Ethio-amlake

Ethio-amlake የእግዚአብሔር ፈቃድ ብቻ ይሁን

29/01/2023

#ደብረብርሃን #ኦርቶዶክስ #ፓፓስ #ጅማ #ሸዋ #የሲኖድስመግለጫ

29/01/2023

with Bini ቢሊጮ

29/01/2023

29/01/2023

# 😍...

😭😭😭😭
29/01/2023

😭😭😭😭

@ዳዊት (Dave Muller) ነኝ የተዋህዶ ልጅ @ዝማሬ መላእክት Tewahdo _ተዋህዶ_ነኝ @ፍኖተ ጥበብ @ስለማይነገር ስጦታው እግዚአብሔር ይመስገ.....

ክፍል-6ፍካሬ ኢየሱስ"በዚያን ጊዜ አንዱ: ከምእራብ: ሌላው: ከምስራቅ: ሲመጡ: ይገናኛሉ፣ "ወዴት: ትሄዳላችሁ?": ይሏቸዋል: "ወደምእራብ: መሄድ: እንወዳለን": ይላሉ: "ወደምእራብ: አት...
02/06/2022

ክፍል-6
ፍካሬ ኢየሱስ

"በዚያን ጊዜ አንዱ: ከምእራብ: ሌላው: ከምስራቅ: ሲመጡ: ይገናኛሉ፣ "ወዴት: ትሄዳላችሁ?": ይሏቸዋል: "ወደምእራብ: መሄድ: እንወዳለን": ይላሉ: "ወደምእራብ: አትሂዱ: በዛ: መከራ: አለና": ይላሉ፤ "እናንተስ: ወዴት: ትሄዳላችሁ?": "ወደምስራቅ: መሄድ: እንወዳለን": ይሏቸዋል፣ "ወደምስራቅ: አትሂዱ: ብዙ: መከራ: አለና": ይላሉ።

ራዕየ ሳቤላ

በጦርነት ብቻ አያበቃም፣ ከፍተኛ ረሀብ ቸነፈርና ችጋር እንደሚመጣ ቃሉ ይናገራል። በዛሬ ቀን የቆምን ቢያንስ በረሀቡ ሳይሆን በጦርነት እንኳን ለመሞት ፀሎት ያስፈልገናል። በጦርነት መሞትን እድለኝነት የሚይስብል በረሀብ ስቃይ የሚመጣ የከፋ ሞትም አለና። በመፅሀፍ ቅዱስም በሰይፍ የመጣ ሞት በረሀብ ከመሞት ይሻላል ተብሎ ተፅፏልና።
አባቶቻችን ሰምተዋቸው የማያውቋቸው አዳዲስ እጅግ ወራሪና ፈጣን ገዳይ በሽታዎች በሀገራችን ይገባሉ። (ምልናባትም በአሁኑ ጊዜ በአፍሪካ በመሰራጨት ላይ ያሉት አዳዲስ ገዳይ በሽታዎች ፍንጭ ሊሆኑን ይገባናል።)

"የሞቱትን ሰወች ንዑዳን ክቡራን ናችሁ እስኪሏቸው ድረስ ችግርና ሀዘን ይሆናል"

ራዕየ ሳቤላ

እውነቱ ይህ ነው።
በሀገራችን እግዚአብሄርን ባገለለ መልኩ፣ የሱን ሀሳብና እርዳታ፣ አብሮነት ሳንጠይቅ በምድራዊ ፖለቲካ ስጋዊ ትርምስምስ፣ እሱን አርቀን የምናደርገው የዘረኝነትና ስጋዊነት ሩጫችን ሁሉ መዳረሻው ያ ነው።

