Christian Press

Christian Press Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Christian Press, Religious organisation, Bishoftu, Debre Zeyit.

ይህን ፔጅ ላይክ በማድረግ የተለያዩ ስለ መንፈሳዊ መዝሙሮችን፣ስብከቶችን፣ማህበራዊ ጉዳዮች መረጃ ያግኙ
የዩቲዩብ ቻናላችንን subscribe በማድረግ ይቀላቀሉን
https://youtube.com/?si=sA00pDgsGfkSGsIz

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስልለሚመለከተው ሁሉጉዳዩ - አስቸኳይ ማስተካከያ እንዲደረግ ስለመጠየቅ ይሆናል፡፡የአማኑኤል ሕብረት ቤተ ክርስቲያን በካውንስሉ በህግ ተመዝ...
24/12/2025

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል

ለሚመለከተው ሁሉ

ጉዳዩ - አስቸኳይ ማስተካከያ እንዲደረግ ስለመጠየቅ ይሆናል፡፡

የአማኑኤል ሕብረት ቤተ ክርስቲያን በካውንስሉ በህግ ተመዝግባ የምትንቀሳቀስና ላለፉት ረጅም አመታት መንፈሳዊና ሁለንተናዊ ተግባራትን በአገር ውስጥና በመላው አለም ስታከናውን የቆየች ቤተ እምነት መሆኗ ይታወቃል ።

ቤተ ክርስቲያኒቱ እንደ ማንኛውም የሐይማኖት ተቋም ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለስርዓተ አምልኮ ማስፈጸሚያ የሚሆን ቦታ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 02 እንድትረከብ በተወሰነላት መሰረት አስፈላጊውን ካሳ ከፍላ እያለ ቤቱን ማስረከብ የነበረበት የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በልዩ ልዩ ምክንያት ተፈጻሚ ሳያደርግ ቆይቷል፡፡

ከዚህም በተጨማሪ አስፈላጊውን ክፍያ አከናውና ላለችው የአማኑኤል ሕብረት ቤተክርስቲያን ማስረከብ ሲገባው ይባስ ብሎ ቦታውን ለእስልምና እምነት ተከታዮች መሰጠቱን በመስማታችን የተሰማን ቅሬታ ከፍተኛ ነው፡፡

ይህ አይነቱ አሰራር በኃይማኖት ተቋማት መካከል ሊያስከትል የሚችለው ግጭት ከግምት ውስጥ ያላስገባ በመሆኑ በአስቸኳይ እንዲታረም ስንጠይቅ በሐዘን ነው፡፡

የተወሰደው ኢ-ፍትሐዊ እርምጃ ሐይማኖትን ከሐይማኖት እንዲሁም በሕዝብ መካከል ከሚፈጥረው ግጭት ባሻገር የፍትህ ስርዓቱን አደጋ ላይ የሚጥል በመሆኑ ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላትም ይህንን ተግባር እንድታስቆሙልን በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡

ከኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ዋና ጽ/ቤት

የአርሰናሉ ኮከብ የመስመር ተከላካይ ቲምበር በአርሰናል ክለብ ውስጥ  የመፅሐፍ ቅዱስ ጥናት ቲም ( Bible study team) ያቋቋመ ሲሆን ራይስ ፣ሳካ  ፣ማዱዌኬ እንደተቀላቀሉትም እየተነ...
14/12/2025

የአርሰናሉ ኮከብ የመስመር ተከላካይ ቲምበር በአርሰናል ክለብ ውስጥ የመፅሐፍ ቅዱስ ጥናት ቲም ( Bible study team) ያቋቋመ ሲሆን ራይስ ፣ሳካ ፣ማዱዌኬ እንደተቀላቀሉትም እየተነገረ ነው ።

ይሄ ነገር ወደ ደጋፊዎች ብናመጣውስ ?🥰😍

ከእንዳለ ጌታ ከበደ ጋር ያደረገችው ቃለ ምልልሱ በእርግጥ በሙሉ፣ ዘሪቱ ከዚህ በፊት በይፋ ካሳየችው ምስል በተለየ መልኩ፣ እጅግ ግልጽ በሆኑ እና የግል ትግሏን በሚያሳዩ ሐሳቦች የተሞላ ነበ...
15/11/2025

