የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት/Central Gondar sunday school unity

  • Home
  • Ethiopia
  • Gondar
  • የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት/Central Gondar sunday school unity

የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት/Central Gondar sunday school unity ይህ የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ይፋዊ የፌስ ቡክ ገጽ ነው።

29/05/2026
የማዕ/ጎ/ሀ/ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የሰ/ት/ቤቶችን  ቀን የፊታችን እሑድ ግንቦት 23 ከቀኑ 7 ሰዓት ላይ በሀገረ ስብከት አዳራሽ ይከናወናል።ስለሆነም ሁላችን እንገኝ:ላልሰሙት በማሰ...
27/05/2026

የማዕ/ጎ/ሀ/ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የሰ/ት/ቤቶችን ቀን የፊታችን እሑድ ግንቦት 23 ከቀኑ 7 ሰዓት ላይ በሀገረ ስብከት አዳራሽ ይከናወናል።
ስለሆነም ሁላችን እንገኝ:ላልሰሙት በማሰማት መንፈሳዊ ኃላፋነታችን እንወጣ።

ለነገ እሑድ ተጠርታችኋል
28/03/2026

ለነገ እሑድ ተጠርታችኋል

ምስጋና ዘበዓለ ጥምቀት ከሰ/ት/ቤቶች አንድነት ላለፊት ሦስት ተከታታይ የጥምቀት ክብረ በዓል ቀናት ረድኤተ አግዚአብሔርን አጋዥ በማድረግ ድካሙን ተቋቁማችሁ :እግዚአብሔርን በዝማሬ ስታገለግሉ...
20/01/2026

ምስጋና ዘበዓለ ጥምቀት
ከሰ/ት/ቤቶች አንድነት

ላለፊት ሦስት ተከታታይ የጥምቀት ክብረ በዓል ቀናት ረድኤተ አግዚአብሔርን አጋዥ በማድረግ ድካሙን ተቋቁማችሁ :እግዚአብሔርን በዝማሬ ስታገለግሉ ለነበራችሁ የሰ/ት/ቤት አባላት እውነተኛ በረከትን የሚያድል የቅዱሳን አምላክ ልዑል እግዚአብሔር በረድኤቱ ይጎብኝልን አንድነታችንንም ይጠብቅልን እያልን ይህን አገለግሎት በስፋት እና በጥራት ማስቀጠል እንዳለብን በእጅጉ የጠቆመ ሁኗል።

በእነዚህ ቀናትም በዝማሬ እና በልዩ ልዩ መደቦች በአስተባባሪነት ላገለገላችሁ አባላት ይልቁንም ቤተ ክርስትያናችንን በሰፊው የሚያስተቸውን እና መስተካከል ያለበትን ጥምቀትን ተተርሶ የሚካሄደው ጭፈራን ለማስቀረት ስታገለግሉ ለነበራችሁ አባላት እግዚአብሔር በበረከት ይጎበኛችሁ ዘንድ ምኞታችን ነው።የተሰራው ስራም እንደጅማሮ ጥሩ የሚባል እና ማሻሻል ያለብንን ብዙ ክፍተት እንድንመለከትበት የረዳን ስለሆነ በሰፊው አሳይቶናል።

በመጨረሻም የሰ/ት/ቤት አንድነቱ ከበዓለ ጥምቀት ስራ ባሻገር አጠቃላይ ሰ/ት/ቤቶችን በማስተባበር ትልልቅ ስራዎች ይዞ ለመንቀሳቀስ በአዲስ መልኩ የጀመረ መሆኑን ከወዲሁ እንገልጻለን።

በድጋሚ በአገልግሎት ለተሳተፋችሁ ለሁሉም የሰ/ት/ቤት አባላት እና ምዕመናን ምስጋናችንን እናቀርባለን።

ከጥምቀት በኋላ ያለውን ቀሪ ሰዓት ሕዝበ ክርስትያኑ በአለማዊ ዘፈን እና ጭፈራ ከሚያሳልፍ በመንፈሳዊ መልኩ አክብሮ የበዓሉን በረከት እንዲሳተፍ በሚል የተዘጋጀ ልዩ መርሐግብር።
17/01/2026

