የጎንደር ህክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ግቢ ጉባኤ ገጽ

  • Home
  • Ethiopia
  • Gondar
  • የጎንደር ህክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ግቢ ጉባኤ ገጽ

የጎንደር ህክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ግቢ ጉባኤ ገጽ የጎ. ህ .ጤ .ሳ . ኮ ግቢ ጉባኤ በግቢ ጉባያችን የተከናወኑ ፣ እየተከናወኑ ያሉ ና ወደፊት የ ሚከናወኑ ተግባራትን እንዲሁም የበዓላት አከባበራችንን በፎቶ እና በምስል የተደገፈ መረጃ መስጠት

ድንቅ  የእመቤታችን ዝማሬ እነሆ።
27/08/2023

ድንቅ የእመቤታችን ዝማሬ እነሆ።

🔴 በማኅቶት ቲዩብ የተለቀቁ ተወዳጅ መዝሙሮችን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፡፡ 👇 👇 👇 https://bit.ly/3C2YHGpአዲስ ዝማሬ " ትእምርተ ኪዳን " ዘማሪት ጽዮን ዓለምሰገድ @-mahtot

እንኳን አደረሳችሁ፡፡የፊታችን ቅዳሜና እሑድ የግቢ ጉባኤያችንን ፳፰ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል በተለያዩ መርሃግብራት ልዑል እግዚአብሔር ቢወድና ቢፈቅድ እኛም ብንደርስ እናከብራለን፡፡በሩቅም በቅ...
20/11/2019

እንኳን አደረሳችሁ፡፡
የፊታችን ቅዳሜና እሑድ የግቢ ጉባኤያችንን ፳፰ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል በተለያዩ መርሃግብራት ልዑል እግዚአብሔር ቢወድና ቢፈቅድ እኛም ብንደርስ እናከብራለን፡፡
በሩቅም በቅርብም ያላችሁ የቀድሞ የግቢ ጉባኤያችን ተማሪዎች( ) እንዲሁም በአሁን ሰዓት በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ትምህርታችሁን በመከታተል ላይ የምትገኙ ውድ የተዋሕዶ ልጆች በዕለታቱ ጉባኤውን ትካፈሉ ዘንድ በክብር ተጠርታችኀል፡፡
:
መረጃውን ለሌሎች በማጋራት የመርሃግብሩ ተሳታፊ ያድርጉ፡፡

