ደ/መ/ቅ/ቂርቆስ/ሰ/ት/ቤት ጎንደር

ደ/መ/ቅ/ቂርቆስ/ሰ/ት/ቤት ጎንደር befor 1950 EC

''ስቅለት'' ቀጥታ ስርጭት ከደብረ መንክራት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተ ክርስቲያን ጎንደር
10/04/2026

''ስቅለት'' ቀጥታ ስርጭት ከደብረ መንክራት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተ ክርስቲያን ጎንደር

የጌታችን ስቅለት ከጎንደር ደብረ መንክራት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን

05/04/2026
እንኳን አደረሳችሁ!!
05/04/2026

እንኳን አደረሳችሁ!!

የሰማዕታቱን በዓል በጎንደር ደብረ መንክራት ቅዱስ ቂርቆስ መጠው ያክብሩ ከበዓሉም በረከትን ያግኙ።አራዳ ከድሮው መናሀሪያ
22/01/2026

የሰማዕታቱን በዓል በጎንደር ደብረ መንክራት ቅዱስ ቂርቆስ መጠው ያክብሩ ከበዓሉም በረከትን ያግኙ።አራዳ ከድሮው መናሀሪያ

🗓ታኅሣሥ 11/፲፩/ ቅዱስ አባት በኪሞስዚህች ዕለት ታላቁ አባት ቅዱስ አባ በኪሞስ ዕረፍቱ ነው፡፡ ይኸውም ቅዱስ ከደቡባዊ ግብጽ መጺል ከምትባል አውራጃ የተገኘ ታላቅ አባት ነው፡፡ እርሱም ...
20/12/2025

