናሉ ። ሸይኽ ሰዒድ ግን ከእናታቸው ጋር በመንደራቸው ጸኑ ።

አባታቸው ለደረስነት እንዲሁም ልጃቸው በኢልሙ ዘርፍ ውጤታማ እንዲሆኑ ልዩ ፍላጎት ነበራቸው ። በርሳቸው ግፊትና ተፅዕኖ ሸይኽ ሰዒድ የደረስነት ህይወት ጀመሩ ። መሰረታዊውን የፊቅህን ስርዓተ እውቀት ካጠናቀቁ በኋላ ወደ ቦረና ተጉዘው ለ3 ዓመታት ያክል የነህዉንና በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆነውም ቢሆን የተፍሲር ቂርዓታቸውን ቀጠሉ ።

በሀገራችን ኢትዮጵያ የሚሰጡ ኪታቦችን ካጠናቀቁ ቡሀላ ወደ አዲስ አበባ መጡ ። እዚህም የመጡበት ምክንያት ከዚህ ሀገር ወተው ወደ አረብ ሀገራት ተጉዘው የሀዲስ እንዲሁም ሌሎች ቂርአቶችን ለመቅራት አስበው ነበር ።

በወቅቱም ሀጂ ሙሐመድ ራፊዕ ከሳውድ አረቢያ ተመልሰው አንዋር መስጂድ ላይ ደረሶችን ሲያቀሩ የሚያቀሩበት ነበርና ያገኟቸዋል ። ሃሳባቸው ከሐጂ ሙሐመድ ራፊዕ ዘንድ ለመቅራት ነበር ። ቆይተው ሐጂ ሙሐመድ ራፊዕ ወደትውልድ መንደራቸው ይሄዱ ነበርና አልተሳካም ። ሸይኽ ሰዒድ ግን ቂርዓታቸውን ከሐጂ ሙሐመድ ወሌ ዘንድ ይቀጥላሉ ። ሐጂ ሙሐመድ ራፊዕ እስኪመለሱ ድረስ . . .!

ሐጂ ሙሐመድ ራፊዕም የጥቅምት ማገባደጃ ላይ ወደአዲስ አበባ ይመለሳሉ ። ሸይኽ ሰዒድ ወትሮም ጊዜያቸውን በአግባቡ የሚጠቀሙ ነበሩ ። ኩቱቡ ሲታን እሳቸው ጋር ቀርተው ማጠናቀቅ ቻሉ ። በማለዳው ክፍለ ጊዜ ደግሞ ከሐጂ ሙሐመድ ሳኒ ዘንድ ተፍሲርን ሙራጀዓ ሲያደርጉ ይቆያሉ ።

አዲስ አበባ የነበራቸውን ቆይታ እንደጨረሱ ወደ ትውልድ ስፍራቸው ሄደው የማስቀራት ፍላጎት የነበራቸው ቢሆንም እዚሁ አንዋር መስጂድ የነበሩት 3 ታላላቅ ዑለሞች ፍቃደኛ ሳይሆኑ ይቀራሉ ። ምክንያታቸው ደግሞ በወቅቱ የነበረው የደረሳ መጠን መብዛት ሸይኽ ሰዒድ እዚህ መቆየታቸውን ግድ ይል ነበር ።

ትዕዛዙን ተቀብለው ሸይኽ ሰዒድ ዒልምን ማቅራት ጀመሩ ። በቆይታቸው የማረፍያ ስፍራና የእለት ጉርስ ማግኘት በጣም አስቸጋሪ ሆኖባቸው እንደነበር ይናገራሉ ። በዚያ ወቅትም ቀኑን ወሎ ሰፈር ድረስ በእግራቸው በመጓዝ ልጆችን ያቀራሉ ። እዚያው ቤትም ምሽቱን በጥበቃነት ማገልገል ይጀምራሉ ።