14/11/2018

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ዱ አምላክ አሜን✞
እንኳን ለቅድስት ቁስቋም ማርያም ዓመታዊ በሰላም አደረሳችሁ✞✝✞
"አብሬሽ ልመለስ"
ከክብር ማረፊያው ከገሊላው ቤትሽ
ሰማሁ መፍለስሽን ወደ ግብጽ ወደ ኩሽ
ፀሐይ ሲያከትራት ያቺን የበረሃ ዖፍ
ጼዋዌን ስትናፍቅ ላንዲት ቅጽበት ሳታርፍ
ሰማሁኝ ስደቷን መጠጊያ ሳታገኝ በልቤ ላይ ስታልፍ...ፈላሲተ ቁስቋም ወዴት ነው ሀገርዋ
ኀበ ሖረት ላቲ በብካይ እትልዋ
ናዛዚት እም ኃዘን ሁሉ ያላት ለማኝ
የምድረ በዳ ዖፍ ጎጆዋን እስካገኝ
መኃልየ ብካይ ኃዘንዋ እየሆነኝ.... እፈልጋታለሁ
እፈልጋታለሁ....እፈልጋታለሁ
እንዲያም ያጣኋት ለት..... ፈልጊኝ እላለሁ
አልያማ
ያለ ምዕራፈ ክብር....ያለ ነፍሴ አስኬማ
ያለ ብሔረ ሰላም ....ያለ ጽድቅ ከተማ
ያለ ጽናት አክሊል ..... ያለ ፍቅር ማማ
ምሕረትን ሲርበኝ ..... ይቅርታን ስጠማ
ከበረሃ እንዳልቀር .... ድምጼ ሳይሰማ.... እፈልጋታለሁ
እፈልጋታለሁ....እፈልጋታለሁ
እንዲያ ያጣኋት ለት..... ፈልጊኝ እላለሁ
ዋዕየ ፀሐይ ዘመዓልት.... ክምር ኃጢዓቴን ንጄ
የሌሊቱን ቁረ ገዳም ... ፈቃደ ሥጋውን ክጄ
ካንቺው ጋራ ልመለስ ..... ከግብጽ ተሰድጄ
" ውስተ ርስትኪ ሰድኒ... እም ብኄረ ዓለም ባዕድ
በቤተልሔም ቤትኪ …..አልቦ አመጻ ወሃይድ "
አ...ብ...ር...ሬ...ሽ.... አይደለም አብሬሽ ልመለስ
ክብርሽን አክብሬ ውድሽን ሳወድስ.... እያልኩ ሥሉስ ቅዱስ
ሥጋ ዓለሜን ጥዬ ከነፍስ ሀገር ልድረስ
አ...ብ...ር...ሬ...ሽ.... አይደለም አብሬሽ ልመለስ
የነፍሴ ወደቧ ወደ ልጅሽ ልድረስ
ያለ እርሱ እምነት የለም ያላንቺም ክርስቶስ
አ...ብ...ር...ሬ...ሽ.... አይደለም ካንቺው ጋር ከኋላ
መርተሽ አሳርፊኝ በብሔረ ተድላ
ለፈጣሬ ዓለማት አንቺ ነሽ መጾሩ
ለተስፋ ስዱዳን ህጽንሽ ነው አገሩ
የጢሮስ አምኃ ... ከቤተልሔም ግብጽ ... ተከትሎሽ ሲፈልስ
ከግብጽ ቤተልሔም .... ካንቺ ጋር ሲመለስ
የልጅሽ ፍጥረቱ እኔም ከዚያ እንዳላንስ
ምን ባልገባ እንኳን ስምሽን ባልቀድስ ..... ልጅሽን ባላወድስ
ጠልተሽ አትጣይኝ ፍኖትሽን ሳስስ
እነሆ ልጅ ልባል ጎልጎታ ልድረስ
አ...ብ...ር...ሬ...ሽ.... አይደለም አብሬሽ ልመለስ
ትተሺኝ አትውጪ ውስተ ምድረ ነኪር
ስደትን ታውቂያለሽ ተሰድጄ እንዳልቀር
መከራን ታውቂያለሽ ተመክሬ እንድኖር
አብሬሽ ልመለስ ወደ ነፍሴ ደብር
እንዳትረሺኝ ከመንገዱ .... አንቺ ቀሊል ደመና
ጥለሽኝ አትሂጂ ከበረሃው .... አማናዊት የሲና መና
በእቅፍሽ ያለው ህብስተ ሕይወት .... የምሕረት ዝናብ ነውና
ዘመንሽ ነውና ዘመኑ .... መጠንሽም ነውና መጠኑ
ለሥጋ ማረግ መሰላሉ .....ለቃል መውረድም ዙፋኑ
ያላንቺማ "እስከማዕዜኑ..."
እንዲህ እየተከዙ እንድያም እያዘኑ...
ጽድቅን እየገፉ ፍዳ እየመዘኑ
ያላንቺማ "እስከማዕዜኑ..."
በንሰሃ እንባ ኃጢዓትን ሳይከድኑ
ከነአንን ናፍቀው ግብጽን ቢኮንኑ
ከስጥመተ-ባህር ከጥፋት ላይድኑ
ከሀገር ተለይተው በስደት ቢጸኑ
ያላንቺማ "እስከማዕዜኑ..."
የበጎቹ መሰማርያ..... እምነ ጽዮን እያሉ
ካንቺ ነውና ሚጠለሉ ..... ከእቅፍሽ ነውና ሚውሉ
መፈውስ ነሽና ለቁስለ ነፍስ .....እባክሽን አዛኝቱ
አስከትለሽው ተመልሽ ልጅችን ጥሪው ለቤቱ
ሊቁ እንደነገረን ....
"ብጹዕ ዘርእየኪ በህልሙ ሌሊተ
አመ ትበርቂ በደብረ ምጥማቅ ሐምሰ ዕለታተ"
እኔም ደሞ ናፍቃለሁ ....አንዲት ነገር ልለምንሽ
በነፍሴ ላይ ስትበርቂ.... ጽልመት ግብሬ ፈርቶ እንዲሸሽ
አንድ ጊዜ ባይነ-ልቤ.... ላንዲት ቅጽበት በህልሜ ልይሽ....ልመለስ አብሬሽ!
በዲ/ን ዶ/ር ቴዎድሮስ በለጠ