🗓ታኅሣሥ 11/፲፩/
ቅዱስ አባት በኪሞስ
ዚህች ዕለት ታላቁ አባት ቅዱስ አባ በኪሞስ ዕረፍቱ ነው፡፡ ይኸውም ቅዱስ ከደቡባዊ ግብጽ መጺል ከምትባል አውራጃ የተገኘ ታላቅ አባት ነው፡፡ እርሱም የአባቱን በጎች የሚጠብቅ እረኛ ነበር፡፡ ዕድሜውም 12 ዓመት በሆነው ጊዜ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ መጥቶ በሰው አምሳል ተገለጠለትና ‹‹በአንድነት ሄደን እንመነኩስ ዘንድ ትሻለህ?›› አለው፡፡ በኪሞስም በዚህ ደስ ተሰኝቶ ሁሉቱም ተስማምተው አብረው ወደ ገዳመ አስቄጥስ ገቡ፡፡ በዚያም ሦስት አረጋውያን መነኮሳት አገኙና አባ በኪሞስ ከእነርሱ ጋር 24 ዓመታትን ኖረ፡፡
ከዚህም በኋላ አባ በኪሞስ ከዚያ ተነሥቶ የሦስት ቀን ጎዳና ተጓዘና ሩቅ ወደሆነ በረሃ ሄደ፡፡ በዚያም ሰይጣናት በእሪያዎችና በዘንዶዎች አምሳል ሆነው መጡበት፡፡ ሊነክሱትም አፋቸውን ከፍተው በከበቡት ጊዜ እርሱ ግን የአጋንንት ሥራ መሆኑን ዐውቆ በእግዚብሔር ኃይል እፍቢልባቸው እንደትቢያ ተበተኑ፡፡ እርሱም ወንዝ አግኝቶ ሰባት ሰባት ቀን እየጾመ በዚያ ሦስት ዓመት ኖረ፡፡ በሱባኤው መጨረሻ ላይ በእጁ ቴምር በተአምራት መልቶ ስለሚገኝ እርሱን ይመገባል፡፡ ቅዱሱም በሌሊት ሁለት ሺህ አራት መቶ ጊዜ በቀንም እንዲሁ ሁለት ሺህ አራት መቶ ጊዜ አቡነ ዘበሰማያትን ይጸልያል፡፡ ከዚህም በኋላ 40 40 ቀን እየጾመ 24 ዓመታትን በታላቅ ተጋድሎ ኖረ፡፡ አርባውም ቀን ሲፈጸም አንድ ጊዜ ይመገባል፡፡ ከዚህም በኋላ ቆዳው ከአንጥንቱ እስኪጣበቅ ድረስ አንድ ጊዜ እስከ ሰማንያ ቀን ጾመ፡፡ በዚህም ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ አባ በኪሞስ የሚበላውንና የሚጠጣውን ሰማያዊ የሕይወት ምግብና መጠጥ አምጥቶ መገበው፡፡ ያንንም መልአክ ያመጣለትን ምግባ መጠጥ አባ በኪሞስ እስካረፈበት ጊዜ ድረስ ብዙ ዓመታት ሲመገበው ኖረ፡፡
በአንደኛውም ቀን በሌሊት ጌታችን ለአባ በኪሞስ ተገልጦለት ወደ አገሩ እንዲመለስ ነገረው፡፡ እርሱም ወደ ሀገሩ ተመልሶ በዚያች ትንሽ በዓት አበጅቶ መኖር ሲጅር ብዙዎች ወደ እርሱ መጥተው ፈውስን የሚያገኙ ሆኑ፡፡ እርሱም ጣዕም ባለው አንደበቱ ወንጌልን እያስተማራቸው ድውያንንም ሁሉ የሚፈውሳቸው ሆነ፡፡ በአንዲት ዕለትም የታዘዘ መልአክ መጥቶ አባ በኪሞስን ነጥቆ ወስዶ ወደ ኤፍራጥስ ምድር አደረሰው፡፡ የዚያች አገር ሰዎች ሕግን በመተላለፍ ከእውነተኛ ሃይማኖት ወጥተው ነበርና፡፡ አባ በኪሞስም አስተምሮ ወደ ቀናች ሃይማኖትና ወደ በጎ ምግባር መለሳቸውና ወደ ሀገሩ ተመለሰ፡፡ በአንዲት ዕለትም ሸጦ የዕለት ምግቡን ያገኝ ዘንድ አገልግሎችን ተሸክሞ ወደ ከተማ ሲሄድ በጎዳና ላይ ደክሞት አገልግሎቹን አስቀምጦ ያርፍ ዘንድ ተቀመጠ፡፡ ወዲያውም ከአገልግሎቹ ጋር የእግዚአብሔር ኃይል ተሸክሞ ወስዶ ከሚሸጥበት ቦታ አደረሰው፡፡
በአንደኛውም ቀን ታላቁ አባት አባ ሲኖዳ ከፍተኛ የዕንቁ ባሕርይ ምሰሶ በራእይ አየና ‹‹ይህ ታላቅ ግሩም የሆነ ምሰሶ ምንድነው?›› ብሎ ደነገጠ፡፡ የታዘዘ መልአክ ተገለጠለትና ‹‹ይህ አባ በኪሞስ ነው›› አለው፡፡ አባ ሲኖዳም አባ በኪሞስን ያገኘው ዘንድ ወደ እርሱ አገር በእግሩ ተጓዘ፡፡ ከዚያም በፊት ከቶ አላየውም ነበር፡፡ ሄዶም ባገኘው ጊዜ ሁለቱ ቅዱሳን ሰላምታ ተሰጣጡና የእግዚአብሔርን ነገር እየተነጋገሩ አብረው እየጸለዩ ጥቂት ቀን ቆዩ፡፡ በአንዲት ዕለት አብረው ሲጓዙ አንድን የሞተ ሰው ራስ ቅል አገኙና አባ ሲኖዳ በበትሩ ነቅነቅ አደረገውና ‹‹ምውት ሆይ! ያየኸውን ትነግረን ዘንድ በጌታችን ስም ተነሥ›› አለው፡፡ ወዲውም ነፍሱ ወደ ዐፅሙ ተመልሳ ሥጋ ለብሶ ተነሣና ሰገደላቸው፡፡ በሲኦል ያየውንም ሁሉ በዝርዝር ነገራቸው፡፡ በየወገናቸው በሲኦል ውስጥ የሚሠቃዩትንና እርሱም የማያምን አረማዊ መሆኑን ነገራቸው፡፡ ዳግመኛም ‹‹ክብር ይግባውና በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ያመኑ ትእዛዙን ግን ያልጠበቁ በአሕዛብ ሥራባ በአረማውያን ርኩሰት የኖሩ በሲኦል ከእኛ በታች የሚኖሩ ክርስቲያኖች አሉ›› ብሎ ነገራቸው፡፡ ቅዱሳኑም ‹‹በል ተመልሰህ ተኛ›› አሉትና እንቀድሞው ሆነ፡፡ ከዚህም በኋላ አባ ሲኖዳ አባ በኪሞስን ተሰናብቶ ወደ አገሩ ተመለሰ፡፡
አባ በኪሞስም የዕረፍቱ ጊዜ ሲደርስ አገልጋዩን ጠርቶ የሥጋውን መቅበሪያ ቦታ አሳየው፡፡ ወዲያውም በሆድ ዝማ ሕመም ጥቂት ታመመና፡፡ ቅዱሳንም ከተለያየ ቦታ በአንድነት ወደእርሱ ሲመጡ በመንፈስ ተመለከተ፡፡ቅዱሱ 58 ዓመት በገዳም በምንኩስና ሥራ ተጠምዶ ኖሮ በሰባ ዓመቱ ነፍሱን በእግዚአብሔር እጅ ሰጠ፡፡ ቅዱሳን መላእክትም በዝማሬ ወደ ሰማያዊት ኢየሩሳሌም አሳረጓት፡፡