በቀጣዩ የህይወት ምዕራፋቸው ለ15 አመታት አንዋር መስጂድ ዒልምን ሲያቀሩ ቆይተዋል ። ሸይኽ ሰዒድ በእድሜ ዘመናቸው በደማቁ ከሚወሱበት አበርክቷቸው መሐል በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያውን የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ማህበር ወይም በተለምዶ ሙነዘማን ማቋቋም ነበር ። እጅግ ብዙ ጥረትና ልፋት የታየበት ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች መብታቸው የሚጠይቁበትና ማንነታቸውን የሚያስከብሩበት ተቋም መሆን የቻለ 165 ያህል ቅርንጫፍ ማዕከላትን ማቋቋም የቻለ ነበር ። በጊዜው መንግስት ለተቋሙ ሕጋዊ እውቅናና ፈቃድ ሰጥቶ የነበረ ቢሆንም የኋላ ኋላ ስጋት ይሆናል በሚል አደረጃጀቱ እንዲፈርስ የተለያዩ ስራዎች ተሰርተዋል ።

ሸይኽ ሰኢድ አህመድ ሙስጠፋ በዚህ ሁኔታ ላይም ሆነው በ 5 መስጂዶች ላይ ተፍሲርን በማቅራት ሙሉ በሙሉ አጠናቀው የነበረ ሲሆን በኒ መስጂድ ፣ አንዋር መስጂድ ፣ ሀሺም መስጂድ ይገኙበታል ። በዚህ አጋጣሚ ኡምራ የማድረግ እድል ያገኙት ሸይኽ ሰዒድ አህመድ ሙስጠፋ ዑምራቸውን ፈጽመው ከ15 ቀናት በኋላ የመመለስ እቅድ ነበራቸው ። ያ ግን በተለያየ ምክንያት ሊሰምር አልቻለም ። እርሳቸው ሄደው ቀናት ባስቀጠሩበት አጋጣሚ አገር ውስጥ ነገሮች ተቀያይረዋል ።

ታዲያ በጊዜው አንድ ሁነት ይከሰትና ነገሮች መልካቸውን ይቀይራሉ ። የወቅቱ መንግስት በአንዋር መስጂድ እጅግ ብዙ ወጣቶችን ህይወት በመቅጠፍ እንዲሁም ሙስሊሞች ተለይተው ድብደባ እንደተፈጸማባቸው ፣ የተለያዩ መሻዒኾች እየታሰሩ የግድያ ፍርድም እየተፈረደባቸው እንደሆነና እሳቸውም በጥብቅ እየተፈለጉ እንደሆኑ ይሰማሉ ።

ሸይኽ ሰዒድም በነዚህና መሰል ምክንያቶች ሳዑዲ አረቢያ ይሰነብታሉ ። በዚህ ሁኔታ ቀናት ቀናትን እየተካ ወራትም ወራትን እየተኩ አመታት ተቆጠሩ ። ሸይኽ ሰዒድ የመኖሪያ ፍቃድ ስላልነበራቸው ከአደባባይ ተሸሽገው ከማንም ጋር ሳይገናኙ ለ 2 አመት ያክል ከቆዩ ቡሀላ ሳዑዲ አረቢያ ይኖሩ የነበሩት ሸይኽ አህመድ ሀዲ ሸይኽ ሰኢድን አፈላልገው ያገኟቸዋል ። ሸይኽ አህመድ ያላቸውን አቅም ያውቁ ስለነበር ወደ አራት የሚጠጉ የዓቂዳ ኪታቦችን እንዲያቀሩና የድምፃቸውም ቅጂ ወደ ኢትዮጵያ በካሴት መልክ ተዘጋጅቶ እንዲሰራጭ ያማክሯቸዋል ። ሸይኽ ሰዒድም በጣም ደስተኛ እንደሆኑ በመናገር ስራቸውን ይጀምራሉ ።

ቆይቶ ሙሉ ለሙሉ ስራቸውን በማጠናቀቅ ሸይኽ አህመድ ሙአሰተል ሀረመይን ከሚባል ድርጅት ጋር የነበራቸውን ትውውቅ ተጠቅመው የሸይኽ ሰዒድ አህመድ ድምፅ ተቀድቶ በካሴት መልክ ወደ ኢትዮጵያ እንዲሰራጭ ሆነ ። ስራቸው ተወዳጅነት ማትረፍ የቻለና በብዙዎች ዘንድ የሚወሳ መሆን ችሏል ። ሙስሊም ያልሆኑ ወገኖች ጭምር ወደው ያደምጡት እንደነበር ይወሳል ።