14/11/2018
14/11/2018

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ዱ አምላክ አሜን✞
🔊አዋጅ...🔉አዋጅ...አዋጅ📢
👂ያልሰማህ ስማ 🗣የሰማህ ላልሰማው አሰማ...
🔁የሕዳር ጉባዔ ልዩ መልእክት ይዞ ሊሆንሎት ማማ...
🔜ከፊትዎ ቀርቧል እንዳያልፎትማ✝

❀እንኳን ለ #፳፯ኛ ዓመት የምሥረታ በዓላችን በሰላም አደረሳችሁ❀
🗒ሕዳር ፰ እና ፱(የፊታችን ቅዳሜ እና እሑድ) የሚካሄደው መንፈሳዊ ጉባዔ ላይ ተሳታፊ እንዲሆኑ በልዑል እግዚአብሔር ስም ተጋብዘዋል፡፡
ለቡ፡ ወዳጅዎን🗣👤👥 በመጋበዝ የሊቃውንቱን ጉባዔ እንዲካፈሉ ያድርጉ

join us 👇👇👇👇👇👇👇
👉 👈
👉 👈
👉 👈
👆👆👆👆👆👆👆

✞ወስብሐት ለእግዚአብሔር✞

06/11/2018

መንፈሳዊ ጉዞ

24/09/2018

መስቀል

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሰው ልጆችን ለማዳን የተሰቀለበት ቅዱስ መስቀል ሕሙማንን በመፈወሱ ምክንያት በርካታ አሕዛብ ክርስቲያን እንዲሆኑ አስችሏል፡፡ በተአምራዊነቱና በክርስቲያኖች ዘንድ ከፍተኛ ክብር የተሰጠው በመሆኑና ይህን የተመለከቱ አይሁድ ቅዱስ መስቀሉን በአንድ የቆሻሻ ማጠራቀሚያ ቦታ እንዲቀበር አደረጉ፡፡ የአካባቢው ነዋሪዎች በየቀኑ ቆሻሻ ስለሚጥሉበት ቦታው ወደ ተራራነት ተቀየረ፡፡ ምንም እንኳን መስቀሉን ለማውጣት ባይችሉም በኢየሩሳሌም የነበሩ ክርስቲያኖች ቦታውን ያውቁት ነበር፡፡ በሰባ ዓመተ ምሕረት በጥጦስ ወረራ ኢየሩሳሌም ስለጠፋች በዚያ የነበሩ ክርስቲያኖች ተሰደዱ፡፡ የተቀበረበትን ቦታ የሚያውቅ ባለመገኘቱ መስቀሉ ከ300 ዓመታት በላይ ተዳፍኖ /ተቀብሮ/ ኖረ፡፡