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ቅዱስ ጸሎት ይማረን አሜን፡፡

† ደ/መ/ቅ/ቂርቆስ/ሰ/ት/ቤት ጎንደር †
† Telegram (https://t.me/StKirkose_Sunday_School) † Facebook

 !" **"ውድ እህቶቻችን! በእምነት ጉዞአችን ልንጠነክር፣ ልምዶቻችንን ልንካፈል እና መንፈሳዊ ጥበብን ልንቀስም የምንችልበት ልዩ ጉባኤ አዘጋጅተናል። በእግዚአብሔር ፊት ያለው ዋጋችን ታላቅ...
11/12/2025

!" **"ውድ እህቶቻችን! በእምነት ጉዞአችን ልንጠነክር፣ ልምዶቻችንን ልንካፈል እና መንፈሳዊ ጥበብን ልንቀስም የምንችልበት ልዩ ጉባኤ አዘጋጅተናል። በእግዚአብሔር ፊት ያለው ዋጋችን ታላቅ ነውና። በዚህ ጉባኤ ላይ በመገኘት የሕይወትን መሠረት አጥብቀን እንያዝ፤ የቤታችንና የወደፊት ሕይወታችን መልካም መሠረት እንሁን! ሁላችሁም ተጋብዛችኋል!"

 "የናግራን ሰማዕታት" የአገረ ናግራን ሰማዕታት አባታቸውም ቅዱስ ኂሩት ይህም ዮስጢኖስ ለቊስጥንጥንያ በነገሠ በአምስተኛው ዓመት ለኢየሩሳሌም አባ ዮሐንስ ለእስክንድርያ አባ ጢሞቴዎስ ለቊስን...
05/12/2025


"የናግራን ሰማዕታት"
የአገረ ናግራን ሰማዕታት አባታቸውም ቅዱስ ኂሩት ይህም ዮስጢኖስ ለቊስጥንጥንያ በነገሠ በአምስተኛው ዓመት ለኢየሩሳሌም አባ ዮሐንስ ለእስክንድርያ አባ ጢሞቴዎስ ለቊስንጥንጥንያም አባ ጢሞቴዎስ ለአንጾኪያ አባ አውፍራስዮስ ሊቃነ ጳጳሳት ሁነው ሳለ በኢትዮጵያም ጻድቁ ካሌብ ነግሦ ሳለ በዚያን ወራት ለአይሁድ ስሙ ፊንሐስ የሚባል አይሁዳዊ ነገሠ።

በመጀመርያ ግን ሳባ የተባለች አገር በኢትዮጵያ ነገሥታት እጅ ውስጥ ነበረች የሮም ነገሥታት አስባስያኖስና ጥጦስ ከኢየሩሳሌም አይሁድን በአሳደዷቸው ጊዜ ይቺን ሳባን አይሁድ ወረሷት። በውስጧም በኢየሱስ ክርስቶስ የሚያምኑ ብዙዎች ክርስቲያኖች በሚኖሩባት ታላቅ ከተማ አለች ይህም የተረገመ አይሁዳዊ ፊንሐስ ሊአጠፋት በመጣ ጊዜ የዚችን የከበረች አገር በመስቀል ምልክት በዙሪያዋ ያለ ቅጽርዋን በበሮቿና በግንብ አጥርዋ ላይ ያሉ ብዙ አርበኞች ሠራዊትን አይቶ በምንም ምክንያት ሊገባባት ስለአልተቻለው ተቆጣ። እግዚአብሔር አጽንቷታልና ነገር ግን በውጭ ያገኛቸውን ገበሬዎች ገደለ ታናናሾችንም ማርኮ ለባሮቹ ሰጣቸው።

