ሠላም መስጂድ مسجد اسلام

ሠላም መስጂድ مسجد اسلام ይህ ገፅ፤ በኦሮሚያ ክልል፣ በሸገር ከተማ፣ በገላን ክ/ከተማ፣ ኤቾ ቀበሌ ውስጥ የሚገኘው ሠላም መስጂድና መድረሳን በተመለከተ መረጃ የሚሰራጭበት ገፅ ነው።

የጋዛ ወንድሞቻችን ሰቆቃ ከዕለት ዕለት እየከፋ መጥቷልና በዱዓ እንበርታ።
10/12/2023

የጋዛ ወንድሞቻችን ሰቆቃ ከዕለት ዕለት እየከፋ መጥቷልና በዱዓ እንበርታ።

ረጀብ ጠይብ ኡርዱጋን የዘንድሮውን የቱርክ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ በአስተማማኝ ብልጫ ማሸነፋቸው ተረጋግጧል። በዚህም መሠረት ላለፉት 20 ዓመታት ሃገሪቱን የመሩትና በቱርካዊያን መንፈሳዊና ዓለማዊ...
28/05/2023

ረጀብ ጠይብ ኡርዱጋን የዘንድሮውን የቱርክ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ በአስተማማኝ ብልጫ ማሸነፋቸው ተረጋግጧል። በዚህም መሠረት ላለፉት 20 ዓመታት ሃገሪቱን የመሩትና በቱርካዊያን መንፈሳዊና ዓለማዊ ሕይወት ላይ የሚገርም ዕድገት በማምጣት በሃገሪቱ ታሪክ ላይ ትልቅ አሻራ ያኖሩት ኡርዱጋን፣ ለቀጣዩ አምስት ዓመታት ቱርክን በፕሬዚዳንትነት የሚመሩ ይሆናል። አልሃምዱሊላሂ።

27/05/2023

"የቱለማን መሬት ሸጦ ሴተኛ አዳሪ በሚሊዮን የገዛ ቡድን ዛሬ በህግ ማስከበር ስም የደሃ ቤት እና ቤተ እምነት ማፍረስ ተገቢ አይደለም!!" አቶ ታየ ደንደዓ


አቶ ታዬ ደንደዓ በአዲስ አበባ ዙሪያ ሸገር ከተማ የሚፈርሱ ቤቶች እና ቤተ እምነቶችን ተከትሎ የፃፉትን ፋስት መረጃ እንደሚከተለው ወደ አማርኛ ተርጉሞታል እንድታነቡት እንጋብዛለን!!
ቱለማዎች መፈናቀላቸው እውነት ነው። ቱለማን አፈናቅሎ ለማኝ እና ስደተኛ ያደረጋቸው ማነው? ሌላ ሃይል ቢኖርም አብዛኛውን ቱለማን ከቤታቸው ያፈናቀለው ሌቦቹ ናቸው። ባለፉት አምስት ዓመታት በአዲስ አበባ ዙሪያ ባሉ ከተሞች የሆነውን ሀገር ያውቃል። በገበሬ ስም የአዲስ አበባን መሬት የዘረፈው ማነው? የአዲስ አበባን መሬት ቸብችቦ ሴተኛ አዳሪ በጨረታ የገዛው በሚሊየን ቲፕ የሰጠው ማነው? የሌባው ቡድን ነው።

ቀን ቀን የቱለማን ደሃ የሚያስለቅሰው፣ ማታ ውስኪ ቤት የሚጨፈረው፣ ይቅር የማይባል ወንጀል እየፈፀሙ ዛሬ ደግሞ የቱለማ ጠበቃ መሆን። በቱለማነት ተከልለው የራስን ወንጀል መደበቅ አይቻልም። ለቱለማ ብለን መስጂድ አፈረስን ማለት ምን ማለት ነው! የመስጂድ ማፍረስን ከቱለማ ጋር ማገናኘት ለግጭት መቀስቀሻ ነው።

ህግን ማክበር ትክክል ነው። የቤተ እምነት ግንባታ ጨምሮ ሁሉም ነገር በሕግና በሥርዓት መከናወን አለበት። ህገ ወጥ ግንባታን መከልከል ጉልበትና ሃብት ሳይባክን ነው መሆን ያለበት። የራስን መሬት ሸጦ፣ ቤት ሲሰራ ዝም ብሎ መብራትና ውሃ አስገብቶ፣ ከፍተኛ የሀገር ሀብት ከፈሰሰበት በኋላ በህግ ማስከበር ስም የደሃ ቤት እና ቤተ እምነት ማፍረስ ተገቢ አይደለም።

ሰላም እንፈልጋለን!
ለተጨማሪ መረጃዎች የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/fastmereja

22/04/2023

በመላው ሃገሪቱ ለምትገኙ ወንድምና እህቶቻችን እንኳን ለታላቁ በዓል አደረሳችሁ፤ ኢድ ሙባረክ!!!

