Bright Light Gospel Ministry page

Bright Light Gospel Ministry page Bright Light

27/10/2024

=================
ጽንስ ከትክክለኛው ጊዜ በፊት ቢወለድ ጤናማ ሆኖ የማደጉ ጉዳይ ፈተና ላይ ስለሚወድቅ መቸኮል አያስፈልግም። ከመወለጃ ጊዜው ቀድሞ የሚወለድ ጽንስ ከፍተኛ የሕክምና ክትትል ካልተደረገለት በቀር በአካሉ፣ በስነልቦናውና ባጠቃላይ ዕድገቱ ላይ ዕክል ያጋጥመዋል። ከፍ ሲልም የመጨናገፍ ዕድልም ሊኖር ይችላል።

በተቃራኒው መንገድ የመወለጃ ጊዜው አልፎ በማህጸን የሚቆይ ጽንስ የእናቱን በሕይወት የመኖር ጉዳይ አደጋ ላይ ይጥላል :: አንዲት እናት የጸነሰችውን ጽንስ ለመውለድ ሌሎች ነገሮች እንዳሉ ሆነው ከ37 እስከ 42 ሳምንታት መቆየት አለባት ተብሎ ይታመናል፡፡ ለጽንስ ትክክለኛውን ጊዜ ጠብቆ መወለድ እጅግ ጠቃሚ ጉዳይ ነው፡፡

ስለዚህም አንተም የህልምህን ትክክለኛ ጊዜ አውቀህ ብትሰራበት ልክ ጤናማ ልጅ ወልዶ እንደመሳም ልብ ያሞቃል።

የተወለደውን ልጅ መንከባከብ፣ ማሳደግና ለወግ ማዕረግ ማድረስ ደግሞ የማንም ሳይሆን የወላጅ ኃላፊነት እንደሆነ ሁሉ አንተም እግዚአብሔር በውስጥህ ያስቀመጠውን ራዕይ ጊዜዉን አዉቀህ ወደሚታይ ፍሬ እንድትቀይር ይጠበቅብሃል፡፡
ከተሰኘ መፅሐፍ የተወሰደ

Coming soon!!
05/09/2024

Coming soon!!

16/08/2024

" እግዚአብሔር ግን ሳሙኤልን። ፊቱን የቁመቱንም ዘለግታ አትይ፤ ሰው እንዲያይ እግዚአብሔር አያይምና ናቅሁት፤ ሰው ፊትን ያያል፥ እግዚአብሔር ግን ልብን ያያል አለው።"
(መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ 16:7)

" ቀን ሳለ የላከኝን ሥራ ላደርግ ይገባኛል፤ ማንም ሊሠራ የማይችልባት ሌሊት ትመጣለች።"(የዮሐንስ ወንጌል 9:4)(መጽሐፈ መክብብ ምዕ. 12)----------1፤ የጭንቀት ቀን ሳይመጣ በጕብ...
06/06/2024

" ቀን ሳለ የላከኝን ሥራ ላደርግ ይገባኛል፤ ማንም ሊሠራ የማይችልባት ሌሊት ትመጣለች።"
(የዮሐንስ ወንጌል 9:4)

(መጽሐፈ መክብብ ምዕ. 12)
----------
1፤ የጭንቀት ቀን ሳይመጣ በጕብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ፤ ደስ አያሰኙም የምትላቸውም ዓመታት ሳይደርሱ፤

2፤ ፀሐይና ብርሃን ጨረቃና ከዋክብትም ሳይጨልሙ፥ ደመናትም ከዝናብ በኋላ ሳይመለሱ፤

እድሜ መሄዱ ካልቀረ!

አንድ የ30 አመት ጎልማሳ ብዙ ከወላወለ በኋላ እድሜ ልኩን ሲመኘው የነበረን የምህንድስና ትምህርት ለመማር ለምዝገባ ወደ አንድ ኮሌጅ ሄደ፡፡ ቢሮ እንደገባ የተማሪዎች አማካሪ አገኘውና ሲያማክረው፣ “በመማርና ባለመማር መካከል ብዙ ወላውያለው” አለው፡፡

አማካሪው ምክንያቱን ሲጠይቀው፣ “አሁን 30 አመቴ ነው፡፡ ስመረቅ እኮ 35 ሊሆነኝ ነው” በማለት የመወላወሉን መነሻ ምክንያት ነገረው፡፡

አማካሪው የመለሰለት መልስ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ወደ ትምህርት ገፋው፡፡ “የዛሬ አምስት አመት እኮ ብትማርም ሆነ ባትማር 35 አመት መሙላትህ አይቀርም፡፡ ሳትማር 35 አመት ከሚሞላህ፣ ተምረህ ቢሞላህ አይሻልም?”