ሸይኽ ሰዒድ ሌላኛው ግዙፍ እድል ብለው የሚያነሱት አንጋፋው አፍሪካ ቲቪ ምስረታውን ያደርጋል ። እሳቸውም በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪው በሆነው ኢስላማዊ የሳተላይት የቴሌቭዥን ጣቢያ የቁርዓን ተፍሲርን ማስማር ጀመሩ ። የብዙዎች ዘንድ ተወዳጅ እና ተናፋቂ ሆኖ የብዙዎችን ልብ ከቁርዓን ጋር አዛምዷል ። በዚህ ሁሉ ውስጥ የ9 ልጆች አባት የሆኑት ሸይኽ ሰዒድ ቤተሰባቸውን አልዘነጉም ነበር ።

ከቅርብ ዓመታት በፊት ለ23 ዓመታት ርቀዋት ወደቆዩት አገራቸው በመመለስ ሙስሊሙን ማህበረሰብ ማገልገላቸውን ቀጥለዋል ። በአፍሪካ ቲቪ አል ፈታዋን ጨምሮ የተለያዩ ሸሪዓዊ መሰናዶዎች እያቀረቡ ያሉ ሲሆን አፍንጮ በር የሚገኘው የአቅሷ መስጂድ ዒማምና ኸጢብ በመሆን ከዚያን ባሻገር በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት የዑለሞች ምክር ቤት አባል በመሆን እያገለገሉ ይገኛሉ ።

አላህ ( ሱ.ወ ) ከመልካም አበርክቷቸው ጋር አጽንቶ በረዥም እድሜ በበረታ አፍያ ያቆያቸው ።

#አፍሪካቲቪ
#የህይወትጎዳና

30/12/2025

የቀድሞ የጦር ክንፉ ቃል አቀባይ አቡ ዑበይዳ መገደሉን ማረጋገጫ የሰጠው ሐማስ ተተኪውን ሠየመ

የፍልስጤሙ ሐማስ የጦር ክንፍ ቃል አቀባይ ሑዘይፋ ሰሚር ዓብደላህ አል ከሕሉት በእስራኤል ጦር መገደሉን በይፋ አረጋግጧል።

በቡድኑ መረጃ መሠረት፤ አቡ ዑበይዳ በሚል የጦር ሜዳ ሥም የሚታወቀው ሑዘይፋ፤ የተገደለው ባለፈው ዓመት ነሐሴ ወር ላይ ነው። ኅልፈቱ የተሰማው አቡ ዑበይዳ የፊት ገጽታው በአደባባይ ሳይታይ ቡድኑን በቃል አቀባይነት ያገለገለው ለሁለት ዐሥርት ዓመታት ነው።

ስለ ሕይወቱ ብዙም የሚታወቅ ነገር ባይኖርም እ.አ.አ በ2005 በሰጠው ቃለ መጠይቅ ላይ ቤተሰቡ በ1948 ነቅባ ወቅት በጽዮናዊ ሚሊሺያዎች በግዳጅ እንደተፈናቀሉ ተናግሯል። በወቅቱ በ20ዎቹ መጀመርያ ዕድሜ ላይ እንደነበር የገለጸው አቡ ዑበይዳ፤ የተወለደው በ1980ዎቹ አጋማሽ ነው።

ሚድል ኢስት ዐይ እንደዘገበው፤ ከመሞቱ በፊት እውነተኛ ማንነቱን የሚያውቁት ጥቂት ሰዎች ብቻ ነበሩ። አቡ ዑበይዳ በሁለተኛው ኢንቲፋዳ (2000-2005) ወቅት ለመጀመሪያ ጊዜ በይፋ ሲታይ የተቀበለው የጦር ሥም ነው። ይህ ሥያሜ ምናልባትም የተወሰደው የነቢዩ መሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ዕውቅ ወታደራዊ አዛዥ ከነበሩት አቡ ዑበይዳ ኢብኑ አል ጀራህ እንደሚሆን ይገመታል።