22/04/2023

በኦሮሚያ ክልል፣ ገላን ክ/ከተማ በተለምዶ ኤቾ (አቢቹ) ተብሎ የሚጠራው አካባቢ ቤታቸው ፈርሶባቸው በሠላም መስጂድ ተጠልለው የሚገኙ አቅመ ደካሞችን የተመለከተ ጥንቅር

22/04/2023
20/04/2023

ከሰሞኑ ቤታችሁ በዕብሪተኞች ፈርሶባችሁ በመከራና ዕንግልት ውስጥ ላላችሁ ወንድም እህቶቻችን ምን ያህል አስከፊ ሁኔታ ውስጥ እንዳላችሁ ቤታቸው ፈርሶ መውደቂያ አጥተው በሠላም መስጂድ ውስጥ የተጠለሉትን ወንድም እህቶቻችንን በመመልከት መገንዘብ ችያለሁ። ታዲያ ምንም እንኳን የደረሰባችሁ መከራና ችግር መራር ቢሆንም፣ ልትገነዘቧቸው የሚገቡ ወሳኝ ነጥቦች አሉ፤ ከነዚህም መካከል፦
• በቅድሚያ አላህ (ሱ.ወ) ይህ ችግር እንዲደርስብህ የፈቀደው ከዚህ በታች ከተጠቀሱት በአንዱ ወይም ከአንድ በላይ በሆኑ ምክንያቶች መሆኑን ፈፅሞ እንዳትዘነጋ፦
o ስለሚወድህ፦ በዚህች ዓለም ሕይወት አላህ (ሱ.ወ) ሁላችንንም ይፈትነናል። የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) የአንድ ሰው ዕምነቱ በጠነከረ ቁጥር በሕይወቱ የሚገጥሙት ፈተናዎችም ይጠነክራሉ፣ እንዲሁም ይበዛሉ በማለት አላህ (ሱ.ወ) የሚወደውንና ኢማነ ጠንካራውን በበለጠ እንደሚፈትነው ነግረውናል። ስለዚህ የገጠመህ ከባድ ችግር ከአላህ (ሱ.ወ) ውዴታ በመነጨ ሊሆን ይችላል፤
o በፈረሰብህ ፈንታ ሌላ የተሻለ ነገር ሊለውጥልህ ፈልጎ፤
o በደረሰብህ ችግር ምክንያት ወንጀልህን ሊምርህ ፈልጎ፤
o በደረሰብህ ችግር ምክንያት በርሱ ዘንድ ደረጃህን ከፍ ሊያደርገው ፈልጎ፤
o በቀደመ ወንጀልህ ምክንያት፦ ጌታችን እንዲህ ይላል፦ «ከመከራም ማንኛውም ያገኛችሁ ነገር እጆቻችሁ በሠሩት (ኃጢኣት) ምክንያት ነው። ከብዙውም ይቅር ይላል።» (ሱረቱ ሹራ፡30)፤
o ለፈተና፦ ፈተና አላህ (ሱ.ወ) ሙእሚኑን ከሙናፊቁ የሚለይበት ፈለጉ ነው። ይህንን አስመልክቶ ጌታችን እንዲህ ይላል፦ «ከፍርሃትና ከረኃብም በጥቂት ነገር፣ ከገንዘቦችና ከነፍሶችም፣ ከፍራፍሬዎችም በመቀነስ በእርግጥ እንሞክራችኋለን። ታጋሾችንም (በገነት) አብስር። እነዚያን መከራ፤ በነካቻቸው ጊዜ ‹እኛ ለአላህ፤ ነን እኛም ወደርሱ ተመላሾች› ነን የሚሉትን (አብስር)። እነዚያ በእነርሱ ላይ ከጌታቸው የኾኑ ምሕረቶች ችሮታም አልሉ። እነርሱም (ወደ እውነት) ተመሪዎቹ እነርሱ ናቸው።» (ሱረቱል በቀራህ፡ 155-157)።
• በመቀጠል ምንም ብታደርግ ቤትህን ከመፍረስ ልታድነው አትችልም ነበር፤ ምክንያቱም የቤትህ መፍረስ ተከትሎም የደረሰብህ መከራ አስቀድሞ በጌታችን የተወሰነ ነውና፤ ጌታችን እንዲህ ይላል፦ «በምድርም በነፍሶቻችሁም መከራ (ማንንም) አትነካም ሳንፈጥራት በፊት በመጽሐፍ የተመዘገበች ብትኾን እንጅ። ይህ በአላህ ላይ ገር ነው። (ይህ ማሳወቃችን) ባመለጣችሁ ጸጋ ላይ እንዳታዝኑ አላህም በሰጣችሁ ነገር (በትዕቢት) እንዳትደሰቱ ነው። አላህም ኩራተኛን ጉረኛን ሁሉ አይወድም።» (ሱረቱል ሐዲድ፡ 22-23)።
• ሲሰልስ ይህንን መጥፎ ክስተት ወደተሻለ መልካም አጋጣሚ መቀየር የምትችልበት ትልቅ ዕድል በጅህ ላይ አለ፤ ይኸውም፦
o በመታገስ፣
o የአላህን (ሱ.ወ) ውሣኔ በመውደድ፣
o የገጠመህን ችግር ለሰዎች ባለማሶሞት፤
• ባጠቃላይ ምንም ብታደርግ ልትቀይረው የማትችለውን መጥፎ ክስተት ወደመልካም ዕድል መቀየር መቻል ከፍ ያለ ብልህነት ነውና አጋጣሚውን ተጠቀምበት። አላህ (ሱ.ወ) የተሻለውን ይስጣችሁ፣ አሚን!