በ326 ዓ.ም. የንጉሥ ቆስጠንጢኖስ እናት ንግሥት ዕሌኒ ቅዱስ መስቀሉን ለመፈለግ ወደ ኢየሩሳሌም ጉዞ አደረገች፡፡ እዚያም ደርሳ ጉብታ የሆነውን ሁሉ ብታስቆፍር መስቀሉ ያለበትን ቦታ ማግኘት አልቻለችም፤ ሰውም ብትጠይቅ የሚያውቅ አልተገኘም፡፡ በመጨረሻም የመስቀሉ መገኘት የእግዚአብሔር ፈቀድ ነበርና አንድ ይሁድ አረጋዊ የታሪክ አዋቂና ሽማግሌ አግኝታ ቅዱስ መስቀሉ የተቀበረበትንና የተጣለበትን አካባቢ ያውቅ ዘንድ ጠየቀችው፡፡ ሽማግሌውም “አንቺም በከንቱ አትድከሚ ሰውንም አታድክሚ እንጨት አሰብስበሽ እጣን አፍሽበት በእሳትም አያይዢው የእጣኑ ጢስ ወደላይ ወጥቶ ወደታች ሲመለስ አቅጣጫውን አይተሽ አስቆፍሪው በዚህ ምልክት ታገኚዋለሽ” አላት እርሷም ያላትን ሁሉ አደረገች። እንጨት ደምራ በዚያ ላይም ዕጣን ጨምራ በእሳት ለኮሰችው፤ የዕጣኑ ጢስ ወደ ላይ ወጥቶ ወደ ታች ሲመለስ መስቀሉ ያለበትን ቦታ በጣት ጠቅሶ እንደማሳየት ያህል አመለከተ፡፡ ንግሥት ዕሌኒም ጢሱ ያረፈበት ቦታ ቅዱስ መስቀሉ የተቀበረበት እንደሆነ አመነች፡፡ ይህ ይሁድ አረጋዊ የታሪክ አዋቂና ሽማግሌ በኋላ በክርስቶስ አምኖ ተጠምቋል፤ ስሙም ኪርያኮስ ተብሏል፡፡



በዚህም መሠረት ከመስከረም 17 ቀን አስጀምራ እስከ መጋቢት 10 ቀን ሌሊትና ቀን ለሰባት ወራት ያህል የጉድፍን ኮረብታ ቆፍረው ቆሻሻውንም ካስወገዱ በኋላ ሦስት መስቀሎች ተገኙ ፡፡ የጌታም መስቀል ሙት በማስነሣቱ ተለይቶ ታውቋል፡፡ መስቀሉ የተገኘው መጋቢት 10 ቀን 326 ዓ. ም. ነበር፡፡ ቅድስት ዕሌኒ ይህን ተአምር በማየቷ እጅግ ደስ አላት፡፡ ሕዝቡም ሁሉ መስቀሉን እየዳሰሱ ኪርያላይሶን እያሉም በመዘመር ደስታና ሐሴት አደረጉ፡፡ ቀኑ መሽቶ ጨለማ በሆነ ጊዜም የኢየሩሳሌም ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መቃርዮስና ንግሥት ዕሌኒ፣ ሠራዊቱና ሕዝቡ በሰልፍ በችቦ መብራት መዝሙር እየዘመሩ ቅዱስ መስቀሉን ወደ ቤተ ክርስቲያን ወስደው በአንድ የጸሎት ቤት አኖሩት፡፡ በኋላም በንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ዕብነ መሠረት ወይም የመሠረት ድንጋይ ተቀምጦ ለመሰቀሉ መታሰቢያ ቤተክርስቲያን ተሠርቶ ተመርቆ የገባው (ቅዳሴ ቤቱ) የተከበረው መስከረም 17 ቀን 327 ዓ.ም. ነው፡፡ በቤተ ክርስቲያናችን ሁለቱም ዕለታት ይከበራሉ፤ በደማቅ ሁኔታና በመጀመሪያ ደረጃ የሚከበረው ግን መስከረም 17 ነው፡፡ ይህም የሆነበት ምክንያት መጋቢት 10 ቀን ሁልጊዜም በዐቢይ ጾም ወቅት የሚውል መሆኑና ለመስቀሉ የተሠራው ቤተ መቅደስ የከበረው መስከረም 17 በመሆኑ ነው፡፡



