ቤናራ መ/ኢ/ቤተክርስቲያን ወጣቶች ህብረት Benara M/K/Y Church Youth Team

  • Home
  • Ethiopia
  • Durame
  • ቤናራ መ/ኢ/ቤተክርስቲያን ወጣቶች ህብረት Benara M/K/Y Church Youth Team

ቤናራ መ/ኢ/ቤተክርስቲያን ወጣቶች ህብረት Benara M/K/Y Church Youth Team መንፈሳዊና ጠቀሚ መረጃዎችን ማገረት

ለታረደው በግ
08/04/2026

ለታረደው በግ

06/04/2026

እሁድ መጋቢት 27/2018 ዓ.ም የከሰዓት አምልኮ ፕሮግራም የእግዚአብሔር ቃል ከመንፈስ ቅዱስ በአገልጋይ (ወንጌላዊ) ሳሙኤል ተስፋዬ


(1ሳሙ 1፥8-18)
ይህ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክ የተጻፈው በሰማይ እግዚአብሔር ቤቱ በክፋት ተሞልቶ ሕዝቡ ከእርሱ እርቆ "ለቤቴ ክብሩን የሚመልስ አገልጋይ የሚሆን አንድ ሰው (ልጅ) አገኝ ይሆንን?" ብሎ እየፈለገ የነበረበት፤
ከምድር ሐና እግዚአብሔርን "ነቀፌታዬን ታስወግድ ዘንድ አቤቱ ልጅን ሰጠኝ" እያለች እየጮኸች የነበረበት ጊዜ ነበር።

ፍለጋዋ ከእግዚአብሔር ሀሳብ ጋር ተገጣጠመ እርሷም ለእግዚአብሔር አገልጋይ ይሆን ዘንድ ጡት እንደጣለ ወስዳ ለእግዚአብሔር ልጁን እንደምትሰጥ ተናገረች።

ፊናና ልጆች አሉዋት ምትበላው እና የምትጠጣው አላት ግን ቃልኪዳን የላትም፤ ሐና ግን ቃልኪዳን አላት ልጅ የላትም።
ሐናን ፊናና ስታበሳጫት ምናልባት ትምክህት በሞለበትና የሐናናን ጎዶሎ በሚያሳይ መንገድ ታበሳጫት ነበር።

ነገርግን በዚህ የሐና ጩኸት ይበረታል እንጂ አልተቋረጠም። ሐና ከእግዚአብሔር ጋር በጩኸትና በልመና አሳልፋ በሠላም ቤት ስትመለስ ጠብቃ ታሰናክላታለች።

"በየዓመቱም እንዲህ ባደረገ ጊዜ እርስዋም ወደ እግዚአብሔር በምትወጣበት ጊዜ ታበሳጫት ነበር፤ ሐናም ታለቅስ ነበር፥ አንዳችም አትቀምስም ነበር።" 1ኛ ሳሙ 1፥7
"ዔሊም፦ ስካርሽ እስከ መቼ ነው? የወይን ጠጅሽን ከአንቺ አርቂው አላት።" 1ኛ ሳሙ 1፥14

እግዚአብሔር ፊት የምናደርገውን ጩኸት ፤አንዳንዶች እንደሚያደርጉት፤
🧾በጣም በተመቻቻ ጊዜ ፤በጣም በልተመቸ ሁኔታ መጥፎ ጊዜን ለማምለጥ ችግር በተጋረጠ ጊዜ ለዚያ ቅጽበት የሚደረግ አይደለም።

🧾እግዚአብሔር የሚሰማው ጩኸት ወይም ጸሎት፦
ያለመታከት በጽኑልብ እራስን በማዋረድ የሚደረግ ነው። ልክ እንደ ሐና ጩኃት ብትበሳጭም ባትበሳጭ በታገኝም ወደ እግዚአብሔር ሳይታክቱ የሚጮኹትን ሰዎች ጨኀት ይሰማል።