ቆርጠን ለስጋዊ ግባችን መጠሪያ ካደረግነው "የኢትዮጵያ ትንሳኤ" በፊት የሚሆነው ይህ ነው።

አይ እምነተቢስነት፣ ከትንቢቶቹ "ትንሳኤ" የምትለውን ቃል ብቻ መርጦ ይዞ በየሚዲያው፣ በየቦታው እየጮሁ ባለቤቱንና ባለቃልኪዳኑን እግዚአብሔር ግን ረስቶና ከድቶ በየቦታው መለፈፍ ቁጣና መከራውን ቢያፀናውንጂ ከዚህ ሁሉ መከራ ከቶ አያድንም። በብልጣብልጥነት የሚሆን ነገር የለምና፣ በተለይ ክርስትያን ነን የምንል ህዝቦች ከቅዱሳን መፅሀፍቱ መልካም መልካሙን በመምረጥ፣ የሚያስፈራንን መተው ከመከራ ፅናት ያለፈ ምንም አያተርፍልንም። ሌላ ለማንም ተብለው አልተፃፉምና፣ አላማቸውም ስለትንሳኤ ሊያስጎመዡን ሳይሆን ለኛው በፍቅርና ቸርነት ተፅፈው ቀድመን አውቀን ከዚህ ከሚመጣው ፅኑ ፍርድና መከራ እንድንድን መድሀኒት ይሆኑልን ዘንድ የተፃፉ ናቸውና

እንደለመድነው መልካም መልካሙን በመምረጥ ይህን ቃል ብንንቅ፣ እሳቱን መጥቶ ካላየን አናምንም ብለን ብንሸሽ በኛው ስልጣን በራሳችን ላይ ሰነፍን እንጂ፣ በማንም አልፈረድንም

ጊዜው ደርሷልና፣ ይህን መልእክት ያየን ብዙዎቻችንም በቸልተኝነትና ልባችን መደንደን ምክንያት ምንም ሳንዘጋጅ እንጠፋለንና፣ ከሞታችን በኋላ በፍርድ ጊዜ የኛው ንግስታችን ንግስተ ሳባ ሳይቀር እንደምትቆምብን መፅሀፍ ይጠቁማል

"ንግሥተ ዓዜብ በፍርድ ቀን ከዚህ ትውልድ ጋር ተነሥታ ትፈርድበታለች፤ የሰሎሞንን ጥበብ ለመስማት ከምድር ዳር መጥታለችና"

ማቴ 12:42

"የነነዌ ሰዎች በፍርድ ከዚህ ትውልድ ጋር ተነሥተው ይፈርዱበታል፤ በዮናስ ስብከት ንስሐ ገብተዋልና"

ሉቃ 11:32

ከእኛው ምእመኑ ጋር ቤተክርስትያናችንም ጭምር እጅግ በበብዙ ስውር በትሮች ብዛትና የሰወችም ችግር በመዳከሟ አብረን ለዚህ የእውቀት ክፍተት ደረስን እንጂ፣ እጅግ በበዙ ቅዱሳት መፅሀፍትና ገናም ባለልቦና ሰው አግኝተው ከግእዝ ያልተተረጎሙና ለህዝብ ባልደረሱ የቤተክርስቲያኒቷ የብራና ቅዱሳት መዛግብት በብዛት የተፃፈ ጉዳይ ነው።

ጥንት በራሳቸው ዘመን መልካም ቀን ቢሆን፣ ያ ሳያዘናጋቸው ጥበበኛ አባቶች በፍቅር ተነሳስተው ለሚመጣው ትውልድ በመጨነቅ በልመና በራእይ ያዩትን ዛሬ እንድንበት ዘንድ የተፃፉ ብዙ አሉ።

ክፍል-5ገዢዎቻችንም ለምን ይሁን በሽታ ይሆን ቆሞ ላየ ግራ እስኪገባ ድረስ ዘለአለም ኗሪ እንኳን በማይዘርፈው መጠን ለማመን የሚያዳግቱ ገንዘብ መጠኖች ያለእረፍት ሲያግበሰብሱ ኖረው፣ ጥቂት ...
02/06/2022