ይህ ዕለት ከ300 ዓመታት በላይ ጠፍቶ የነበረውን ቅዱስ መስቀል በንግሥት ዕሌኒ አማካኝነት መገኘቱን የምንዘክርበት በዚህም ደስ የምንሰኝበት ዕለት ነው፡፡ ይህን መነሻ በማድረግ በኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ደመራ በመደመር የመስቀል በዓል በታላቅ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዐት ይከበራል፡፡

09/12/2016

ዘመነ አስተምሕሮ (አስተምህሮ) የመጀመሪያ ክፍል ዲሴምበር 7, 2016/in ወቅታዊ ትምህርት /by Mahibere Kidusanኅዳር ፳፰ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም የተወደዳችሁ የድረ ገጻችን ተከታታዮች! ኅዳር ፫ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም ባቀረብነው ዝግጅት እንዳስታወስነው በቤተ ክርስተያናችን የዘመን አከፋፈል መሠረት ከኅዳር ፮ ጀምሮ እስከ ታኅሣሥ ፯ ወይም ፲፫ ቀን ድረስ ያለው ወቅት ዘመነ አስተምሕሮ ይባላል፡፡ ትርጕሙም በሃሌታው ‹ሀ› (‹‹አስተምህሮ›› ተብሎ) ሲጻፍ የቃለ እግዚአብሔር...

03/12/2016

+*"+ እንኩዋን ለታላቁ ሰማዕት "ቅዱስ መርቆሬዎስ (ፒሉፓዴር)" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ +"*+

"ኅዳር 25"

+*" ቅዱስ መርቆሬዎስ ኃያል "*+

=>ለክርስትና ሃይማኖት የሚከፈል ትልቁ ዋጋ ሰማዕትነት ነውና ቤተ ክርስቲያን ለምስክሮቿ ሰማዕታት ልዩ ክብር አላት:: ከኮከብ ኮከብ እንዲበልጥ ሁሉ ከሰማዕታትም ቅዱስ ጊዮርጊስን እና ቅዱስ መርቆሬዎስን የመሰሉት ደግሞ ክብራቸው በእጅጉ የላቀ ነው::

+ቅዱስ መርቆሬዎስን ብዙ ጊዜ ሊቃውንት "ካልዕ (ሁለተኛው) ሊቀ ሰማዕታት" ሲሉ ይገልጹታል:: ጥንተ ነገሩስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-

+በ2ኛው መቶ ክ/ዘመን መጨረሻ አካባቢ ከሮም ግዛቶች በአንዱ (አስሌጥ) ከአባቱና ከሚስቱ ጋር የሚኖር "አሮስ" የሚሉት ሰው ይኖር ነበር:: ሚስቱ ደም ግባት የሠመረላት: እርሱም ደግነት ያለው ሰው ቢሆኑም የሚያመልኩት ግን ጣዖትን ነበር::

+አንድ ቀን አሮስ ሚስቱን ከቤት ትቶ ለአደን ከአባቱ ጋር ወጣ:: እንደ ልማዳቸው ወጥመዱን አስተካክለው ተደበቁ:: የወጥመዱ ደወል ሲያቃጭል: "እንስሳ ተያዘልን" ብለው ሲሯሯጡ ዐይናቸው ያየው ነገር በድንጋጤ እንዲፈዙ አደረጋቸው:: 2 ገጻተ ከለባት በወጥመዱ ውስጥ ተይዘው ነበር::

+እነዚህ ፍጡራን ሰዎች ናቸው:: ግን ባልታወቀ የተፈጥሮ አጋጣሚ እንደዚህ እንደ ሆኑ ይታመናል:: ግን እጅግ ግዙፍ: ከአንገታቸው በላይ እንደ ውሻ: ወገባቸው እንደ ሰው: ጉልበታቸው እንደ አንበሳ ሲሆን ታችኛው እግራቸው የጋለ የናስ ብረት ነው የሚመስል::