ሐና በዚህ ተሪኳ ስጻፍ በረጀ እድሜዋ ልጅ አግኝታ የምታመሰግን ሴት ሆኔ ሳትሆን እግዚአብሔር የተመለከታት ነቀፌታዋ ተወግዶ ሴቶች በሕዝብ ፊት ልናገሩ በማይችሉበት ዘመን እግዚአብሔር ከእርሷ ጋር ተናግሮላት ለበቀል የሆነ ከዳን እስከ ቤርሳቤህ የእግዚአብሔርን አደራ ተሸክሞ የሚኖር ነብይ ያገኘች ናት።
ይህንን ስታገኝ የስህለት ልጇን ሳሙኤልን በሕዝብ ፊት እንደምናምንቴ የቆጠራትን የወይን ጠጅሽንም ከአንቺ አርቂው ያላትን ከህን ፊት ለእግዚአብሔር ከሚቀርብ መስዋዕት ጋር ይዛ መጣች።
በዓለም ዛሬ ላይ ብዙ ፊናናዎች ይኖራሉ በእግዚአብሔር ፊት የመሆን ጉዳይ ግን መወሰን መቻል የለባትም።
1ኛ ሳሙ 1
ጡትም በተወ ጊዜ ከእርስዋ ጋር እርሱንና አንድ የሦስት ዓመት ወይፈን፥ አንድ የኢፍ መስፈሪያ ዱቄት፥ አንድ አቁማዳ የወይን ጠጅ ይዛ ወደ ሴሎ ወደ እግዚአብሔር ቤት አመጣችው፤ ሕፃኑም ገና ታናሽ ነበረ።
ወይፈኑንም አረዱ፥ ሕፃኑንም ወደ ዔሊ አመጡት።

ቀንንዴን ከፍ ከፍ አደረገው ስትል የምትናገረው ሐና አንድ ልጅ ብቻ ሳይሆን ልጆችን አግኝታ የአስጨናቂዎቿን ኩራት ጌታ አስወግዶ በማህበር ፊት ስለእግዚአብሔር የምትናገር ሆነች።
እኛም እንደ ሐና ወደ እግዚአብሔር ስንጮህ



እንደቃሉ እንድንኖር በፀጋው ይርዳን፤የእግዚአብሔር ፍለጋና ጸሎታችን የሚገጥምበት ዘመን ይሁንልን...በኢየሱስ ስም አሜን።

03/04/2026

***እንኳን ለ 2018ዓ.ም የወጣቶች በዓል ሳምንት አደረሳችሁ!***

የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ተልዕኮዋ ሁለንተናዊ ወንጌልን ለሁለተናዊ ሰው በኢትዮጵያ እና ከኢትዮጵያ ውጭ ሁሉ ማወጅ ነው። ቤተክርስቲያኒቱ ተመስርታ አገልግሎት መስጠት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በሁለንተናዊ አገልግሎቶቿ ለሚልዮኖች በረከት ሆናለች፡ እየሆነችም ትገኛለች፡፡ የወንጌል ሚስዮን አገልግሎት ከአገልግሎቶቿ አንዱ ሳይሆን ዋና ማንነቷ ነው፡፡ ይሄን የቤተክርስቲያናችንን ሁለንተናዊ አገልግሎት ተልዕኮ እና ራዕይ ተረካቢ መሪ የሆኑት ወጣቶች በሚገባ ተረድተው ፤ በህይወታቸው እና አገልግሎታቸው ተለውጠው ፍሬያማ እንዲሆኑ እና መልካም ተጽዕኖ መፍጠር እንዲችሉ በሁለንተናዊ መልኩ ቀርጾ ማሳደግ ትኩረት የሚፈልግ ብርቱ ሥራ ነው፡፡ ይሄንንም የቤተክርስቲያኒቱን ራዕይ እና ተልዕኮ በተቀናጀ መልኩ ከግብ ለማድረስ እና ወጣቶችን በሁለንተናዊ መልኩ በመቅረጽ ላይ ትኩረት ያደረገ የሁለንተናዊ አገልግሎት ፓኬጅ ተቀርጾ እየተሰራበት መሆኑ ይታወቃል፡፡ ዓላማውም ወጣቶቻችን በሁለንተናዊ አገልግሎት ታንጸው፤ በህይወታቸው እና አገልግሎታቸው የምድር ጨው እና የዓለም ብርሃን ሆነው እንዲገለጡ ነው፡፡