የቀድሞውን ቃል አቀባይ ኅልፈት ተከትሎ ቡድኑ የተተኪውም ሥም በተመሣሣይ አቡ ዑበይዳ እንደሚባል አስታውቋል። አዲሱ ቃል አቀባይ ከሑዘይፋ በተጨማሪ የቀድሞው የኢዘዲን አል ቀሳም ብርጌድ አዛዥ ሙሐመድ ሲንዋር በግንቦት ወር በእስራኤል ኃይሎች መገደሉንም አረጋግጠዋል። በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ የተገደለውን ራኢድ ሳዕድን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ ወታደራዊ መሪዎችም መሞታቸውን ተናግሯል። (ሚንበር ቲቪ)

★ ★ ★
Ethio Sat | 11545 | H | 45000
!

26/12/2025

ሙሐመድ ﷺ የነብያት አውራ ❤
اللَّهُمَّ صل عَلَى مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ
إِنَّ اللَّهَ وَمَلَائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ ۚ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا
አላህና መላእክቱ በነቢዩ ላይ የአክብሮት እዝነትን ያወርዳሉ፡፡ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በእርሱ ላይ የአክብሮት እዝነትን አውርዱ፡፡ የማክበርንም ሰላምታ ሰላም በሉ፡፡
(አል-አሕዛብ፡ 56)
#ሰለዋት

15/12/2025

In a world that grows numb to cruelty, be like Ahmed al-Ahmed, who ran toward danger to protect life.

That is Islam.

We mourn the victims of today’s attack in Australia and pray for safety and sanity everywhere.

May those who murder while cloaked in power or false righteousness leave no legacy worth repeating.

15/12/2025
15/12/2025

With Engr/Ustaz Bedru Hussein - በድሩ ሁሴን – I'm on a streak! I've been a top fan for 9 months in a row. 🎉

10/12/2025

With ሸይኸ ሙሓመድ ዘይን ዘህረዲን ኸሊል الشيخ/ محمدزين زهر الدين – I'm on a streak! I've been a top fan for 9 months in a row. 🎉

10/12/2025

ሐማስ ከእስራኤል ጋር እስከ ዐሥር ዓመት የሚዘልቀው 'ሁድናህ' እንዲፈረም ምክረ ሐሳብ አቀረበ

የፍልስጤሙ ሐማስ የእስራኤል ጦር ጋዛን ሙሉ ለሙሉ የሚለቅ ከሆነ ለዐሥር ዓመት የሚዘልቅ የተኩስ አቁም ዕቅድ (ሁድናህ) ምክረ ሐሳብ ለአደራዳሪዎች አቅርቧል። ቡድኑ መሣሪያዎቹን ወደ ምሽግ የመመለስ ፍላጎቱንም አስታውቋል።

ሚድል ኢስት ዐይ በሒደቱ ላይ የተሣተፉ ሥማቸው ያልተጠቀሰ ከፍተኛ የፍልስጤም ባለሥልጣንን ጠቅሶ እንደዘገበው፤ የቡድኑ ዕቅድ ባለፈው ሣምንት በካይሮ ለግብጽ፣ ኳታር እና ቱርክ አደራዳሪዎች ቀርቦ ተደምጧል። ቡድኑ ያቀረበው ሁድናህ በእስልምና ታሪክ ውስጥ በጦርነት ወቅት ሲተገበር የቆየ ነው። በታሪክ ከተመዘገቡት መካከል ነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) በሁደይቢያህ ዘመቻ ወቅት ከቁረይሽ ጎሳዎች ጋር የተፈራረሙት ተጠቃሽ ነው። ድርሣናት እንደሚያስረዱት ስምምነቱ 'ሱልህ' በመባል እንደሚጠራው ዘላቂ የሰላም ስምምነት አይደለም። ስልቱ አቅምን እንደገና በማደራጀት በተሻለ ሁኔታ ለመደራደር እንደ ረፍት የመውሰጃ አጋጣሚ ተደርጎ ይታሠባል።