ክፍል-5
ገዢዎቻችንም ለምን ይሁን በሽታ ይሆን ቆሞ ላየ ግራ እስኪገባ ድረስ ዘለአለም ኗሪ እንኳን በማይዘርፈው መጠን ለማመን የሚያዳግቱ ገንዘብ መጠኖች ያለእረፍት ሲያግበሰብሱ ኖረው፣ ጥቂት ስንኳ ሳይነኩለት ለማንም ሲሆን አይተናል።

እነዚህ ከብዙዎቹ የተፃፉ መግለጫዎች ጥቂቶቹ ቢሆኑም በብዙ መልኩ ወደኛ ያመለክታሉ።

ከራሱ፣ ከማንነቱ፣ ከአእምሮው የተጣላ የአመፅ ትውልድ አፍርተን፣ ማንነቱ መንገዱ ምኞቱ ይሄ ነው ለማይባል ላፈራነው ምስኪን ትርምስምስ ትውልድ ይኸው ዛሬ ባለ ድንቅ የባህልና እምነት ታሪክ፣ ብዙ መለኮታዊ ምስጢራት ማህደር የሆነች ሀገርን ከሁሉ በላይ የራሷ ዘመን የማይለውጠው የማይተዋት መንፈሳዊ ባለቤት ያላትን ሀገር እነሆ ሊወዳት ይችል ዘንድ ለማያውቃት ትውልድ ለፍፁም ጥፋቷ የሚሆን ርክክብ ላይ አድርሰናታል። እሷስ የማትጠፋበት ፅኑ ቃልኪዳን አላት፣ ማ እንደሚጠፋ ግን የምናየው ይሆናል

የመፈናቀል፣ የጥላቻ፣ የሞት ዜና፣ የዘረኝነት፣ የቃጠሎ፣ የፍጅት፣ የሀገራዊ ውጥረት ዜና አስጨነቃችሁ?
ዛሬ ይሄ አስጨነቃችሁ?

ከፍቅር በራቀ፣ እግዚአብሄርን በረሳ በዛሬው አካሄዳችን ስንቀጥል
አይቀርምና፣ ፅኑ የማያልፍ የትንቢት ቃሉ ገና የሚሆነውን እንዲህ ነው የሚለው።

"በምስራቅ: ባለች: ታላቅ: ሀገር: በርሷ: ላይ: ሶስት: ቀንና: ሶስት: ሌሊት: ጦርነት: ይነሳል፣ ከጥቂት: ሰወች: በስተቀር: በርሷ: የሚተርፍ: የለም።"

ራዕየ ሳቤላ

ሶስት ቀንና ሶስት ሌሊት ብሎ በምሳሌ አስቀምጦታል፣ እንደ ንሰሀና መመለሳችን ሶስት አመትም፣ ሰላሳም፣ እንደ እስራኤላውያን ሺም ልናደርገው ስልጣኑ በኛው ይመስላል።

ምናልባትም እዚህ ጋር ሰላሳ አመት ሲባል ቀልድ መስሎን ሊታየን ይችላል። ርቀን ሳንሄድ እዚህ ሶማሊያ በጦርነት መሀል፣ መንግስት ሳይኖራት ከ ሰላሳ አመታት በላይ መኖሯን አንርሳ። ያውም አንድ እምነት፣ አንድ ቋንቋ፣ አንድ ባህል ያላቸው ህዝቦች ሆነው። በራስ ሹፈታችንን ትተን ቆም ብለን ማሰብ ይኖርብናል። አላሰቡም ተብሎ የሚቀርልን መከራ የለምና

"በዚያን ዘመን : የሚጣፍጠው: ውሀ፣ የሚጥመው: እህል: መራራ: ይሆናል፣ ህዝብ: እርስ: በርስ: ይተላለቃል"

