የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት/Central Gondar sunday school unity

  • Home
  • Ethiopia
  • Gondar
  • የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት/Central Gondar sunday school unity

የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት/Central Gondar sunday school unity ይህ የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ይፋዊ የፌስ ቡክ ገጽ ነው።

የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በሀገረ ስብከቱ ስር ባሉ አጥቢያዎች በሥርዓተ ትምህርቱ መሠረት   ትምህርታቸዉን ሲከታተሉ የነበሩ የ4ኛ ክፍል ተማሪዎችን በ...
13/09/2026

የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በሀገረ ስብከቱ ስር ባሉ አጥቢያዎች በሥርዓተ ትምህርቱ መሠረት ትምህርታቸዉን ሲከታተሉ የነበሩ የ4ኛ ክፍል ተማሪዎችን በሀገረ ስብከት አቀፍ ደረጃ በማስመረቅ ላይ።

በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ከ10 በላይ ኦርቶዶክሳውያን ሲገደሉየ101 ዓመት እድሜ ያለው የቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በእሳት ወድሟል።  የመድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ላይም ...
02/06/2026

በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ከ10 በላይ ኦርቶዶክሳውያን ሲገደሉ
የ101 ዓመት እድሜ ያለው የቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በእሳት ወድሟል።

የመድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ላይም ዘረፋ የተካሄደ ሲሆን ምእመናን ጽላቱን ይዘው ተሰደዋል፤ መኖሪያ ቤታቸውም ተቃጥሏል።

EOTCMK TV ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም

እንደ ወትሮው ሁሉ ዛሬም በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ምድር ላይ ታላቅ ሃዘን ላይ ይገኛል። ማቅ የለበሱ እናቶች፣ እንባቸው ያላለቀ ሕፃናት እና ማደሪያ ያጡ አረጋውያን ጩኸት ሰሚ አጥቷል።

ከግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት፣ አሰኮ ወረዳ፣ ጠላታ ጨፋ ቀበሌ እና ካራ ኩፍቴና በሚባሉ አካባቢዎች በኦርቶዶክሳውያን ላይ ያነጣጠረ አሰቃቂ ግድያ ተፈጽሟል።

ለደኅንነታቸው ሲባል ስማቸውን የማንጠቅሰው የአይን እማኝ እና መረጃ ሰጭያችን እንደገለጹልን ከሆነ፣ ጥቃቱ እጅግ አሳዛኝና አረመኔያዊ እንደነበር ይናገራሉ።

በአሰኮ ወረዳ ጠላታ ጨፋ ቀበሌ ብቻ በታጣቂ ኃይሎች በተፈጸመ ሰብአዊነት በጎደለው ጥቃት ከ10 በላይ ንጹሃን ኦርቶዶክሳውያን ተገድለዋል።

ይህ አሰቃቂ ጥቃት በሰዎች ሕይወት ላይ ብቻ አላበቃም የክርስቶስ ቅዱስ ሥጋና ክቡር ደም የሚፈተትበትን መቅደስም ጭምር ኢላማ ያደረገ ነበር። በአካባቢው 101 ዓመታትን ዕድሜ ያስቆጠረው፣ ታላቁ የዕድሜ ባለጸጋ የጠላታ ጨፋ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በእሳት ወውደሙን መረጃ ሰጭያችን ገልጸውናል።

በተመሳሳይ ጥቃት በካራ ኩፍቴና መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ላይ ጥቃት የተሰነዘረ ሲሆን፣ የቤተክርስቲያኑ ንብረት የሆኑ ቤቶች በመቃጠላቸው ምእመናን የመድኃኔዓለምን ቅዱስ ጽላት ይዘው በእግራቸው ወደሌላ አካባቢ መሸሻቸው ታውቋል።

ኦርቶዶክሳውያኑ ተወልደው ካደጉበት፣ ወልደው ከሳሙበት ቀያቸው በሃይማኖታቸው ብቻ ቤታቸው እየተለየ ተቃጥሏል፤ ንብረታቸውና ከብቶቻቸው ተዘርፈዋል። ከጥቃቱ የተረፉት ነዋሪዎችም ይዘውት የሸሹት እምነታቸውንና ማንነታቸውን ብቻ በመሆኑ አሁን ላይ ሜዳ ላይ ወድቀው ይገኛሉ ሲሉ ነበር በሃዘን ተውጠው የነገሩን።

በተያያዘ ዜና

በዚሁ በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት በሺርካ ወረዳ በሁለት ወጣት ኦርቶዶክሳውያን ላይ ዘግናኝ ግድያ መፈጸሙ ተሰምቷል።

ድርጊቱ የተፈጸመው ሚታና ዋጂ ቀበሌ ሲሆን፣ ታጣቂዎች ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ወደ ወጣቶቹ መኖሪያ ቤት በመግባት በቁጥጥር ስር እንዳዋሏቸውና በመቀጠልም ወጣቶቹን ወደ ሚታና ጋዶ ቀበሌ በመውሰድ፣ አንደኛውን በስለት አርደው፣ ሁለተኛውን ደግሞ በጥይት በመምታት በጭካኔ ሕይወታቸውን እንዳጠፉት ተገልጿል።

ሕይወታቸውን ያጡት የእነዚህ ወጣቶች ሥርዓተ ቀብር ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በጋዶ ማሕደረ ስብሐት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን፣ ምዕመናንና በቤተሰብ በተገኘበት በአንድ መቃብር ተፈጽሟል።

በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት በአገልጋዮችና ምእመናን ላይ በተደጋጋሚ ጥቃት እንደሚፈጸምበት ማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ለዓመታት መረጃ እያደረሰ ቢሆንም ዛሬም ድረስ ዘላቂ መፍትሔ አልተገኘም።

ምንጭ:-MK ቴሌቪዥን

29/05/2026
የማዕ/ጎ/ሀ/ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የሰ/ት/ቤቶችን  ቀን የፊታችን እሑድ ግንቦት 23 ከቀኑ 7 ሰዓት ላይ በሀገረ ስብከት አዳራሽ ይከናወናል።ስለሆነም ሁላችን እንገኝ:ላልሰሙት በማሰ...
27/05/2026

የማዕ/ጎ/ሀ/ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የሰ/ት/ቤቶችን ቀን የፊታችን እሑድ ግንቦት 23 ከቀኑ 7 ሰዓት ላይ በሀገረ ስብከት አዳራሽ ይከናወናል።
ስለሆነም ሁላችን እንገኝ:ላልሰሙት በማሰማት መንፈሳዊ ኃላፋነታችን እንወጣ።

ለነገ እሑድ ተጠርታችኋል
28/03/2026

ለነገ እሑድ ተጠርታችኋል

Address

Gondar
GONDAR

Telephone

+251942858880

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት/Central Gondar sunday school unity posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share