ቤታቸው ፈርሶባቸው በመስጂደ ሠላም ንብረታቸውን አጭቀው በመስጂዱ የተጠለሉ ወንድምና እህቶቻችንን አላህ ይዘንላቸው!!!
19/04/2023

ቤታቸው ፈርሶባቸው በመስጂደ ሠላም ንብረታቸውን አጭቀው በመስጂዱ የተጠለሉ ወንድምና እህቶቻችንን አላህ ይዘንላቸው!!!

17/04/2023

በመስጂዳችን (ሠላም መስጂድ) ዙሪያ ነዋሪ የነበሩ ሁሉ ባለፈው ሳምንት ቤታቸው በአፍራሽ ግብረሃይል በመፍረሱ ቀድሞ ሞቅ ብሎ የነበረው መስጂዳችን ጨርሶ ባዶ ሆኗል፤ ያሳዝናል።

12/04/2023

ቤታችሁ በዕብሪተኞች ፈርሶባችሁ ለጎዳና ተዳዳሪነት ለተዳረጋችሁ ወንድም እህቶቻችን፤ ከዚህ በመቀጠል ያሉትን ልብ በሉልኝ፦
• «ከችግርም ጋር ምቾት አልለ፡፡ ከችግር ጋር በእርግጥ ምቾት አልለ፡፡» (ሱረቱል ኢንሺራሕ፡ 5-6)።
• «ሊሶጃን ቀዳ ጪልማሽ ይቢሳን» ስልጢ።
• «ሊነጋ ሲል ይጨልማል» ኢትዮጵያ።
• «No matter how the night is long, the day is sure to come» ምዕራባውያን።

07/04/2023

ያ ኢኽዋኒ ወል አኽዋት
መስጂዳችን (ሠላም መስጂድ) የመፍረስ አደጋ ተጋርጦባታል። በመሆኑም በቀይ የኤክስ ምልክት ተደርጎበታል። በተጨማሪም 99% ሙስሊም የሆነው የአካባቢው ማኅበረሰብም በሁለት ቀናት ውስጥ ቤታችሁን አፍርሳችሁ፣ ኮተታችሁን ይዛችሁ መድረሻችሁን ፈልጉ ተብለው በጭንቅ ውስጥ ወድቀዋል። በዚህም ምክንያት በደላቸውን ለጌታቸው ከማሰሞት ውጪ አማራጭ ያጡት ተበዳዮቹ ቤታቸው እንዳይፈርስባቸው ጠዋት ማታ እንባቸውን ወደአላህ (ሱ.ወ) እየረጩ ይገኛሉ። እናንተም ለአላህ (ሱ.ወ) ብላችሁ ዱዓ አድርጉላቸው።

አላህ (ሱ.ወ) የበዳዮችን እጅ ይያዝልን፤ አሚን!!!

Address

Dukem

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሠላም መስጂድ مسجد اسلام posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category