ፍካሬ ኢየሱስ

"ደግሞ: በክንፍ: የሚሰበስብ: አሞራ: እልካለሁ፣ እሱም: ፮፻፻፻፵፰: በግና: ፍየል: ባንድ: ቀን: የሚገድል: ነው። ከነዚያውም: የተዘጋጀ: የለም። በግና: ፍየል: ያልኋቸው: ፃድቃንና: ኃጥአን: ናቸው።"

ክፍል-4አልፎም በመፅሀፍ ቅዱስ ላይ የአሶር ንጉስ ኢየሩሳሌምን ለማጥፋት በተነሳ ጊዜ፣ ህዝቅያስን ባስጨነቀ ጊዜ በነቢዩ ኢሳያስ በኩል ወደእግዚአብሄር ባለቀሰ ጊዜ እግዚአብሄር ኢየሩሳሌምን ከ...
02/06/2022

ክፍል-4
አልፎም በመፅሀፍ ቅዱስ ላይ የአሶር ንጉስ ኢየሩሳሌምን ለማጥፋት በተነሳ ጊዜ፣ ህዝቅያስን ባስጨነቀ ጊዜ በነቢዩ ኢሳያስ በኩል ወደእግዚአብሄር ባለቀሰ ጊዜ እግዚአብሄር ኢየሩሳሌምን ከወረራ ለማትረፍ ቢፈልግ ከደቡብ በአሶር ንጉስ ላይ ያስነሳው ይህንን ታላቅ ንጉስ ነበር። ይህንንም ሲገልፅ በመፅሀፍ ቅዱስ ሁለት ቦታዎች ላይ "የኢትዮጵያ ንጉሥ ቲርሐቅ ሊወጋህ መጥቶአል የሚል ወሬ በሰማ ጊዜ ደግሞ ወደ ሕዝቅያስ መልእክተኞችን ላከ..." ብሎ ይህንን እስከ ሶሪያ ድረስ የዘመተ የኢትዮጵያ ታላቅ ንጉስ ይገልፀዋል።

" በዚያን ጊዜ: አሉባልታ: ትእቢት: ስድብ: ራስን: መውደድና: ማክበር: መማለጃ: ተቀብሎ: ፍርድ: ማጣመም፣ ገንዘብ: መቀማት፣ ወንድምን: መግደል". . . "ድንበር: ማፍረስ፣ ወሰን: መግፋት". . . "ፍቅር: ከነሳቸው: ይርቃል።"

ፍካሬ ኢየሱስ

" በዚያን ጊዜ: ለብዙ: ክብር: የታጩ: በማዕርግ: በሹመት: ያደጉ: በከፍተኛ: ደረጃ: ላይ: የሚገኙ: ሁሉ: አደራቸውን: ይዘነጋሉ፣ ሀገራቸውን: ይከዳሉ፣ መሀላቸውን: ያፈርሳሉ፣ ከባለሟልነታቸው: ይወጣሉ፣ ከማዕርግና: ሹመት: ጓደኞቻቸው: ይለያሉ". . ."ባለስልጣኖች: ከአመፀኞች: ጋር: ይተባበራሉ:". . ."ክፉ: ስራቸው: በተገለፀባቸው: ጊዜ: ይፀፀታሉ"

ፍካሬ ኢየሱስ

" በዚያን ጊዜ: የምድረበዳ: አውሬዎች: ቦታቸውን: ትተው: ወደከተማ: ይገባሉ። አውሬ: የተባሉ: ባሕታውያን: ናቸው። ባሕታውያን: ነን: ሲሉ: የብትሕናውን: ስራ: አይሰሩም፣ ፆም: ፀሎት: ሌሊት: መንቃት: የለባቸውም". . ."ወንድማቸውን: ባለንጀራቸውን: አይወዱም: እንደ: ዓለማዊ: ሰው: የዚህን: ዓለም: ሹመት: ይሻሉ: "

ፍካሬ ኢየሱስ

" ውሀ አሻቅቦ: ይፈሳል። ውሀ: አሻቅቦ: ይፈሳል: የተባለው: የማይገባቸው: እኔ: እነግስ: እኔ: እነግስ: የሚሉ: ናቸው።"