+እነዚህን ፍጡራን ሰማያዊ ካልሆነ ምድራዊ ፍጡር አይችላቸውም:: አንበሳና ነብርን እንኩዋ እንደ ጨርቅ በጣጥሰው ይጥሏቸው እንደ ነበር ይነገራል:: ዐይናቸው እንደ እሳት ይነድ ስለ ነበር ማንም ትክ ብሎ ሊያያቸው አይችልም::
ምሥጢራቸውን ግን የሚያውቀው የፈጠራቸው አምላክ
ነው::
+ወደ ቀደመ ነገራችን እንመለስና:- አሮስና አባቱ ባዩአቸው
ጊዜ ደንግጠው ወደቁ:: ገጻተ ከለባቱ የብረት ወጥመዱን
እንደ
ክር በጣጥሰው የአሮስን አባት በቅጽበት በሉት:: አሮስን
ሊበሉት ሲሉ ግን ድንገት ቅዱስ መልአክ ወርዶ በእሳት
ሰይፍ
አጠራቸው::
+"ከእርሱ የሚወጣ ቅዱስ ፍሬ አለና እንዳትነኩት"
አላቸው::ወዲያውም መልአኩ ያንን ኃይለኝነታቸውን
አጠፋው:: በዚህ ጊዜ
2ቱም ወደ አሮስ ሒደው ሰገዱለት:: አሮስም ወደ ቤቱ
ወስዶም ደበቃቸውና የሆነውን ሁሉ ለሚስቱ ነገራት::
+ጥቂት ቆይታም ጸንሳ ወለደች:: ልጃቸውን ፒሉፓዴር
(ፒሉፓተር) ሲሉ ስም አወጡለት:: ትርጉሙም "መፍቀሬ
አብ-የአብ
ወዳጅ" ማለት ነው:: ከዚያም አሮስ ሚስቱን ልጁንና 2ቱን
ገጻተ ከለባት ይዞ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሒዶ ተጠመቀ::
+አበው ካህናት እሱን 'ኖኅ': ሚስቱን 'ታቦት': ልጁን
ደግሞ 'መርቆሬዎስ' ሲሉ ሰየሟቸው:: መርቆሬዎስ
ማለትም "ገብረ
ኢየሱስ ክርስቶስ-የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ" እንደ
ማለት
ነው::
+ከዚያም ደስ እያላቸው: ክርስቶስን እያመለኩ: ነዳያንን
እያሰቡ: ልጃቸውን መርቆሬዎስን አሳደጉ:: ነገር ግን
የገጻተ
ከለባት ወሬ በመሰማቱ ንጉሡ 'ካላመጣሃቸው' አለው::
ኖኅ ጸልዮ ወደ ኃይለኝነታቸው መልሷቸው ስለነበር ፊታቸው
ገና
ሲገለጥ ብዙ አሕዛብ በድንጋጤ ሞቱ::
+ንጉሡም ስለ ፈራ ኖኅን የጦር መኮንን አደረገው::
በጦርነት ጊዜም ገጻተ ከለባቱ ኃይላቸው ስለሚመለስ
ተሸንፎ አያውቅም
ነበር:: አንድ ጊዜ ግን 2ቱን ገጻተ ከለባት ንጉሡ አታሎ
ወሰዳቸው:: ሃይማኖታቸውን ሊያስክዳቸው ሲል "እንቢ"
በማለታቸው አንዱ ሲገደል ሌላኛው አምልጦ ጠፋ::
+በዚያ ወራትም ኖኅ ለጦርነት ወጥቶ ተማረከ:: ንጉሡ
ደግሞ ታቦትን 'ላግባሽ' ስላላት የ5 ዓመት ልጇን ቅዱስ
መርቆሬዎስን ይዛ ተሰደደች:: በስደት ጥቂት እንደ ቆየች
ግን ባሏን ኖኅን አየችው::
+እርሷ ብታውቀውም እርሱ ዘንግቷት ነበር:: በኋላግን
በሕጻኑ መርቆሬዎስ አማካኝነት ማስታወስ በመቻሉ ደስ
አላቸው:: በዚያው በሮም ዙሪያ ሳሉም አንዱ ገጸ ከልብ
መጥቶ አገኛቸው:: በዚህም ምክንያት በስደት ሃገርም
መኮንን ሆኖ
ተሾመ::
+በዚያም ቤተ ክርስቲያንን አንጾ: ቤቱን ቤተ ነዳያን