እስቲ አንድ ጊዜ ጸጥ በሉና ስንት እድሜ ላይ እናዳላችሁ አስቡት፡፡ ከዚያም በአሁኑ እድሜያች ላይ አምስት አመት ደምሩበት፡፡ ድምሩ ስንት መጣ?

በሉ እንግዲህ . . .
በኢየሱስ ብታምኑም ባታምኑም ዕድሜአችሁ መሄዱ አየሰቀርም፤ ነገር ግን በመጨረሻ የዘለዓለም ሞት ከመሞት በጌታ ኢየሱስ በማመን የዘለዓለም ሕይወት አግኙ።
ለጌታ ብታገለግሉም ባታገለግሉም ዕድሜያቸው ይሄዳል፤ ነገር ግን ሳታገለግሉ ከምታረጁ አክሊል እንዲታገኙ ለጌታ አገለግሉ።

• ብትማሩም ሆነ ባትማሩም የዛሬ አምስት አመት እድሜያችሁ በአምስት አመት መጨመሩ አይቀርም! ሳትማሩ ከሚጨምር፣ እየተማራችሁ ቢጨምር አይሻልም?

• ብትነግዱም ሆነ ባትነግዱም የዛሬ አምስት አመት እድሜያችሁ በአምስት አመት መጨመሩ አይቀርም! ሳትነግዱ ከሚጨምር፣ እየነገዳችሁ ቢጨምር አይሻልም?

• ብታቅዱም ሆነ ባታቅዱም የዛሬ አምስት አመት እድሜያችሁ በአምስት አመት መጨመሩ አይቀርም! ሳተቅዱ ከሚጨምር፣ አቅዳችሁና ተንቀሳቅሳችሁ ቢጨምር አይሻልም?

በእድሜ ምክንያት ከመንቀሳቀስ ራስን ማገድ ማለት፣ ነገ መሞቴ ካልቀረ ዛሬውኑ መኖርን ላቁምና እንደሞተ ሰው ልኑር እንደማለት ነው፡፡

05/06/2024

የእንደገና መርሆች!

እንደገና ሊታረም፣ ሊታደስና በአዲስ መልክ ሊጀመር የማይችል ምንም አይነት ስህተት እንደሌለ በማስታወስ ሳምንታችሁን ጀምሩ፡፡

የማይንቀሳቀስን ነገር ሁሉ ሕይወት የሌለው ግዑዝ ፍጥረት እንለዋለን፡፡ የሚንቀሳቀሰውን ደግሞ ሕይወት ያለው ሕያው ፍጡር እንለዋለን፡፡ ሕይወት ካለ መንቀሳቀስ አለ፡፡ መንቀሳቀስ ካለ ደግሞ ስህተት የማይቀር ነው፡፡ ለስህተት ሊሰጥ የሚገባው ትክክለኛው ምላሽ - እንደገና መነሳት! እንደገና መጀመር! እንደገና መገስገስ! እንደገና!!!

ሆኖም፣ ይህንን የእንደገና አመለካከት ተግባራዊ፣ ሚዛናዊና ጤናማ የሚያደርጉልንን መርሆች አንዘንጋ፡፡

1. ይቅርታ መጠየቅ - እንደገና መነሳት ከፈለጋችሁ፣ ስህተቱ የጎዳው ሰው ካለ ይቅርታን መጠየቅ የግድ ነው፡፡

2. ይቅርታ ማድረግ - እንደገና መነሳት ከፈለጋችሁ፣ ስህተቱ የተከሰተው በሰዎች ሰበብ ከሆነ ሰዎቹን ይቅር ማለት የግድ ነው፡፡

3. በራስ ላይ አለመጨከን - እንደገና መነሳት ከፈለጋችሁ፣ በሰራችሁት ስህተት ምክንያት ራሳችሁን ከመደብደብና ከመኮነን መቆጠብ የግድ ነው፡፡

4. ከስህተቱ ትምህርት ማግኘት - እንደገና መነሳት ከፈለጋችሁ፣ ከተሰራው ስህተት ያላችሁ ብቸኛ ትርፍ፣ ያገኛችሁት ትምህርት መሆኑን በማወቅ ትምህርታችሁን መውሰድና ስህተቱ እንዳይደገም ማቀድ የግድ ነው፡፡

5. እንደገና መጀመር - እንደገና መነሳት ከፈለጋችሁ፣ የተሰራውን ስህተት በማስተካከል እንደገና መጀመር የግድ ነው፡፡

6. በአዲስ መቀየር - እንደገና መነሳት ከፈለጋችሁ፣ ሊታደስ የማይችሉ ሁኔታዎች ካሉ እነዚህን ሁኔታዎች ስታብሰለስሉ መዋል ማደሩን ትታችሁ በአዲስ በመቀየር ወደፊት መራመድ የግድ ነው፡፡