ይህም ዲያብሎስን የሚመስለው አይሁዳዊ የኦሪትና የነቢያት ፈጣሪ በሆነ በእግዚአብሔር ስም እየማለ በተንኰል መልእክትን ላከ እንዲህም አላቸው "እኔ ከእናንተ ጋር ጠብ አልሻም ከአገር ሰው አንዱን እንኳ ማጥፋት አልፈልግም ነገር ግን የከተማዋን አሠራርዋን አደባባዮቿን ገበያዎቿን ማየት እሻለሁ" ለአገር ሰዎችም የተናገረው እውነት መስላቸው። የካዕቢ ልጅ አባት ኂሩት "ይህን አይሁዳዊ አትመኑት ሐሰተኛ ነውና ደጁንም አትክፈቱለት" አላቸው አባት ኂሩትንም አልሰሙትም ደጁንም ከፈቱለትና ሰዎች ገንዘባቸውን እንዲዘርፋአቸው አዘዘ። ሁለተኛም ነባልባሉ ወደ አየር እስቲደርስ እሳትን አንድደው የአገሪቱን ኤጲስቆጶስ አባ ጳውሎስን እንዲአመጡት አዘዘ እርሱ እንደ ሞተም በነገሩት ጊዜ ዐፅሙን ከመቃብር አውጥቶ አቃጠለው።

ከዚህም በኋላ ቀሳውስትን ዲያቆናትን መነኰሳትን፣ አንባቢዎችንና መዘምራኑን በቀንና በሌሊት መጻሕፍትን በማንበብ የሚተጉትን ሰበሰበ እነርሱንም ከእሳት ውስጥ ጨመራቸው ቊጥራቸው አራት ሺህ ሃያ ሰባት ነፍስ ሆነ ክርስቲያኖችን በዚህ ሊአስፈራራቸው አስቧልና። ዳግመኛም የብረት ዛንጅር በቅዱስ አባት ኂሩት አንገት ውስጥ እንዲአስገቡ እጆቹንና እግሮቹንም እንዲአሥሩት አዘዘ ታላላቆችንና የአገሩን መኳንንትንም እንዲአሥሩአቸው ክርስቶስን የማይክደው ሁሉ እንዲህ ተሠቃይቶ በክፋ አሟሟት ይሞታል የሚል ዐዋጅ ነጋሪ እየጮኸ በከተማው ውስጥ እንዲአዞቸው አዘዘ።

ቅዱሳን ክርስቲያን ወገኖች በሰሙ ጊዜ እንዲህ እያሉ ጮኹ "እኛ ያመንበትንና በስሙ የተጠመቅንበትን ክብር ይግባውና ክርስቶስን አንክደውም ይህ ርጉም አይሁዳዊም ሰምቶ ወንዶችና ሴቶችን ወጣቶችንና ሕፃናትን ሽማግሎችን ሁሉንም እንዲገድሉ አዘዘና ገደሉአቸው ቊራቸውም አራት ሺህ ሁለት መቶ ኃምሳ ሁለት ነፍስ ሆነ።

ከዚህም በኋላ የቅዱስ ኂሩትን ሚስት ቅድስት ድማህን ከሁለት ሴቶች ልጆቿ ጋር ያዟት እነርሱም በቤታቸው መስኮት ከሚገባው በቀር ፀሐይ ያልነካቸው ናቸው ደርሰውም በአይሁዳዊ ንጉሥ ፊት በቆሙ ጊዜ እርሱም ሃይማኖታቸውን ያስክዳቸው ዘንድ በብዙ ተንኮል ሊሸነግራቸው ጀመረ እምቢ ባሉትም ጊዜ የራሳቸውን መሸፈኛ እንዲገልጧቸው አዘዘ የአገር ሴቶችም እስከ ሚያለቅሱ ድረስ ከልጆቿም የምታንስ አንዲቱ ዕድሜዋ ዐሥራ ሁለት ዓመት የሆነ ከንጉሡ ፊት ላይ ምራቋን ተፋችበት። ወታደሩም አይቶ ሰይፋን መዝዞ አንገቷን ቆረጠ የእኅቷንም አንገት ቆረጠ። ድማህ የልጆቿን ደም እንዲአጠጧት አዘዘ እርሷም ቀምሳ "የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ አመሰግንሃለሁ እንደቊርባን መሥዋዕት የሆነውን የልጆቼን ደም እኔ ባሪያህ እንድቀምስ አድርገሃልና" አለች። በዚያንም ጊዜ ርሷንም በሰይፍ አንገቷን እንዲቆርጡ ዳግመኛ አዘዘ ተጋድሎአቸውንም ፈጸሙ።