ከእንዳለ ጌታ ከበደ ጋር ያደረገችው ቃለ ምልልሱ በእርግጥ በሙሉ፣ ዘሪቱ ከዚህ በፊት በይፋ ካሳየችው ምስል በተለየ መልኩ፣ እጅግ ግልጽ በሆኑ እና የግል ትግሏን በሚያሳዩ ሐሳቦች የተሞላ ነበር። ምናልባትም ዋነኛው እና ያልተጠበቀው ንግግሯ፣ ቀደም ባሉት ጊዜያት በህዝብ ዘንድ ከፍተኛ መሳለቂያ እና ትችት የዳረጓትን ክስተቶች አሁን ላይ እንዴት እንደምትመለከታቸው የሰጠችው ማብራሪያ ነው።

⭐️ "የመጀመሪያው ስደቴ ጠቅሞኛል"

በጣም አስገራሚ ከነበሩት ንግግሮች አንዱ፣ በ2000ዎቹ መጀመሪያ ላይ በአንድ ኮንሰርት ላይ "ዲጄ ያምቦሌን ክፈትላቸው!" በማለቷ የደረሰባትን ከፍተኛ የህዝብ ትችት እና ስድብ እንዴት እንደተጠቀመችበት ስትገልጽ ነው፦

"የመጀመሪያ ስደቴ እሱ ነበር። ብዙ ተቃውሞ፣ ብዙ ስድብ በይፋ ያስተናገድኩበት... [ግን] ጠቅሞኛል።"

ዘሪቱ እንደገለጸችው፣ በወቅቱ በዝና፣ በተወዳጅነት እና በስራ ብዛት (ቢዚነስ) ተወጥራ ነበር። ይህ ሁከት ደግሞ ወደ እምነት ህይወት ለመቅረብ ብትፈልግም "ፋታ" እንዳልሰጣት ተናግራለች።

በ"ያምቦሌ" ክስተት ምክንያት የመጣው የህዝብ ትችት እና "ስደት" ግን፣ ከዚህ ሁሉ ጫጫታ እንድትርቅ እና ቤት ውስጥ እንድትቀመጥ አስገደዳት። ይህንን ጊዜ "አረፍ ብዬ በቤቴ ሆኜ የእግዚአብሔርን ቃል እንድከፍት፣ መጽሐፍ ቅዱሴን እንዳነብ እድል የሰጠኝ" በማለት ገልጻዋለች።

በአጭሩ፣ ብዙዎች እንደ ውድቀት እና ማፈሪያ ያዩትን ክስተት፣ እሷ ለመንፈሳዊ ህይወቷ መሰረት የጣለላት "ጠቃሚ" አጋጣሚ አድርጋ መናገሯ አስገራሚ ነበር።

የአለም ቤዛ እየሱስ እንጂ ማርያም አይደለችም ‼️በዛሬው ዕለት የሮማ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን የዓለም ቤዛ ኢየሱስ እንጂ ማርያም አይደለችም በማለት ይፋ አደረገች።የማርያምን ተሳትፎ ለመግለጽ አ...
05/11/2025

የአለም ቤዛ እየሱስ እንጂ ማርያም አይደለችም ‼️

በዛሬው ዕለት የሮማ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን የዓለም ቤዛ ኢየሱስ እንጂ ማርያም አይደለችም በማለት ይፋ አደረገች።

የማርያምን ተሳትፎ ለመግለጽ አብሮ አዳኝ "co-redemptrix ማለት ፈጽሞ ተገቢ አይደለም በማለት ገልጻለች።

የኢየሱስ አስታራቂነትን(ምልጃን) ብቸኛ እና ማንም የማይጋራው እንደሆነ ገልጸው፤ ኢየሱስ ብቸኛ አስታራቂ ነው፤ በማለት Mediatrix ፍጹም አምላክ እና ፍጹም ሰው ለሆነ ለኢየሱስ የተገባ ነው።

ሙሉውን ለማንበብ ከፈለጋችሁ ሊንኩ ኮሜንት ላይ አለ።
የናዝሬቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻውን ጌታ ነው✝️

ከጨካኙ ፖለቲካችን ባሻገር!በዶ/ር ደሳለኝ ጫኔየሀገራችን ፖለቲካ እጅግ የተበላሸ፣ የጨካኝ አረመኔዎች እና ሆዳሞች መድረክ መሆኑ ብዙ ተብሎበታል። ከፖለቲካችን ባለፈ የባህል መበስበስ  እንደገ...
23/10/2025