ከጥምቀት በኋላ ያለውን ቀሪ ሰዓት ሕዝበ ክርስትያኑ በአለማዊ ዘፈን እና ጭፈራ ከሚያሳልፍ በመንፈሳዊ መልኩ አክብሮ የበዓሉን በረከት እንዲሳተፍ በሚል የተዘጋጀ ልዩ መርሐግብር።

የማ/ጎንደር የሰ/ት/ቤቶች አንድነት በወቅታዊ የቤተ ክርስተሰያናችን ፈተናዎች ዙሪያ ከአባላቱ ጋር በትናትናው ዕለት በ28/03/2018 ዓ.ም በ3ት የሥልጠና ማዕከላት  ሰፊ ውይይቶችን እና ሥ...
08/12/2025

የማ/ጎንደር የሰ/ት/ቤቶች አንድነት በወቅታዊ የቤተ ክርስተሰያናችን ፈተናዎች ዙሪያ ከአባላቱ ጋር በትናትናው ዕለት በ28/03/2018 ዓ.ም በ3ት የሥልጠና ማዕከላት ሰፊ ውይይቶችን እና ሥልጠናዎችን አድርጓል።
ሥልጠናው የቤተ ክርስትያናችን ሀገረ አቀፍ ፈተናዎችን በሰፊው የዳሰሰ እና በልዩ ሁኔታም በጎንደር እና አካባቢዋ ምን እየተደረገ ነው በሚለው ላይ ያጠነጠነ ሲሆን እንደ አንድ የሰ/ት/ቤት አባል ከእኛ ምን ይጠበቃል የሚለው የተገለጸበት ሁኗል።
በሥልጠናው መጨረሻም የመፍትሔ አቅጣጫ እና የቀጣይ ስራዎች ምን መሆን እንዳለባቸው በውይይት በሰፊው ተነስቶ እንደ አቋም ተይዟል።

በመርቲ ወረዳ የሚኖሩ 5 ኦርቶዶክሳውያን መገደላቸው እና 3 መታገታቸው ተነገረ።በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት መርቲ ወረዳ በሚገኘው ጋዶ ቀበሌ የሚኖሩ ኦርቶዶክሳውያን በትናንትናው ዕለት ጥቅም...
04/11/2025

በመርቲ ወረዳ የሚኖሩ 5 ኦርቶዶክሳውያን መገደላቸው እና 3 መታገታቸው ተነገረ።

በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት መርቲ ወረዳ በሚገኘው ጋዶ ቀበሌ የሚኖሩ ኦርቶዶክሳውያን በትናንትናው ዕለት ጥቅምት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 6፡00 ሰዓት በኋላ 5 ምእመናን የእርሻ ሥራቸውን አጠናቀው ምሳቸውን እየበሉ ባሉበት ጊዜ በታጠቂዎች በተከፈተባቸው የተኩስ ጥቃት መገደላቸውን ለማኅበረ ቅዱሳን ሚዲያ የደረሰን መረጃ ያሳያል፡፡

በተጨማሪም ከተገደሉት ውጪ ሌሎች 3 ምእመናን ደግሞ ታግተው የተወሰዱ ሲሆን እስከ አሁንም የደረሰቡት እንዲሁም ያሉበት ሁኔታ አይታወቅም ተብሏል፡፡

ይህን የምእመናኑ የግድያ እና የአፈና ተግባር ከሰሞኑ በሀገረ ስብከቱ እንደነበረው ሁሉ ተባብሶ የቀጠለ መሆኑን በመረጃው ተነግሯል፡፡

በተለይም ላለፉት ሁለት ዓመታት የገጠር ቀበሌው እና በውስጡ የሚኖሩ ምእመናን ከስጋት ነጻ ሆነው ኖረው አያውቁም፡፡

የተገደሉት ምእመናን ሥርዓተ ቀብራቸው በአቦምሳ ከተማ በሚገኘው በደብረ ገነት ትንሣኤ ብርሃን መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን እንደተፈጸመ በመረጃው ተመላክቷል፡፡

