የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ክርስቲያኖች ኅብረት ጎንደር

  • Home
  • Ethiopia
  • Gondar
  • የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ክርስቲያኖች ኅብረት ጎንደር

የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ክርስቲያኖች ኅብረት ጎንደር ስለ ኢትዮጽያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ወቅታዊ ሁኔታ እና ስለ ኅብረቱ ስራዎች መረጃ ያገኙበታል፡፡

የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ የበኩረ ትጉኃን ዘርዓዳዊት የቀብር ሽኝት ሥነ ሥርዓት በጎንደር ከተማ ተካሄደ።የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ...
11/12/2023

የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ የበኩረ ትጉኃን ዘርዓዳዊት የቀብር ሽኝት ሥነ ሥርዓት በጎንደር ከተማ ተካሄደ።

የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ በመምህር በኩረ ትጉሃን ዘርዓዳዊት ዕረፍት የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገልጸዋል።

የቤተክርስቲያን ዐይን ነበሩ የሀገረ ስብከታችን ሥራ አስኪያጅ ያሉት ብፁዕነታቸው ሥራ ወዳድ እና ሰው አክባሪ አባት ነበሩ ብለዋል።

ብፁዕነታቸው ተጠርጣሪዎችን ሕዝቡ አጋልጦ ሊሰጥ እንደሚገባው አባታዊ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

በሸኝት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የጎንደር ከተማ አስተዳር ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ ደብሬ የኃላ እንደተናገሩት በበኩረ ትጉኃን ዘርዓ ዳዊት ህልፈተ ህይወት የተሰማቸውን ሃዘን ገልፀው አባታችን በህይወት እያሉ መልከም ሥራዎችን ሰርተዋል ብለዋል።

ወንጀለኞችን ለመያዝ የምርመራ ቡድን ተቋቁሞ እየተሰራ ሲሆን ሕብረተሰቡ ከጸጥታ መዋቅሩ ጋር በመቀናጅት ወንጀለኞችን ለፍርድ ለማቅረብ በትብብር ሊሰራ ይገባል ብለዋል ሲል የጎንደር ከተማ ኮሙኒኬሽን ዘግቧል።

የማዕከላዊ ሀገረ ስብከት ስራ አስኪያጅ ሊቀ ትጉሀን ዘርዓዳዊት ኃይሉ በትላንትናው ዕለት ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች መገደላቸው ይታወቃል። የጎንደር ከተማ ሊቃውንት አባቶች እና ምዕመናንም ከዕ...
11/12/2023

የማዕከላዊ ሀገረ ስብከት ስራ አስኪያጅ ሊቀ ትጉሀን ዘርዓዳዊት ኃይሉ በትላንትናው ዕለት ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች መገደላቸው ይታወቃል። የጎንደር ከተማ ሊቃውንት አባቶች እና ምዕመናንም ከዕለቱ ጀምሮ በማኅሌት፣ በሰዓታት እና በፀሎተ ፍትሐት ከጎናቸው ሳይለዩ አድረዋል። ዛሬ ሰኞ 01/04/2016 ዓ.ም ጠዋት ጀምሮ በጎንደር መስቀል አደባባይ የሽኝት መርሐ ግብር እየተደረገላቸው ሲሆን የቀብር ሥነ ስርዓታቸው በደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት ይፈፀማል።
የሽኝት መረሐ ግብሩ ዛሬ ከ12:00 ጀምሮ በጎንደር መስቀል አደባባይ ብፁዕ አቡነ የሐንስ(የሀ/ስብከቱ ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል) ብፁዕ አቡነ በርናባስ(የሰሜን አሜሪካ ካሊፎርኒያ ሊቀጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል) እንዲሁም መላው የጎንደር ሊቃውንት፣ መምህራን፣ የአብነት ተማሪዎች እና ምዕመናን በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል።
የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ክርስቲያኖች ኅብረትም በበትረ ትጉሀን ዘርዓዳዊት ኃይሉ ሕልፈተ ሕይወት የተሰማውን ጥሕቅ ሐዘን እየገለፀ ለመላው ኦርቶዶክሳውያን እና ለቤተሰቦቻቸው መጽናናትን ይመኛል።