ፍካሬ ኢየሱስ

ካገላለፃቸው ዘመናችንን ከኛ ከኖርንበት የተሻለ ያውቁታል ብንል ሐሰት አይሆንም

" ከሴቶችም : ሸብቶ፣ ጥርስ አውጥቶ ይወለዳል። የሚጣፍጠውም ውሀ ይመራል፣ ወዳጆችም እንደጠላት ድንገት እርስበርሳቸው ይጋደላሉ።"

ፍካሬ ኢየሱስ

ልጆች በብዙ ነገር ነቅተው፣ እንደልጅ ሳይሆን እንደአዋቂ ሆነው እንደሚወለዱ፣ ፊት ፊት እንደሚሉ በምሳሌ ይገልፀዋል

" የእግዚአብሄርን: መኖር: ይዘነጋሉ". . . "ገንዘባቸውንና: ወርቃቸውን: የሚያከማቹበት: ከፍተኛ: ሳጥን: ለማዘጋጀት: ይፋጠናሉ: ነፍሳቸውንም: ለብዙ: ዘመን: የሚበቃሽ: የደለበ: እህል: የተከማቸ: ገንዘብ: አለሽና: እንግዲህ: ዓርፈሽ: ብዪ: ጠጪ: ደስም: ይበልሽ: ይሏታል። ነገርግን: ባላሰቡበት: ሰዓትና: ጊዜ: ሞት: ነፍሳቸውን: ነጥቆ: ይወስዳታል። ያደለቡትና: ያከማቹት: ሀብት: ለማንም: ይሆናል። እግዚአብሄርን: ያላሰበ: በባለጠግነቱም: ብዛት: የተማመነ: ዕድሉ: እንዲህ: ይሆናል።"

ፍካሬ ኢየሱስ

ይሄም ሁላችንም የምናምነው የተለመደ ሐቅ ነው። ከመደበኛው ህዝብ እግዚአብሄርን ከትርፍ ጊዜ ርእስ አሳልፎ የሚያስብ ማንም የለም። እንደተገለፀው ሁላችንም ሩጫችን ለልጆቻችንም እንደባህል የህይወት አላማ ብለን የምናስተምረው እንደምንም በሁሉ ተሯሩጠን የባንክ አካውንታችንን መሙላት ነው። መመኪያም የህይወት መለኪያም የምናደርገው እንደተጠቀሰው በገንዘብ ጎተራችን (አካውንታችን) ያለንን የገንዘብ መጠን ነው።
ውጤቱም አልቀረ፣ እንደወጡ መቅረት፣ በአደጋ፣ በተኛንበት፣ "ባላሰቡት ሰአትና ጊዜ" እንዳለው በሞት መወሰድን ፍፁም ተላምደነው የለተለት ነገር ሆኗል፣ ገንዘቡም ለማንም ይሆናል።

ክፍል-3የጥንት ኢትዮጵያውያን ይህ በአምላክ የተወደደ ባህል፣ ስነልቦናና አኗኗራቸው እንዲሁ አፈታሪክ፣ እራስንም በባዶ መካብ ይሚሉ ነው ይኖራሉና ነገር በምስክር ይፀናል እንዲል የጥንት ከኛ ...
02/06/2022

ክፍል-3
የጥንት ኢትዮጵያውያን ይህ በአምላክ የተወደደ ባህል፣ ስነልቦናና አኗኗራቸው እንዲሁ አፈታሪክ፣ እራስንም በባዶ መካብ ይሚሉ ነው ይኖራሉና ነገር በምስክር ይፀናል እንዲል የጥንት ከኛ መዛግብት ውጪ ባሉ በዘመኑ በታዘቡ የውጭ ምስክሮች እንኳን እንደገለፁት
ሆሜር እውቁ የግሪክ ባለቅኔ "የኢትዮጵያ ሰወች በጉልበት ኃያላን፣ በውበት የተደነቁ፣ በጠባይ ጭምቶች ትህትናን የተሞሉ..." ብሎ ሲገልፃቸው፣