ይህንንም ታሳቢ በማድርግ በቤተክርስቲያናችን ካሌንደር መሰረት በመጋቢት 27, 2018 ዓ.ም ( April 5, 2026) ተከብሮ የሚውለው የወጣቶች በዓል፤ ከሰኞ መጋቢት 21 ጀምሮ ሳምንቱን በሙሉ ከእግዚአብሔር ቃል ማቴ. 5፡16 ላይ ፤ “መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ’’ የሚለውን የጌታ ኢየሱስን ቃል መነሻ በማድረግ ‘ተጽዕኖ ፈጣሪ ሕይወት ለሁለንተናዊ አገልግሎት‘ በሚል ርዕስ ይከበራል።

የበዓሉ አከባበር ዝርዝርም እንደሚከተለው ይሆናል፡-
• ሰኞ፤ መጋቢት 21፡ 2018ዓ.ም ፡ በጾም እና በጸሎት፡- ለሁለንተናዊ የወንጌል አገልግሎት (ለሀገር-አቀፍ እና አለም-አቀፍ የሚስዮን አገልግሎት፤ ለማህበራዊ እና ልማታዊ አገልግሎቶች፤ ስለ ሀገር እና አለም-አቀፍ ወቅታዊ ጉዳዮች… እና ወዘተ)

• ማክሰኞ፤ መጋቢት 22፡ 2018ዓ.ም ፡ በአካባቢ እና ከተማ ጽዳት ስራ (በማ/ምዕመናን ግቢ፤ በምንኖርበት አካባቢ፤ በመንደሮች እና በከተሞች ዙርያ…)

• ረቡዕ ፤ መጋቢት 23፡ 2018ዓ.ም ፡ በስፖርታዊ ጨዋታዎች እና ውድድሮች (የአካል እንቅስቃሴ፤ እግር ኳስ፤ የመረብ ኳስ፤ ሩጫ፤ የገመድ ጉተታ፤ … እና ወዘተ )

• ሐሙስ ፤ መጋቢት 24፡ 2018ዓ.ም ፡ በተለያዩ የስነ-ጽሁፍ አገልግሎቶች (ዝማሬ፤ ግጥም፤ ድራማ፤ ጭውውት፤ ጥያቄ እና መልስ፤ የስዕል ውድድሮች… እና ወዘተ)

• አርብ ፤ መጋቢት 25፡ 2018ዓ.ም ፡ በወንጌል ሰርጭት ዘመቻ (በአካባቢ ፤በመንደሮች እና በከተሞች ዙርያ የወንጌል ስርጭት ማድረግ)

• ቅዳሜ፤ መጋቢት 26 ፡ 2018ዓ.ም ፡ ሁሉን አቀፍ ኮንፈረንስ እና የገቢ ማሰባሰብያ (የወጣቶችን አገልግሎት ለመደገፍ)

• እሁድ ፤ መጋቢት 27፡ 2018ዓ.ም ፡ ሁሉን አቀፍ ኮንፈረንስ እና የበዓሉ ማጠቃለያ

ከላይ በተጠቀሰው አቅጣጫ መሰረት በሳምንቱ ቀናት በሙሉ እንደየ አካባቢው አውድ በተሰጠው ርዕስ ዙርያ በሁሉምፐማ/ምዕመናናት ፕሮግራሞቹ ይካሄዳሉ ፤ ወጣቶቻችን በህይወታቸው እና አገልግሎታቸው መልካም ተጽዕኖ የሚፈጥር ህይወት እንዲኖራቸው የሚረዳ ትምህርት ይሰጣል ፡፡

በነዚህ በወጣቶች ቀናትም በማ/ምዕማናን፡ በሰበካ/በፕሬስፕቴሪ፡ በሲኖዶስ እና በዋናው ጽ/ቤት ያለውን የወጣቶች አገልግሎት ለማጠናከር የገቢ ማሰባሰብያ ይደረጋል።

ስለዚህ፡ የቤተ ክር

ኑ አብረን ጌታን እናመልከለን
02/04/2026

ኑ አብረን ጌታን እናመልከለን

27/08/2025

Check out Yeega3651’s post.