አድርጐ ኖኅ ለዓመታት ኖረ:: ቅዱስ መርቆሬዎስ ወጣት
ሲሆንም
ወላጆቹ ታቦትና ኖኅ ዐረፉ:: እርሱ ከባልንጀራው ገጸ ከልብ
ጋር ሆኖ በጾምና ጸሎት ሲኖር ስለ አባቱ ፈንታ የጦር መሪ
አደረጉት::
+በጦርነትም እጅግ ኃያል: በሰው ዘንድም ፍጹም
ተወዳጅ:የጾምና የጸሎት ሰው ሆነ:: ያን ጊዜ ግን ዳክዮስ
ንጉሡ
ክርስቶስን በመካዱ ምዕመናን ላይ ሞት ታወጀ:: በጊዜው
ደግሞ የበርበር ሰዎች በሮም መንግስት ላይ ጦርነትን
በማንሳታቸ
ውዳኬዎስና ቅዱስ መርቆሬዎስ ለጦርነት ወጡ::
+ነገር ግን በርበሮች እንደ አሸዋ ፈሰው ብዛታቸውን ሲያይ
ንጉሡ ደነገጠ:: ለማግስቱ ቀጠሮ ተይዞ ቅዱስ
መርቆሬዎስ
ሲጸልይ ቅዱስ ገብርኤል ወርዶ ሰይፍ ሰጠው::
+በማግስቱም 'ምን ይሻላል?' ሲባል ቅዱስ መርቆሬዎስ
"እኔ የክርስቶስ ባሪያ ነኝና ብቻየን እቁዋቁዋማቸዋለሁ"
ቢል
ሳቁበት::
+እርሱ ግን በጥቁር ፈረሱ (አብሮት ያደገ ነው) ተጭኖ
በርበሮችን "ጠብ ይቅርባችሁ: በሰላም ሒዱ" ቢላቸው
ተሳለቁበት:: ያን ጊዜም ጸሎት አድርሶ የመልአኩን ሰይፍ
ሲመዘው ብዙዎቹ ወደቁ:: ከበርበሮችም ለወሬ ነጋሪነት
እንኳ
የተረፈ የለም ::
+ነገሩ በሮም ሲሰማ ታላቅ ሐሴት ሆነ:: ዳሩ ግን ከሃዲው
ዳኬዎስ 'ድሉ የጣዖቶቼ የነ አዽሎን ነው' በማለቱ ቅዱስ
መርቆሬዎስ ሲያዝን አደረ::
+በ3ኛው ቀንም 'ለጣዖት ሠዋ' የሚል ትዕዛዝ ከንጉሡ
ዘንድ መጣ:: ቅዱሱ ግን ወደ አደባባይ ሔደ:: የክብር
ልብሱንና
መታጠቂያውን አውልቆ በንጉሡ ፊት ወረወረው::
+"ሃብትከ ወክብርከ ይኩንከ ለኃጉል: ሊተሰ ክብርየ
ክርስቶስ ውዕቱ (ለእኔስ ክብሬ ክርስቶስ ነውና ንብረትህ
ለጥፋት
ይሁንህ)" ሲልም ንጉሡን በአደባባይ ዘለፈው::
ዳኬዎስም በቁጣ እሳት አስነድዶ: የብረት አልጋውንም
አግሎ ቅዱስ
መርቆሬዎስን በዚያ ላይ አስተኛው::
+ያም አልበቃ: ወታደሮች እየተፈራረቁ ሲደበድቡት ደሙ
ፈሶ እሳቱን አጠፋው:: ለዚያ ነው ሊቃውንት:-
"አመ አንደዱ ላእሌከ ውሉደ መርገም:
እምቅሡፍ አባልከ እንተ ውኅዘ ደም:
አርአያ ዝናም ብዙኅ አጥፍኦ ለፍህም" ያሉት::
+ከዚያም ወስደው ወኅኒ ቤት ውስጥ ጣሉት:: ክርስቶስን
ያስክደው ዘንድ በረሃብ: በግርፋት: በእሳት: በስለትም
አሰቃየው
:: በመጨረሻ ግን አሰቃይተው እንዲገድሉት ወደ እስያ
ሰደደው:: በስፍራውም ብዙ አሰቃይተው ኅዳር 25 ቀን
አንገቱን
ሰይፈውታል::
+እርሱ ካረፈ በኋላም የተባረከ ፈረሱ ለዓመታት ወንጌልን
ሰብኳል:: አረማውያንንም ከአፉ በወጣ እሳት አጥፍቷል::
ተአምረኛውና ኃያሉ ሰማዕት ቅዱስ መርቆሬዎስ በ200 ዓ/
ም እንደ ተወለደ: በ220 ዓ/ም መከራ መቀበል እንደ
ጀመረና በ
225 ዓ/ም ሰማዕት እንደሆነ ይታመናል::



