03/04/2026
***እንኳን ለ 2018ዓ.ም የወጣቶች በዓል ሳምንት አደረሳችሁ!***
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ተልዕኮዋ ሁለንተናዊ ወንጌልን ለሁለተናዊ ሰው በኢትዮጵያ እና ከኢትዮጵያ ውጭ ሁሉ ማወጅ ነው። ቤተክርስቲያኒቱ ተመስርታ አገልግሎት መስጠት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በሁለንተናዊ አገልግሎቶቿ ለሚልዮኖች በረከት ሆናለች፡ እየሆነችም ትገኛለች፡፡ የወንጌል ሚስዮን አገልግሎት ከአገልግሎቶቿ አንዱ ሳይሆን ዋና ማንነቷ ነው፡፡ ይሄን የቤተክርስቲያናችንን ሁለንተናዊ አገልግሎት ተልዕኮ እና ራዕይ ተረካቢ መሪ የሆኑት ወጣቶች በሚገባ ተረድተው ፤ በህይወታቸው እና አገልግሎታቸው ተለውጠው ፍሬያማ እንዲሆኑ እና መልካም ተጽዕኖ መፍጠር እንዲችሉ በሁለንተናዊ መልኩ ቀርጾ ማሳደግ ትኩረት የሚፈልግ ብርቱ ሥራ ነው፡፡ ይሄንንም የቤተክርስቲያኒቱን ራዕይ እና ተልዕኮ በተቀናጀ መልኩ ከግብ ለማድረስ እና ወጣቶችን በሁለንተናዊ መልኩ በመቅረጽ ላይ ትኩረት ያደረገ የሁለንተናዊ አገልግሎት ፓኬጅ ተቀርጾ እየተሰራበት መሆኑ ይታወቃል፡፡ ዓላማውም ወጣቶቻችን በሁለንተናዊ አገልግሎት ታንጸው፤ በህይወታቸው እና አገልግሎታቸው የምድር ጨው እና የዓለም ብርሃን ሆነው እንዲገለጡ ነው፡፡
ይህንንም ታሳቢ በማድርግ በቤተክርስቲያናችን ካሌንደር መሰረት በመጋቢት 27, 2018 ዓ.ም ( April 5, 2026) ተከብሮ የሚውለው የወጣቶች በዓል፤ ከሰኞ መጋቢት 21 ጀምሮ ሳምንቱን በሙሉ ከእግዚአብሔር ቃል ማቴ. 5፡16 ላይ ፤ “መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ’’ የሚለውን የጌታ ኢየሱስን ቃል መነሻ በማድረግ ‘ተጽዕኖ ፈጣሪ ሕይወት ለሁለንተናዊ አገልግሎት‘ በሚል ርዕስ ይከበራል።
የበዓሉ አከባበር ዝርዝርም እንደሚከተለው ይሆናል፡-
• ሰኞ፤ መጋቢት 21፡ 2018ዓ.ም ፡ በጾም እና በጸሎት፡- ለሁለንተናዊ የወንጌል አገልግሎት (ለሀገር-አቀፍ እና አለም-አቀፍ የሚስዮን አገልግሎት፤ ለማህበራዊ እና ልማታዊ አገልግሎቶች፤ ስለ ሀገር እና አለም-አቀፍ ወቅታዊ ጉዳዮች… እና ወዘተ)
• ማክሰኞ፤ መጋቢት 22፡ 2018ዓ.ም ፡ በአካባቢ እና ከተማ ጽዳት ስራ (በማ/ምዕመናን ግቢ፤ በምንኖርበት አካባቢ፤ በመንደሮች እና በከተሞች ዙርያ…)
• ረቡዕ ፤ መጋቢት 23፡ 2018ዓ.ም ፡ በስፖርታዊ ጨዋታዎች እና ውድድሮች (የአካል እንቅስቃሴ፤ እግር ኳስ፤ የመረብ ኳስ፤ ሩጫ፤ የገመድ ጉተታ፤ … እና ወዘተ )
• ሐሙስ ፤ መጋቢት 24፡ 2018ዓ.ም ፡ በተለያዩ የስነ-ጽሁፍ አገልግሎቶች (ዝማሬ፤ ግጥም፤ ድራማ፤ ጭውውት፤ ጥያቄ እና መልስ፤ የስዕል ውድድሮች… እና ወዘተ)
• አርብ ፤ መጋቢት 25፡ 2018ዓ.ም ፡ በወንጌል ሰርጭት ዘመቻ (በአካባቢ ፤በመንደሮች እና በከተሞች ዙርያ የወንጌል ስርጭት ማድረግ)
• ቅዳሜ፤ መጋቢት 26 ፡ 2018ዓ.ም ፡ ሁሉን አቀፍ ኮንፈረንስ እና የገቢ ማሰባሰብያ (የወጣቶችን አገልግሎት ለመደገፍ)
• እሁድ ፤ መጋቢት 27፡ 2018ዓ.ም ፡ ሁሉን አቀፍ ኮንፈረንስ እና የበዓሉ ማጠቃለያ
ከላይ በተጠቀሰው አቅጣጫ መሰረት በሳምንቱ ቀናት በሙሉ እንደየ አካባቢው አውድ በተሰጠው ርዕስ ዙርያ በሁሉምፐማ/ምዕመናናት ፕሮግራሞቹ ይካሄዳሉ ፤ ወጣቶቻችን በህይወታቸው እና አገልግሎታቸው መልካም ተጽዕኖ የሚፈጥር ህይወት እንዲኖራቸው የሚረዳ ትምህርት ይሰጣል ፡፡
በነዚህ በወጣቶች ቀናትም በማ/ምዕማናን፡ በሰበካ/በፕሬስፕቴሪ፡ በሲኖዶስ እና በዋናው ጽ/ቤት ያለውን የወጣቶች አገልግሎት ለማጠናከር የገቢ ማሰባሰብያ ይደረጋል።
ስለዚህ፡ የቤተ ክር