ከዚህም በኋላ ቅዱስ ኂሩትን ከአሥር ቤት እንዲአመጡት ንጉሥ አዘዘ ከርሱም ጋር አንድ ሺህ አርባ እሥረኞች ሰዎች አሉ ሃይማኖቱንም ይተው ዘንድ አስገደደው። ቅዱስ ኂሩትም ንጉሡን እንዲህ አለው "ክብር ይግባውና ጌታዬን ኢየሱስ ክርስቶስን እያመለክሁት ስኖር ሰባ ስምንት ዓመት ሆነኝ እስከ አራት ትውልድ ለማየትም ደርሼአለሁ ዛሬም ስለ ከበረ ስሙ ምስክር ሁኜ ስሞት እጅግ ደስ ይለኛል። እኔኮ አስቀድሜ መሐላህን እንዳያምኑ ለወገኖቼ ነግሬአቸው ነበር አንተ ሐሰተኛ ነህና ነገር ግን ይህ ሁሉ በእግዚአብሔር ፈቃድ ነው የሆነው ለዚህም ተጋድሎ ላደረሰኝ ለእርሱ ምስጋና ይሁን" ንጉሡም ይህን ሰምቶ ተቆጣ ወደ ወንዝም ወስደው በዚያ አንገቱን እንዲቆርጡት አዘዘ።

ቅዱስ አባት ኂሩትም በሰማ ጊዜ ደሰሰ አለው የሮምንና የኢትዮጵያን መንግሥት ያጸና ዘንድ የተረገመ አይሁዳዊውን መንግሥት ያጠፋ ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ ሕዝቡንም ባረካቸው። ከእርሳቸው ጋር በሰላምታ ተሰናበታቸው ከዚህም በኋላ የቅዱሳኑን ራሶቻቸውን ቆረጧቸው በዚያም የአምስት ዓመት ልጅ ያላት አንዲት ክርስቲያን ሴት ነበረች ከቅዱሳን ደም ወስዳ ተቀባች ልጅዋንም ቀባችው ወታደሮችም አይተው ከእሳት ጨመርዋት ልጅዋን ግን አይሁድ ወደእነርሱ ወስደው ወደ ንጉሥን አቀረቡት ንጉሡም "እኔን ትወዳለህ? ወይስ ክርስቶስ የሚሉትን?" አለው ሕፃኑም "እኔስ የእጁ ሥራ ነኝና ክርስቶስን እወደዋለሁ ይልቅስ ልቀቀኝ ወደ እናቴ ልሒድ" አለው በከለከለውም ጊዜ እግሩን ነከሰው አምልጦም ሩጦ ከእሳቱ ውስጥ ገባ። ሁለተኛም የዐሥር ወር ሕፃን እንደተሸከመች አንዲትን ሴት አመጧት እርሷም "ልጄ ሆይ ላዝንልህ አልቻልኩም" አለችው ያ ሕፃንም "እናቴ ሆይ በፍጥነት ወደ ዘላለም ሕይወት እንሒድ ይቺን እሳት ከዛሬ በቀር አናያትምና" አላት በዚያንም ጊዜ ከልጅዋ ጋር ወደ እሳት ውስጥ ተወረወረች።

የክርስቲያን ወገኖችም ይህን አይተው እኩሌቶቹ ወደ እሳት እኩሌቶቹም ወደ ሰይፍ ተቀዳደሙ የአይሁድ ጉባኤ ዕጹብ ዕጹብ ብለው እስኪያደንቁ ድረስ ከዚህም በኋላ እሳቱ በሰማይ ውስጥ መልቶ አርባ ቀን አርባ ሌሊት ታየ። የአይሁድ ንጉሥ ፊንሐስም ወደአገሩ በሔደ ጊዜ ወደ ነገሥታቱ ሁሉ በኃይሉ እየተመካ ላከባቸው የሮሜ ንጉሥ ዮስጢኖስም ሰምቶ ወደ እስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት ወደ አባ ጢሞቴዎስ ላከ በአገረ ናግራን ለሚኖሩ የክርስቲያን ወገኖች ደማቸውን ይበቀል ዘንድ ለኢትዮጵያ ንጉሥ ለካሌብ መልእክት እንዲልክ ነው።