ታላቁ የምእራባውያን የታሪክ አባት የሚባለው ግሪካዊው ሔሮዳይተስ ደግሞ ኢትዮጵያውያን ሲገልፅ "እጅግ ያማሩ ሕዝቦች ያሉባት፣ ርህራሄያቸው እንደ እግዚአብሔር የሆነ፣ ምንም መንገደኛ የሚበላው የማያጣባት ፣ በእድሜያቸው ክ100-130 አመት የሚኖሩ፣ ነውርና ክፉ ነገር በሀገራቸው የተጠላ፣ የጤና ምንጭ የሚሆኑ ውሆች ያሏቸው፣ እነሱን በጠጡ ጊዜ ሰውነታቸው የሚታደስ (ፀበል?) " በማለት ድንበሯም አልፎ እስከነጭ አባይ እንደነበረ ጠቅሶ የኢትዮጵያን ህዝብ አኗኗርና በእምነታዊ ኑሯቸው ያገኙትን የአምላክ በረከትና ቅርበት ይመሰክራሉ።

ይህ ፍልስፍና፣ እምነትና በእንቁ ማህበራዊ እሴቶች የተገነባ ማንነታችን እንዲሁ የተወሰኑ አናሳ ጥቃቅን ህዝቦች ለአጭር ጊዜ የነበራቸው ማንነት ሳይሆን፣ እጅግ በግዙፉ የሰራ፣ ለረዥም ጊዜ በታላቅ ግዝፈት ተተግብሮ የተኖረበት፣ የሰው ልጅና አእምሮው በልዕልና ላይ ደርሰው በሰፊውና በቀጣይነት ሊኖሩ የሚችሉበት ታላቅ ስርአት ነውንጂ። ለዚህም ምስክር የሚሆኑን፣ ኢትዮጵያውያን በአናሳነት ተወስነው የቆዩ ሳይሆኑ በታላቅነት ሲሄዱ የነበሩበት መሆኑ ነው።
የዘመኑ ትውልድ ማንነቱን ይቀበለውም አይቀበለውም፣ በዚህ ማንነት የቀድሞው አክሱም መንግስት በዘመኑ "የምድር 5ቱ ምሶሶዎች" ከተባሉት ታላላቅ መንግስታት ዋናው ነበር። ይህቺን ምድር ካስተዳደሩ ታላላቆቹ 5 ነገስታት ዋናው ተብሎ ነበር የሚጠቀሰው። ብሎም አለማቀፍ ታሪክ እንደሚናገረው ከዛ በፊት የነበሩት የኢትዮጵያ ነገስታት ታላቅነታቸው ከዛ በእጅጉ የጨመረ እንጂ የቀነሰ አልነበረም።
በመፅሀፈ ነገስት እንዲሁም በትንቢተ ኢሳያስ ተደጋግሞ "የኢትዮጵያው ንጉስ ቲርሐቅ" ተብሎ የተጠቀሰው ታላቅ ንጉስ ኢትዮጵያን አልፎ በግብፅም በመንገሱ ታላላቅ ፈርኦኖች ከሚባሉት ዋናው ሆኖ በታሪክ ተዘግቧል።
ይህም የኢትዮጵያውያን የራስ ማኮፈስ ወሬ ሳይሆን ከኛ ይልቅ በሌላው አለም የተዘገበ ነው። መቼም የዛሬዋ ኢትዮጵያ ልጆች በውጪዎች ካልተነገራቸው አለማመናቸው እጅግ አሳዛኝ፣ የማትገባቸውን ሀገር ላይ የተወለዱ ቢያስመስላቸውም፤ እነሱ ከፈለጉ ለቀዋት ሊሄዱ ይችላሉ እንጂ ታሪክ እንደሆነ ታሪክ ነው፤ ለዘላለም ፅኑ ሀቅ ነው።
ይህ ሐቅ በመሆኑም የዚህ ኢትዮጵያዊ ንጉስ ታላቅነት ከአፍሪካውያን ይልቅ የራሳቸውን በማግነን በሚታሙት የውጭ ሀገራት ሰወች ሳይቀር ሊካድ ያልተቻለው ሀቅ ነው።
የተባለው ታዋቂ የግሪክ የጂዎግራፊ አባት ስታርቦ በፅሁፎቹ ይህ ንጉስ አልፎ እስከ አውሮፓ ክፍሎች ድረስ በእጁ ያስገባ መሆኑን እንደዘገበ "Starbo" በሚል ርእስ የሀርቫርድ ዩኒቨርሲቲ ባሳተመው ፅሁፍ ላይ ማግኘት ይቻላል።
አልፎም በሌሎች ፅሁፎች ይህ ታላቅ ንጉስ ብሎም በስፔን ምድር እስከሚገኘው "የሄርኩሊስ ምሶሶዎች" እስከሚባሉት ቦታዎች የተቆጣጠረ ታላቅ ንጉስ እንደነበረ በ1975 የሀርቫርድ ዩኒቨርሲቲ "Before Color Prejudice: The Ancient View of Blacks" በሚል ባሳተመው ፅሁፍ ላይ ማግኘት ይቻላል።