እንደ ፍልስጤሙ ባለሥልጣኑ ገለፃ ሁድናህ ከተፈረመ የሐማስ ታጣቂዎች በእስራኤል ላይ ቃታ ከመሣብ ከመታቀብ ባለፈ የጦር መሣሪያዎቹ ተደብቀው ይቆያሉ። ቡድኑ የፈረመውን ቃል ኪዳን ተግባራዊ ማድረጉን አደራዳሪዎች በቀጥታ ቁጥጥር ያደርጋሉ። በዚህ ረፍት ከሁለት ዓመት በላይ በጦርነት ውስጥ ያለፈችው ጋዛና ሕዝቧ ከከበባና መፈናቀል ፋታ በመውሰድ ወደመልሶ ግንባታና መደበኛ አስተዳደር ትመለሣለች።

በቅርቡ በአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በቀረበው የጋዛ ተኩስ አቁም ስምምነት ትጥቅ ይፈታል ተብሎ የነበረው ሐማስ፤ እስካሁን ድረስ ሙሉ በሙሉ ሉዓላዊ በሆነው የፍልስጤም መንግሥት በዴሞክራሲያዊ መንገድ በተመረጠ አመራር ሥልጣን ካልሆነ በስተቀር የጦር መሣሪያዎቹን ለማስረከብ ፍቃደኛ አልሆነም። እንቅስቃሴው በእስራኤል ላይ የሚያካሂደው የትጥቅ ዘመቻ የሚጠናቀቀው የፍልስጤም መሬት ከወረራ ነጻ ሲሆን ብቻ መሆኑን በተደጋጋሚ በመሪዎቹ በኩል ይገልጻል።

ለሚድል ኢስት ዐይ የተናገሩት የፍልስጤም ከፍተኛ ባለሥልጣን፤ የቡድኑ መሪዎች የትራምፕ ስምምነት ሰነድ ላይ በተቀመጡት ሐሳቦች ሙሉ በሙሉ ባይስማሙም የፈረሙት ጦርነቱን የማስቆም ዋንኛ ግብ በማስቀመጥ ነው።

በትራምፕ የጋዛ ዕቅድ የእስራኤል ጦር ከተማው እንዲለቅ ቢሠፍርም አሁንም ድረስ ጦሩ የተኩስ አቁም ስምምነቱን በመጣስ 53 በመቶውን የጋዛ መሬት በቁጥጥር ስር ማዋሉም በዘገባው ተጠቅሷል። በተጨማሪም በአካባቢው የሰላም አስከባሪ ኃይል እንዲሠማራ ዕቅድ ቢቀርብም የተኩስ አቁም ስምምነቱ ዝርዝር ጉዳዮች እስካሁን ድረስ ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ ባለመደረጋቸው ወታደሮችን ለመላክ በግለጽ ፍቃደኛ የሆነ ሀገር አልተገኘም። የፍልስጤሙ ባለሥልጣን ስለ ጉዳዩ ሲናገሩ አደራዳሪዎቹ የሰላም አስከባሪውን ኃይል ሐሳብ በወረቀት ቢያቀርቡትም መሬት ላይ የሚታይ ነገር የለም።

ባለሥልጣኑ አያይዘው የገለጹት ሌላው ጉዳይ በአሁኑ ሰዓት በተለይ በአደራዳሪዎች በኩል የተኩስ አቁም ስምምነቱ የተጣሰው በእስራኤል ወገን መሆኑ ላይ ከመግባባት መደረሱን ነው። ሐማስ ፕሬዝዳንት ትራምፕ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ ግፊት ያሳድራሉ የሚል ዕምነት ቢኖረውም እስካሁን የተሰማ ነገር የለም። በሐማስ አዲስ የተኩስ አቁም ዕቅድ ላይ በእስራኤልና አሜሪካ በኩል የተሰጠ ምላሽ ስለመኖሩ ምንም አልተጠቀሰም። (ሚንበር ቲቪ)

በድረ ገጽ ያንብቡ፦ https://minbertv.com/?p=11017

03/12/2025

Address

Harbu

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Peace Mission Islamic association posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Peace Mission Islamic association:

Share