የኢትዮጵያ ንጉሥ ካሌብም መልእክት በደረሰው ጊዜ ፈጥኖ ተነሣ በዋሻ ከሚኖር ከአባ ጰንጠሌዎን በረከትን ተቀብሎ ከብዙ ሠራዊት ጋር በመርከቦች ተጭኖ ሔደ በደረሰም ጊዜ የሳባን ንጉሥ የፊንሐስን አገር አጠፋ ሰውም ሆነ እንስሳም ሆነ ሸሽቶ የሚያመልጥ እንኳ ምንም ምን ሳይቀር አጠፋቸው የናግራንን ከተማ ሕንፃዋን አደሰ የሰማዕታትንም መታሰቢያ አቆመ። ከዚህም በኋላ ወደ ሮሜ ንጉሥ ዮስጢኖስ ወደ እስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት አባ ጢሞቴዎስ የምሥራች ላከ እነርሱም ሰምተው እጅግ ደስ አላቸው እግዚአብሔርንም አመሰገኑት። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በእሊህ በናግራን ሰማዕታት ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
† † †✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ † † †

† ደ/መ/ቅ/ቂርቆስ/ሰ/ት/ቤት ጎንደር †
† Telegram † Facebook †

ክፍል ሁለትመርቆሬ በዚያ ስላልተገኘ ለጣዖታቱ ዕጣን በማሳረጉ እንዳልተባበረ ንጉሡ ሲያውቅ መልእክተኞችን ልኮ አስመጣው፤ ንጉሡም ‹‹ከእኔ ጋር ለምን አታጥንም›› ባለው ጊዜ ቅዱስ መርቆሬዎስ ...
04/12/2025

ክፍል ሁለትመርቆሬ በዚያ ስላልተገኘ ለጣዖታቱ ዕጣን በማሳረጉ እንዳልተባበረ ንጉሡ ሲያውቅ መልእክተኞችን ልኮ አስመጣው፤ ንጉሡም ‹‹ከእኔ ጋር ለምን አታጥንም›› ባለው ጊዜ ቅዱስ መርቆሬዎስ ትጥቁንና ልብሱን አውልቆ ከወረወረለት በኋላ ‹‹ክብር ይግባውና አምላኬ ኢየሱስ ክርስቶስን ፈጽሞ አልክደውም፤ ለረከሱ ጣዖቶችህም አልሰግድም›› አለው፤ ንጉሡም ተናዶ ልዩ ልዩ በሆኑ ሥቃዮችም እጅግ አሠቃየው፡፡ ንጉሡም ስለ መርቆሬዎስ ብለው የሀገሩ ሰዎች እንዳይነሡበት ፈርቶ በብረት ችንካር ቸንክሮ የቀጵዶቅያና የእስያ ክፍል ወደ ሆነች ወደ ቂሳርያ ከደብዳቤ ጋር ላከው፡፡ በዚያም እጅግ ካሠቃዩት በኋላ ንጉሡ ዳኬዎስ እንዳዘዘ ኅዳር ፳፭ ቀን አንገቱን በሰይፍ ቆረጡት እና የሰማዕትነት ተጋድሎውን ፈጸመ፤ የሕይወትንም አክሊል ተቀዳጀ፤ በዓለሙ ሁሉ አብያተ ክርስቲያናት ታነጹለት፤

እግዚአብሔርም ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተአምራትን በቅዱስ መርቆሬዎስ ስም አደረገ፡፡

ከብዙ ተአምራቱም አንዱ የቂሳርያውን ሊቀ ጳጳስ ባስልዮስን ረድቶ ከሃዲውን ዑልያኖስን የገደለበት ነው፤ ዑልያኖስ ነግሦ የክብር ባለቤት ጌታችንን ክዶ ጣዖታትን ማምለክና ክርስቲያኖችን ማሠቃየት ጀመረ፡፡ የቂሳርያው ሊቀ ጳጳስ ባስልዮስም አስተምሮ ሊመልሰው ወደ ንጉሡ ቢመጣ ክብር ይግባውና ዑልያኖስ ጌታችንን ሰድቦ ባስልዮስንም አሠረው፡፡