ክፍል-2ሙሉ ህይወታችንን ተወልደን ያደግነው በዚሁ ዘመን በመሆኑ፣ ከዚህም ዘመን አኗኗር ሌላ አይተንም ስለማናውቅ ራሳችንን አወዳድረን ከሰው የተፈጠረበት አኗኗር ስተናል/ቀርበናል የሚለውን ል...
02/06/2022

ክፍል-2
ሙሉ ህይወታችንን ተወልደን ያደግነው በዚሁ ዘመን በመሆኑ፣ ከዚህም ዘመን አኗኗር ሌላ አይተንም ስለማናውቅ ራሳችንን አወዳድረን ከሰው የተፈጠረበት አኗኗር ስተናል/ቀርበናል የሚለውን ልናውቅ አንችል ይሆናል። ነገር ግን የቀደሞችን አኗኗር የተዘገበውን፣ ያባቶቻችን ከእግዚአብሄር ጋር አኗኗር የተፃፈውን ሁሉ ለማየት ገድ ሰጥቶን አያውቅም እንጂ ምን ያክል በአስፈሪ ደረጃ ፈጣሪ አስቦ ከፈጠረን የአኗኗር ሁኔታና የሱ ልጅነት ህይወት እንደራቅን ማየት በቻልን ነበር።
ዛሬ ኢትዮጵያውያን ከልባችንና ታሪካችን በተቃራኒ እግዚአብሄርን ከህይወትና ስራችን እጅግ አርቀን እንደ አህዛብ በስም ብቻ በማያዝ፣ ጭራሽ መሬት ላይ እንደሚታየው ማንም ሳያስገድደን ልጆቻችን ስሙን በአደባባይ መጥራትን እንዲሸማቀቁበት ለሚያደርግ ትምህርት እንዲሁም አስተዳደግ አሳልፈን ሰጥተን፣ ትልቁንና ዋናውን የአለም አካል የሆነውን ፈጣሪ ከህይወታችን አስወጥተንና ክደን፣ በስጋችን እኛ ለሁሉ ብለን፣ ከሁሉ አልፎም የአምላክን ስም በአደባባይ መጥራትን የሚጠየፍና የሚያስጠይፍ የአስተዳደር ርእዮትና መዋቅር ባልገባን መልኩ ተቀብለንና አውጀን የማይፈታ ቅዠት፣ ትርምስና ግራ መጋባት ውስጥ እንገኛለን።
ተቀበልነው አልተቀበልነው የሀገሪቱም ሆነ የአለሙ ሁሉ ባለቤትና አድራጊ ባለስልጣን እሱ ነውና በዘመናችን የሚፈፀመው የሚሆነውን የገለጠላቸው ተናግረውት፣ እንዲሁም በበዙ የትንቢት መፅሀፍት ላይ ሰፍሮ ይገኛል።

