11/12/2023
የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ የበኩረ ትጉኃን ዘርዓዳዊት የቀብር ሽኝት ሥነ ሥርዓት በጎንደር ከተማ ተካሄደ።
የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ በመምህር በኩረ ትጉሃን ዘርዓዳዊት ዕረፍት የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገልጸዋል።
የቤተክርስቲያን ዐይን ነበሩ የሀገረ ስብከታችን ሥራ አስኪያጅ ያሉት ብፁዕነታቸው ሥራ ወዳድ እና ሰው አክባሪ አባት ነበሩ ብለዋል።
ብፁዕነታቸው ተጠርጣሪዎችን ሕዝቡ አጋልጦ ሊሰጥ እንደሚገባው አባታዊ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
በሸኝት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የጎንደር ከተማ አስተዳር ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ ደብሬ የኃላ እንደተናገሩት በበኩረ ትጉኃን ዘርዓ ዳዊት ህልፈተ ህይወት የተሰማቸውን ሃዘን ገልፀው አባታችን በህይወት እያሉ መልከም ሥራዎችን ሰርተዋል ብለዋል።
ወንጀለኞችን ለመያዝ የምርመራ ቡድን ተቋቁሞ እየተሰራ ሲሆን ሕብረተሰቡ ከጸጥታ መዋቅሩ ጋር በመቀናጅት ወንጀለኞችን ለፍርድ ለማቅረብ በትብብር ሊሰራ ይገባል ብለዋል ሲል የጎንደር ከተማ ኮሙኒኬሽን ዘግቧል።