ባስልዮስም በእሥር ቤት ሳለ በቅዱስ መርቆሬዎስ ሥዕል ፊት ጸለየ፤ ሥዕሉም ወዲያው ተሠወረው፤ ያንጊዜም ወደ ከሃዲው ንጉሥ ዑልያኖስ ዘንድ ሄዶ በጦር ወግቶ ገደለውና ወዲያው ወደ ቦታው ተመለሰ፤ ከጦሩም አንገት ደም ይንጠፋጠፍ ነበር።

ቅዱስ ባስልዮስም ከሃዲውን ንጉሥ እንደገደለው ዐውቆ ‹‹የክርስቶስ ምስክር ጌታዬ ሆይ የእውነት ፀር የሆነ ዑልያኖስን ገደልከውን›› አለው፤ ሥዕሉም ያን ጊዜ አዎን እንደሚል ራሱን ዘንበል አደረገ። ቅዱስ ባስልዮስም ደስ ብሎት እግዚአብሔርን አመሰገነ፤ ሌላው ሰማዕት ቅዱስ መርቆሬዎስ በተአምሩ ከእስልምና እምነት መልሶ ክርስቲያን ያደረገው አንድ እስላም ሰው አለ፡፡ ይኸውም የቅዱስ መርቆሬዎስ ቤተ ክርስቲያኑ በተሠራችበት በምስር ሀገር የሚኖር ከመሳፍንት ወገን የሆነ ወጣት ነበረ፤ ከብዙ ሰዎችም ጋር ሆኖ ወደ መሐመድ መቃብር ለመሄድ እንዳሰበ ለአባቱ ሲነግረው ስንቅ ሰንቀው በሰላም ወደ መካ መዲና ሸኙት፤ መካ ደርሰውም ሥራቸውም ፈጽመው ወደ ቤታቸው እየተመለሱ ሰባት ቀን ተጓዙ፤ በሌሊትም ሲጓዙ ስለ ሥጋዊ ግዳጁ ያ እስላም ወጣት ከግመል ላይ ወርዶ ለመጸዳዳት ዘወር አለ፡፡ እነርሱም አብሯቸው የሚጓዝ መስላቸው ስለነበር ባልንጀሮቹም በበረሃው ውስጥ ትተውት ሄዱ፤ እርሱም ወዴት እንደሚሄድ ስላላወቀ አራዊትም እንዳይበሉት ፈርቶ እጅግ ደነገጠ፡፡በዚያም ጊዜ በምስር አገር በአባቱ ቤት አቅራቢያ ያለች የሰማዕቱ የቅዱስ መርቆሬዎስን ቤተ ክርስቲያን አስታውሶ በልቡ ቅዱስ መርቆሬዎስን እንዲያድነው በመለመን ተሳለ፤ ወዲያውም ቅዱስ መርቆሬዎስ በፈረሱ ተቀምጦ ወደ እርሱ መጣና ‹‹ከወዴት ነህ? ከዚህ በረሃ ውስጥስ እንዴት ጠፋህ?›› አለው፤ ወጣቱ እስላምም የሆነውን ነገረው፡፡

ቅዱስ መርቆሬዎስም ‹‹ና በኋላዬ በፈረሱ ላይ ተፈናጠጥ›› አለውና በአየር ላይ እየበረረ በምስር ሀገር ወዳለች የቅዱስ መርቆሬዎስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ እንደ ዐይን ጥቅሻ አደረሰውና እንደተዘጋች በውስጧ አስገባውና ከእርሱ ተሰወረ፡፡ይህም ወጣት በኋላ አምኖ ተጠምቆ ብዙ ሰማዕትነት ተቀብሏል፤ ገዳምም ገብቶ ብዙ ከተጋደለ በኋላ እንደገና ወደ ሀገሩ ተመልሶ ብዙዎችን ወደ ክርስትና መለሰ፡፡

የሰማዕቱ ቅዱስ መርቆሬዎስ አማላጅ ነትና ተራዳኢነት አይለየን፤ አሜን!

04/04/2025


Address

Gondar

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ደ/መ/ቅ/ቂርቆስ/ሰ/ት/ቤት ጎንደር posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share