=>አምላከ ቅዱስ መርቆሬዎስ በከበረ ቃል ኪዳኑ
ይጠብቀን::ከርስቱም አያናውጠን:: ከበረከቱም ይክፈለን::

=>ኅዳር 25 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ መርቆሬዎስ ሰማዕት
2.ቅዱሳን ታቦትና ኖኅ (ወላጆቹ)
3.ቅዱስ ሮማኖስ

"" ከክርስቶስ ፍቅር ማን ይለየናል!"" ሮሜ ፰:፴፭

>

03/12/2016

ጾመ ነቢያት (የገና ጾም) ኖቬምበር 24, 2016/in ወቅታዊ ትምህርት /by Mahibere Kidusanኅዳር ፲፭ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም ጾመ ነቢያት በየዓመቱ ከኅዳር ፲፭ ቀን ጀምሮ እስከ በዓለ ልደት ዋዜማ ድረስ የሚጾም፤ ከሰባቱ አጽዋማት መካከል አንደኛው ጾም ነው፡፡ እግዚአብሔር አምላክ ዓለምን ለማዳን ሲል የሰውን ሥጋ ስለ መልበሱ፤ ወደ ግብጽ ስለ መሰደዱ፤ በባሕረ ዮርዳኖስ ስለ መጠመቁ፤ በትምህርቱ ብርሃንነት ጨለማውን ዓለም ስለ ማብራቱ፤ ለሰው ልጆች ድኅነት ልዩ ልዩ…

01/12/2016

የክርስቶስ ቤተሰቦች፤የእናታችን የቅድስተ ቅዱሳን፤ንጽህተ ንጹሀን እመአምላክ ወላዲተ አምላክ የ አደራ ልጆች፤የ ቅዱሳን ወዳጆች እንደምን ከረማችሁ?ምስጋና የባህሪው የሆነ የአባቶቻችን አምላክ እግዚአብሔር፥ከእናቱ ከቅድስት ድንግል ማርያም እንዲሁም በ ጸጋው ከፍ ካደረጋቸው ቅዱሳን ጋር የከበረ የተመሰገነ ይሁን።
የተወደዳችሁ ወንሞችና እህቶች ሆይ፦ ይህ የጎ/ህ/ጤ/ሳ/ኮ ግቢ ጉባዔ ፌስ ቡክ ገጽ ከተመሰረተ ጀምሮ ወደ 4 ሺ የሚጠጋ ላይክ(like) ያገኘ ሲሆን ከዚህ በበለጠ ተደራሽ እንዲሆን comment፣ like ወይም share እንዲሁም invite በማድረግ ሌሎች ወንድሞችና እህቶች እንዲጋሩት በማድረግ የበኩልዎን ድርሻ እንድያበረክቱ ተጋብዘዋል።
ግቢ ጉባዔው

Address

Gondar

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የጎንደር ህክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ግቢ ጉባኤ ገጽ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to የጎንደር ህክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ግቢ ጉባኤ ገጽ:

Share