ብፁዕ አቡነ አረጋዊ ዶ/ር  አረፉሐምሌ 9 ቀን 2009 ዓ.ም በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት አ...
21/03/2023

ብፁዕ አቡነ አረጋዊ ዶ/ር አረፉ

ሐምሌ 9 ቀን 2009 ዓ.ም በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት አንብሮተ ዕድ የሾሙት ጳጳሳት 14 ኤጲስ ቆጶሳት መካከል አንዱ የሆኑት በቀድሞ ስማቸው አባ ኃይለማርያም መለሰ ዶ/ር በጵጵስና ስማቸው ብፁዕ አቡነ አረጋዊ ዶ/ር የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት እና የውጪ ግንኙነት መምሪያ የበላይ ኃላፊ የድሬዳዋና የጅቡቲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል። ብፁዕነታቸው ለረጅም ጊዜ ከሀገር ውጪና በሀገር ውስጥ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ሊሻላቸው ሳይችል ቀርቶ ከዚህ ዓለም በሞተ ሥጋ ተለይተዋል።
በረከታቸው ይደርብን።
EOTC TV

እንኳን አደረሳችሁ። መጋቢት አቦ፣ፊት አቦ ጎንደር🌼🌼
13/03/2023

እንኳን አደረሳችሁ። መጋቢት አቦ፣ፊት አቦ ጎንደር🌼🌼

ነገ ቅዳሜ እና ዕሑድ ከቀኑ 9:00 ጀምሮ። ሁላችንም የምንገኝበት መንፈሳዊ ጉባኤ!!!!
03/03/2023

ነገ ቅዳሜ እና ዕሑድ ከቀኑ 9:00 ጀምሮ። ሁላችንም የምንገኝበት መንፈሳዊ ጉባኤ!!!!

የሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የተስማሙባቸው ጉዳዮች ይፋ ሆኑ።በሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን እና በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ...
21/02/2023

የሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የተስማሙባቸው ጉዳዮች ይፋ ሆኑ።

በሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን እና በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መካከል ለሁለተኛ ጊዜ የሁለትዮሽ ውይይት ከቅዳሜ የካቲት 4 ቀን እስከ የካቲት 9 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ በሩሲያ ሞስኮ መደረጉ ይታወሳል።

ይህ ጉባኤ በኢትዮጵያ በኩል በብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንትና የደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ መሪነት በሩሲያ በኩል በብፁዕ አቡነ ሊዮኒድ በአፍሪካ የሩሲያ ቤተ ክርስቲያን የበላይ ኃላፊ ሊቀ ጳጳስ እየተመራ ተከናውኗል።

በዚህ ጉባኤ ላይ ከአራት ዓመታት በፊት በተካሔደው በመጀመሪያው የሁለቱ አብያተ ክርስቲያናት ጉባኤ ወቅት በጋራ ይተገበራሉ ተብለው በተስማሙባቸው ፕሮጀክቶች ዙሪያ ግምገማ ተደርጓል።

ተ.ሚ.ማ ባገኘችው መረጃ መሠረት ከዚህ መቀጠል በተደረገው ውይይት ሁለቱ አብያተ ክርስቲያናት ክርስትናንና ክርስቲያኖችን መከላከል፣ በዘመናዊው ዓለም ክርስቲያናዊ ዕሴቶች እንዳይጠፉ መጠበቅ፣ በሚዲያ አማካኝነት የልምድ ልውውጥ ማድረግ፣ በትምህርት ዘርፍ መደጋገፍን ጨምሮ በአስራ ሁለት ርእሰ ጉዳዮች ላይ ስምምነት ፈጽመዋል።

አብያተ ክርስቲያናቱ በጋራ ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገው በጋራ ድምፃቸውን ለማሰማት የተስማሙ ሲሆን የመነኮሳት ልዑካንም ወደ ሁለቱም አብያተ ክርስቲያናት እንዲሔዱና በሁለቱም በኩል ያለውን የገዳማውያን ሕይወት እንዲመለከቱም ዕቅድ ይዘዋል።