ይህ ለዘመናት ሲጠበቅ የነበረው "የኢትዮጵያ ትንሳኤ" ተብሎ በብዛት የሚታወቀውን ጨምሮ የብዙ ነገሮች መፈፀሚያ የሆነው ጊዜ ፍፁም ስለመቅረቡ ምስክር ይሆነን ዘንድ የተፃፉት ምልክቶችን ስንመለከታቸው፣ ጊዜው እጅግ እጅግ መቅረቡን እየመሰከሩ ብቻ ሳይሆን ያለፍነው እስኪመስል ድረስ በገሀድ ተፈፅመዋል።

ለመሆኑ እነዚህ ማንን/የትኛውን ትውልድ ይገልፃሉ?

እስኪ የተፃፉትን ቃል በቃል እንመልከታቸው...

" ነጋድያን: ወዲያና: ወዲህ: ብለው: እንዳይነግዱ: የባህር: ወደብ: ይዘጋባቸዋል፣ የዚያን: ጊዜ: ንብረት: ብላሽ: ነው"

ፍካሬ ኢየሱስ

በዚያ ጊዜ ወደብ አልባ መሆናችን፣ ረብህ የሌላቸው እቃዎች መወረራችን ቀድሞ ተነግሯል

"ባህላቸውን: ይለውጣሉ፣ የያዙትን: ይጥላሉ፣ ያላዩትን: ይናፍቃሉ፣ ሰብአዊ: ባህሪያቸውን: በእንሰሳ: ባህርይ: ይለውጣሉ፣ ነውርን: ይንቃሉ፣ ኃፍረታቸውን: ይገልጣሉ. . .

እግዚአብሔር: ኃጢያታቸውን: ስለታገሳቸው: እንደሌለ: ይቆጥሩታል፣ በስራቸው: የጎሰቆሉ: በሀሳባቸው: የረከሱ: ናቸው።"

ፍካሬ ኢየሱስ

በመፅሀፍ ቅዱስ ላይ "እርሱም አለ፦ ፊቴን እሰውርባቸዋለሁ ፍጻሜያቸው ምን እንደ ሆነ አያለሁ፤ ጠማማ ትውልድ፥ ያልታመኑም ልጆች ናቸው።"
ብሎ እግዚአብሄር የተናገረውቃል፣ ልጆቹ የሆንን ግን የረሳነው የዛሬዎቹን እኛን በደንብ ይገልፀናል።

" የሀገር: ፍቅር፣ የወገን: ክብር: አይሰማቸውም፣ የአባት: እናታቸውን: ምክር: አይቀበሉም: ተውን: ልቀቁን: እንሩጥ: እንፈርጥጥ: ይላሉ". . . "እድሜያቸው: ያጥራል፣ በወጣትነት: ዘመናቸው: ይቀሰፋሉ"

ፍካሬ ኢየሱስ

ከአገላለፁ እንደምንረዳው ራእዮቹ በተፃፉባቸው ጊዜያት ከነበረው የእምነት እሴቶችና ስብእና ጋር እያወዳደሩ እንደሆነ ይጠቁማል
በጥንት ኢትዮጵያውያን ዘንድ የነበሩትን ወርቃማ እሴቶች ዛሬ ላይ ያለን አናውቃቸውምና፣ የኛን ትውልድ የገለፁበት መንገድ እንዲሁ በባዶ እየወቀሱን መስሎ ሊሰማን ይችላል።

Address

Dessie

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio-amlake posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Ethio-amlake:

Share