ምንጭ:-EOTCMK TV

✝️የኃዘን ዜና ✝️በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በምንጃር ሽንኮራ አረርቲ ማርያም ቤተ ክርስቲያን መስከረም  21 ቀን 2018 ዓ.ም  ከጠዋቱ  1:45 ላይ ዓመታዊ የቅድስት ድንግል ማርያም ክብ...
01/10/2025

✝️የኃዘን ዜና ✝️

በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በምንጃር ሽንኮራ አረርቲ ማርያም ቤተ ክርስቲያን መስከረም 21 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 1:45 ላይ ዓመታዊ የቅድስት ድንግል ማርያም ክብረ በዓል ለማክበር በተገኙ ምእመናን ላይ አዲስ እየተሰራ ባለው ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የመወጣጫ መሰላል ተደርምሶ ሕይወታቸውን ያጡ እና የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ምዕመናን በርካታ ሲሆኑ በዚህም ምክንያት ሕዝበ ክርስትያኑን በእጅጉ ኃዘን ተሰምቶታል።

የማዕ/ጎንደር ሀ/ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነትም በጉዳቱ ለሞቱት ዕረፍተ ነፍስን :ለቤተሰብ :ለወዳጅ ዘመድ እና ለመላው ሕዝበ ክርስትያንም መጽናናትን :ለተጎዶት ደግሞ ፈውስና ድህነትን እንዲሰጥልን እየተመኘን በድጋሚ በጉዳቱ የተሰማንን ጥልቅ ኀዘን ለመግለጽ እንወዳለን።

በበዓለ መስቀል የሰ/ት/ቤቶች የበገና እና ያሬዳዊ ወረብ በምስል።ጎንደር 2018 ዓ.ሞ ።
27/09/2025

በበዓለ መስቀል የሰ/ት/ቤቶች የበገና እና ያሬዳዊ ወረብ በምስል።

ጎንደር 2018 ዓ.ሞ ።

የማዕከላዊ ጎንደር ሀ/ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ለአንድ ወር ያክል ሲያሰለጥናቸው የነበሩ 51 የተተኪ መምህራን ሰልጣኞችን አስመረቀ። የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት...
04/08/2025

የማዕከላዊ ጎንደር ሀ/ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ለአንድ ወር ያክል ሲያሰለጥናቸው የነበሩ 51 የተተኪ መምህራን ሰልጣኞችን አስመረቀ።

የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ከሰኔ 29 እስከ ሐምሌ 27 /2017 ዓ.ም በክረምት የሀገረ ስብከቱ ትምህርት ቤት በሆነው በሐዋርያው ጳውሎስ ትምህርት ቤት በተለያዩ የትምህርት አይነቶች እውቀቱ እና ልምዱ ባላቸው መምህራን በዝግ ሲያሰለጥናቸው የቆዩ 51 ተተኪ መምህራን ሰልጣኞችን የማ/ጎ/ሀ/ስብከት ሥራ አስኪያጅ የሆኑት ሊቀ ሥልጣናት አባ ዮሴፍ ደስታ:በርዕሰ ከተማው የሚገኙ የአድባራት አስተዳዳሪዎች እና በእለቱ የተጠሩ የክብር እንግዶች በተገኙበት በታላቅ ድምቀት አስመርቋል።

ይህም ልዩ ስልጠና የቤተ ክርስትያን ስብከተ ወንጌልን ከማስፋፋት ባሻገር የሰ/ት/ቤቶችን ሥርዓተ ትምህርት ከማስፈጸም አኳያ የመምህራን ዝግጅት ላይ በጣም አስፈላጊ እና ወሳኝ ግብዓት መሆኑን የተገለጸ ሲሆን በሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅም አባታዊ የአደራ መልዕክት እና ምክር በመስጠት በጥሩ ሁኔታ ፍጻሜውን አግኝቷል።

Address

Gondar
GONDAR

Telephone

+251942858880

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት/Central Gondar sunday school unity posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share