በተጨማሪም የሞስኮ የነገረ መለኮት አካዳሚና የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርስቲ በትብብር እንዲሠሩ ስምምነት ላይ የተደረሰ ሲሆን የሩሲያ ቤተ ክርስቲያን ልዑክ ቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲንና ሌሎች የኢትዮጵያ ቦታዎችን እንደሚጎበኝም ተጠቅሷል።

ከዚህ ባለፈም የሁለቱ አብያተ ክርስቲያናት ምእመናን በሩሲያ እና በኢትዮጵያ ያሉ ቅዱሳን ቦታዎችን መጎብኘት እንዲችሉ ለማድረግ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር በትብብር ለመሥራት ተስማምተዋል።
ተሚማ

15/02/2023

ዲያብሎስ ዝናሩን ጨረሰ!!!

ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን የሲዖል ደጆች አይችሏትም።

ሰበር ዜናምርኮ ይቀጥላል+++++++++++++++++++++++++++++++++++++በሕገ ወጡ ቡድን የጵጵስና ልብስ አልብሶ ሾሜዎታለሁ ካላቸው መነኮሳት መካከል ከኢየሩሳሌም የመጡት "አባ" ን...
12/02/2023

ሰበር ዜና
ምርኮ ይቀጥላል
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++
በሕገ ወጡ ቡድን የጵጵስና ልብስ አልብሶ ሾሜዎታለሁ ካላቸው መነኮሳት መካከል ከኢየሩሳሌም የመጡት "አባ" ንዋየሥላሴ አክሊሉ ቅዱስ ሲኖዶስ የሰጠውን ዕድል በመጠቀም በመንበረ ፓትርያርክ በመገኘት አስኬማቸውንና አርዌ በትሩን ለሕጋዊዋ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በማስረከብ ቤተክርስቲያንንና ምእመናንን ይቅርታ ጠይቀዋል።
በይቅርታ ደብዳቤያቸውም ሰሞኑን በቅድስት ቤተክርስቲያናችን ከቅዱስ ሲኖዶሱ እውቅና ውጪ አዲስ ኤጲስ ቆጶሳት ሹመት ሲካኼድ ከኢየሩሳሌም መጥቼ ከተሾሙት አንዱ ነበርኩ።

በዚህ ምእመናንን ባሳዘነ ቅዱስ ሲኖዶስ ቃለ ውግዘት ባስተላለፈበት ሕገ ወጥ ሢመት ውስጥ ባለማወቅና ነገሩን ሳላጣራ የገባሁበት በመሆኑ በእጅጉ የተጸጸትኩና በዚህም ተግባር ያዘንኩ መሆኔን በይቅርታ ልብ ለመግለጥ እወዳለሁ። በመሆኑም በዛሬው ዕለት ቅዱስ ሲኖዶስ በሠየመው አቀራራቢና በይቅርታ ኮሚቴ አማካኝነት በቅዱስ ሲኖዶሱ ውሳኔ መሠረት በተከፈተው የይቅርታና የምሕረት በር ወደ እናት ቤተክርስቲያኔ እና የመንፈስ ቅዱስ አባቶቼ እንዲሁም ምእመናን ለይቅርታ የቀረብኩ ስለሆነ ቋሚ ሲኖዶሱ በምልዓተ ጉባኤው ውሳኔ መሠረት ይቅርታዬን በአባትነት መንፈስ ይቀበለኝ ዘንድ በታላቅ ትህትና እጠይቃለሁ ብለዋል ።

ምንጭ EOTC TV

11/02/2023

በጎንደር ከተማ እና አካባቢው የምንገኝ ምዕመናን ነገ ዕሁድ ጠዋት 12:00 ጀምሮ በአደባባይ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን በደመ ሰማዕታት አደባባይ ምህላ ይደረሳል። ለቅድስት ቤተ ክርስቲያናቸው ሲሉ የተሰው ሰማዕታትን እናስባለን። መልዕክቱ ለሁሉም ይድረስ።
ሁልጊዜም የአባቶቻችንን ውሳኔ እንጠብቃለን።

10/02/2023

በፅናት እንታገላለን!!!
ለድል እንበቃለን።

10/02/2023

የአሸናፊው የክርስቶስ ልጆች ነን።

Address

Gondar

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ክርስቲያኖች ኅብረት ጎንደር posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share