7. ከ“ግን” መጠበቅ - እንደገና መነሳት ከፈለጋችሁ፣ ከላይ የተጠቀሱትንና ሌሎች የእንደገና መነሳት መርሆችን እንዳትተገብሩ ከሚያደርጋችሁ፣ “አዎ፣ ግን . . .” ከሚል ምክንያት ፈላጊነት መጠበቅ የግድ ነው::

05/02/2024

Online telegram
Weekly program of prayer and teaching the word of God.

Ethiopian Local time 2:300@evening.

24/01/2024

✍️

“የመንፈስ ፍሬ ግን #ፍቅር፥ #ደስታ፥ #ሰላም፥ #ትዕግሥት፥ #ቸርነት፥ #በጎነት፥ #እምነት፥ #የውሃት፥ ነው።”
— ገላትያ 5፥22 📖

🙋‍♂ ክፍል አንድ (፩) #ፍቅር

❖ በክርስቲያናዊ ሕይወት ከሁሉም የመንፈስ ፍሬዎች የሚቀድመውና የሚበልጠው የመንፈስ ፍሬ ፍቅር ነው፤ ምክንያቱም

“እኛም #እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን #ፍቅር አውቀናል አምነንማል፤ #እግዚአብሔር #ፍቅር ነው፤ በፍቅርም የሚኖር #በእግዚአብሔር ይኖራል #እግዚአብሔርም በእርሱ ይኖራል” 📖1ኛ ዮሐንስ 4፥16

✅ ባሕርይ ስለሆነ ነው።

“እርስ በርሳችሁ ከመዋደድ በቀር ለማንም ዕዳ አይኑርባችሁ፤ ሌላውን የሚወድ ሕግን ፈጽሞታልና” ፍቅር የሕግ ሁሉ ፍጻሜ ስለሆነ ነው። 📖ሮሜ 13፥8

❖ #የእግዚአብሔር ቃል ይህንን ሲያስረዳ እንዲህም ከሆነ እምነት፣ ተስፋ፣ ፍቅር፣ እነዚህ ሦስቱ ጸንተው ይኖራሉ፤ ከነዚህም የሚበልጠው ፍቅር ነው ይላል።
📖1ኛ ቆሮ 13፥13

❖ ስለዚህ እኛ ክርስቲያኖች ከሁሉ የሚበልጠው ይህ የመንፈስ ፍሬ እንዲታይብን #እግዚአብሔርንም ሰውንም ከልብ ልናፈቅር ይገባናል ፤ ሌሎቹን የመንፈስ ፍሬዎች ከማሰባችን በፊት ፍቅር ሊኖረን ፍቅርን ልንከታተል ያስፈልጋል።

“ፍቅርን ተከታተሉ፥ መንፈሳዊ ስጦታንም ይልቁንም ትንቢት መናገርን በብርቱ ፈልጉ” 📖1ኛ ቆሮንቶስ 14፥1

❖ #እግዚአብሔር አብ ዓለምን ያዳነው በአንድያ ልጁ በተገለጠው እውነተኛና ዘለዓለማዊ ፍቅር ነው ።

❖ አምላካችን ኃጢአተኛ ሆነን ጠላቶቹ ሳለን እንዲሁ ወደደን ልጁ ስለ እኛ በመሞት ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ፤ ይህም #እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን ፍቅር ያስረዳል፡፡

✍️“ነገር ግን ገና ኃጢአተኞች ሳለን #ክርስቶስ ስለ እኛ ሞቶአልና #እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን የራሱን ፍቅር ያስረዳል” እኛም ፍቅርን ያወቅነው በዚህ ነው።
📖ሮሜ 5፥8

ተባረኩ 🙏

ክፍል ሁለት (፪) #ደስታ
ይቀጥላል ...

✍️ #ኢቫን

28/12/2023

በማይጠፋ ብርሃን የወንጌል አገልግሎት ለተከታታይ አርቦች በቴለግራም ግሩፕ
ደቀመዝሙር ማነው? በሚል ርዕስ
በመንድም ዘካሪያስ አሰፋ
ዘውትር አርብ ከምሽቱ 2:30-3:30
https://t.me/+h1s2JbNC84g2MGE0

27/12/2023
26/12/2023

የእግዚአብሔር ብርሃን ጨለማችሁን ይገፈዋል!!

Address

Dila

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bright Light Gospel Ministry page posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share