የተወደዳችሁ በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ በተለያየ ክፍለ ዓለም ያላችሁ ቅዱሳን፣ ሌት ተቀን ለዚህ (ቤናራ መ/ኢ/ማ/ም) ህንፃ ሥራ እየተባበራችሁ የምትገኙ ጌታ እግዚአብሔር አብዝቶ ይባርካችሁ...
19/08/2025

የተወደዳችሁ በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ በተለያየ ክፍለ ዓለም ያላችሁ ቅዱሳን፣ ሌት ተቀን ለዚህ (ቤናራ መ/ኢ/ማ/ም) ህንፃ ሥራ እየተባበራችሁ የምትገኙ ጌታ እግዚአብሔር አብዝቶ ይባርካችሁ። ከታች በፎቶ እንደሚትመለከቱት፦
እናቾች፡ ቡና አፍልተው አሸም በማለት
ወጣቶችና አባቾች፡ ጊዜያቸውንና ጉልበታቸውን ሰጥተው ከጧት እስከ ማታ ድረስ በደስታ በመሥራት ላይ ይገኛሉ።
የሥራው ባለቤት እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን፤ እያልን፦ በሚያስፈልገው ሁሉ ድጋፋችሁ አይቋረጥ። ጌታ እግዚአብሔር ስለቤቱ፣ ስለስሙ የምታደርጉትን በጎነት አይረሳም።🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏

የቤናራ መካነ ኢየሱስ አዲሱ የህንፃ ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሎአል። ጌታ ይመስገን👏!  " እነርሱም፦ እንነሣና እንሥራ አሉ። እጃቸውንም ለበጎ ሥራ አበረቱ።" ነህ 2:18 አሁንም ለዚህ ሥራ የየበኩ...
16/08/2025

የቤናራ መካነ ኢየሱስ አዲሱ የህንፃ ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሎአል። ጌታ ይመስገን👏!
" እነርሱም፦ እንነሣና እንሥራ አሉ። እጃቸውንም ለበጎ ሥራ አበረቱ።" ነህ 2:18
አሁንም ለዚህ ሥራ የየበኩላችሁን ተሳትፎ እያደረጋችሁ ያላችሁትን በሀገር ውስጥና ውጭ የምትኖሩ ቅዱሳንን እያመሰገንን፤ እገዛችሁ በሁሉ አይለየን ፣በአንድነት ሠርተን እንጨርሳለን። እግዚአብሔር ይባርካችሁ🙏🙏🙏🙏

ዛሬም ሥራው ቀጥሎ ውሏል የቀረው ፖድ ተቆፊሯል እንድሁም ነገም የምቀጥል ይሆናል ።ቅዳሜ የጌታ መልካም ፈቃድ ከሆነ የፖድ መሙላት ሥራ ይቀጥላል  # # ዛሬ ከአካባቢ ቤ/ክርስቲያንም የመጣችሁ...
14/08/2025

ዛሬም ሥራው ቀጥሎ ውሏል የቀረው ፖድ ተቆፊሯል እንድሁም ነገም የምቀጥል ይሆናል ።
ቅዳሜ የጌታ መልካም ፈቃድ ከሆነ የፖድ መሙላት ሥራ ይቀጥላል
# # ዛሬ ከአካባቢ ቤ/ክርስቲያንም የመጣችሁ ወጣቶችንም እጂግ አድርገን እናመሰግናለን ፈጣሪ ዘመናችሁን ይባርክ።
👉በጉልበት
👉በፀሎት
👉በገንዘብ
👉በሀሳብ
🙏አብራችሁ ስለምታግዙንና እያገዘችሁን ስለሆነ ጌታ ኢየሱስ በረከቱን ያብዘላችሁ
✝️share
👉like በማድረግ ለብዙዎች እናድርስ

➡️ለወጣቶች የተዘጋጀ የትምህርት ጊዜ 🗓ሚያዝያ 05 እሁድ ከሰዓት 🕘9:00 ስዓት ጀምሮ ✝️ቤናራ መ/ኢ/ቤተክርስቲያን📙🖊📝
10/04/2025

➡️ለወጣቶች የተዘጋጀ የትምህርት ጊዜ
🗓ሚያዝያ 05 እሁድ ከሰዓት
🕘9:00 ስዓት ጀምሮ
✝️ቤናራ መ/ኢ/ቤተክርስቲያን
📙🖊📝

አጥብቀን እንቃወማለን
15/03/2025

አጥብቀን እንቃወማለን

Address

Durame

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ቤናራ መ/ኢ/ቤተክርስቲያን ወጣቶች ህብረት Benara M/K/Y Church Youth Team posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share