ከጨካኙ ፖለቲካችን ባሻገር!
በዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ

የሀገራችን ፖለቲካ እጅግ የተበላሸ፣ የጨካኝ አረመኔዎች እና ሆዳሞች መድረክ መሆኑ ብዙ ተብሎበታል። ከፖለቲካችን ባለፈ የባህል መበስበስ እንደገጠመንም ብዙ ሲባል እሰማለሁ። እንደ ማህበረሰብ የደረስንበትን የመበስበስ ወይም የንቅዘት ደረጃ ለመመልከት ግን የማህበራዊ ሚዲያ በተለይም የፌስቡክ እና ቲክቶክ አጠቃቀማችንን ብቻ በጥቂቱ መቃኘት በቂ ነው። አንድ ሰሞኑን የተፈጠረ የፌስቡክ ገጠመኝ ግን በዚህ ጉዳይ ላይ ለረዢም ጊዜ በአንጎሌ ውስጥ ሲመላለስ የቆየ ጉዳይ ላይ ይቺን አጭር ማህበራዊ ሂስ እንድሰጥ አስገድዶኛል።

በቅርቡ አንድ ወጣት (የቤተ ክርስቲያን አገልጋይ እንደሆነ ተገልጿል) በቅንነትና በፍቅር የትዳር አጋር ትሆነኛለች ብሎ ያጫትን ሴት ለትዳር መጠየቁን እንደዘመኑ ወጣቶች የ"ታገቢኛለሽ ወይ?" ዝግጅት አዘጋጅቶ መጠየቁን እና እጮኛውም ጥያቄውን በደስታ መቀበሏን አስመልክቶ ለወዳጅ ዘመዶቹ በማህበራዊ ሚዲያ ደስታውን ያጋራል።

በአጭር ጊዜ ውስጥ ማኅበራዊ ሚዲያው በፌዝ እና በአካል ገጽታ ማሸማቀቅ (Body Shaming) ኮሜንቶች መሞላቱን ሳይ ግን እጅግ በጣም ደነገጥሁ፣ ሰቀጠጠኝ። ድርጊቱ አሳፋሪና አሳዛኝ ነው። እንደ ማህበረሰብ የደረስንበትን ዝቅታ የሚያሳይ ይመስለኛል። ትንሽ ማሰብ የሚችል ሰው እንዴት ፍቅርን በሰውነት ቅርጽ መመዘን ጎጂና ኋላቀር ባህል መሆኑን መረዳት ይሳነዋል? የዚህ ድርጊት ምንጭ የት ላይ ነው የሚለው ላይ ጥቂት ልበል።

• ይህ አካሄድ የውስጣችንን ባዶነት እና የተሸረሸረ እሴት በግላጭ ማሳያ ነው፦ የአንድን ሰው ክብር፣ ዋጋ እና ደስታ የምንለካው በአካላዊ ገጽታው (መወፈር እና መክሳቱ) ከሆነ፣ ችግሩ ያለው በሰዎቹ አካላዊ ተፈጥሮ ላይ ሳይሆን፣ በአስተሳሰባችን ጥልቀት ማጣት እና ደመነፍሳዊ ስሜታችን (id) መግራት ያለመቻላችን ላይ ነው። ፍቅር ማለት ነፍስ ከነፍስ የምትገናኝበት ድልድይ እንጂ፣ በቁመና ላይ የተመሠረተ ጊዜያዊ ስሜት አይደለም። የሰው ልጅ አካላዊ ውበት፣ የሰውነት ቅርጽ እና ገጽታ ከጤና፣ ከእድሜና ከኑሮ ሁኔታ ጋር ይቀያየራል። እውነተኛ ፍቅር ግን በሁኔታዎች የሚቀያየር አይደለም።

• እንደ ማህበረሰብ ሲበዛ ፌዘኞች እና ጨካኞች ሆነናል፦ ፌዝን እንቀንስ፣ እንሰልጥን፣ የሰውን ስሜትና ፍቅር እናክብር። ማንኛውም ሰው በፈለገው ሰው መወደድ እና የፈለገውን የመውደድ መብት አለው። የሌላ ሰውን የግል ምርጫ እና ደስታ ማፌዣ ማድረግ የጭካኔ እና የሞራል ውድቀት ማሳያ ነው። የሰውነት ቅርፅ የህዝብ መወያያ አጀንዳ ሳይሆን፤ የግለሰቡ የግል ጉዳይ ነው።

• የሴት ልጅ እሴት በሰውነቷ ቅርጽ አይወሰንም፦ በተለይ ደግሞ የሴቶችን ውበትና ዋጋ በውጫዊ ቅርጽ ብቻ መመዘን፣ በዓለም ላይ ከብዙ ዘመናት በፊት የቀረ ኋላቀር እና ጎጂ አስተሳሰብ ነው። እውነተኛ ውበት፣ ጥንካሬ እና ክብር ከውስጥ የሚመነጭ ነው።

ይህንን መርዛማ አስተሳሰብ እና ባህል (Toxic Culture) በጋራ እንቃወም! ሴቶችን በሰውነት ገጽታቸው ማዋረድ (Body Shaming) ላይ የተመሠረተ ማንኛውም አስተያየት በማህበረሰባችን ውስጥ ቦታ ሊነፈገው ይገባል።

የታገቢኛለሽ ወይ ጥያቄ ላቀረበው ወጣት የቤተ ክርስቲያን አገልጋይና እጮኛው መልካም ጋብቻ እመኛለሁ፣ እግዚአብሔር ጋብቻችሁን ይባርክላችሁ!

ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ

 !ሰዎች ያላሉትን ብሎ በውሸት የሰዎችን ስም በማጥፋት፣ የተሳሳተ ስም መለጠፍ ቀላል በሆነበት በዚህን ጊዜ፣ እውነት መናገር እንጂ ብርቁ መዋሸትማ የተለመደ ነው።የእህታችን ዘሪሁ ከበደ መጽሐ...
23/10/2025

!

ሰዎች ያላሉትን ብሎ በውሸት የሰዎችን ስም በማጥፋት፣ የተሳሳተ ስም መለጠፍ ቀላል በሆነበት በዚህን ጊዜ፣ እውነት መናገር እንጂ ብርቁ መዋሸትማ የተለመደ ነው።

የእህታችን ዘሪሁ ከበደ መጽሐፍ ከወጣ በኃላ ሰሞኑን አንድ ልጥፍ ሲዘዋወር ተመለከትኩ "ከብዙ ወንዶች ጋር ተኝቻለሁ" የሚል። ይህን ልጥፍ ካየሁ በኃላ፣ መጽሐፏን አነበብኩት። እንደዚህ የሚል ሐሳብ፣ ንግግር በመጽሐፉ ውስጥ የለም!! ታዲያ ይህን ማለቱ ለምን አስፈለገ? የሚል ጥያቄ ጭሮብኛል።

በዚህ መልዕክት የምናያቸው ነገሮች፦ የመጀመሪያው ዘሪቱ፣ 'ለትውልዱ እንደዚህ አይነት መልዕክት አስተላለፈች' የሚል ሲሆን፣ ሁለተኛው 'ዘሪቱን በሰዎች ዘንድ እንድትጠላ' ማድረግ ነው። ከዘፈን አለምና፣ ከአርቱ አለም ወደ ወንጌል የሚመጡ ሰዎችን ስም በውሸት የማጥፋት ነገር የተለመደ ቢሆንም፣ ዋናው ነጥብ ዘሪቱ በመጽሐፏ ውስጥ እንደዚህ የሚል ሐሳብ አልጻፈችም።

በመሰረቱ ሰው ከብዙ ውድቀት ወደ ጌታ ሊመጣ ይችላል፣ ኢየሱስ የምህረት እጅና የአባትነት ልብ አለው። ቢሆንም ንስሐ የተገባበት ህይወት ከሆነ፣ በምህረት ታጥቧል። ነገር ግን ዘሪቱ እንዲህ የሚል ሐሳብና መልዕክት አልጻፈችም። የተባለው ውሸት ነው።


Christian zema tube

18/10/2025

የነገስታት ንጉስ
የጌቶች ሁሉ ጌታ የሆነው

::

ሰላምና ፀጋ ለተወደዳችሁ ቅዱሳን ቤተሰቦቼ ይሁን እያልሁ በሰሞኑ በተለያዩ የማህበራዊ ድህረገፆች በምስልና ተንቀሳቃሽ ምስለ መቅረፅ ባያችሁት መልኩ ስላሳየሁት አላስፈላጊ ህብረትና ቅር መሰኘታ...
17/09/2025

ሰላምና ፀጋ ለተወደዳችሁ ቅዱሳን ቤተሰቦቼ ይሁን እያልሁ በሰሞኑ በተለያዩ የማህበራዊ ድህረገፆች በምስልና ተንቀሳቃሽ ምስለ መቅረፅ ባያችሁት መልኩ ስላሳየሁት አላስፈላጊ ህብረትና ቅር መሰኘታችሁ በጣም ከልቤ ይቅርታ እየጠየቅሁ በእለቱ ለሆነ ትልቅ ዝግጅት ጉዳይ እንደ ኮሚቴ በመገኘት በተስፋ ደረጃ ስለተሰጠን ቃልና ሊያሳዩን ስለሞከሩት አብሮነት ደስ ብሎን በቅድሚያም ከካውንስሉ ጋር የነበረው መቃረንና እገዳ በመታረም ተስተካክሎ የፈቃዳቸውን መመለስ አይተንና አረጋግጠን ነበር የተገኘነው::ቢሆንም ግን የቱም በጎ ምክኒያት ይሄን ያህል ርቀት ሊወስደኝ እንደማይገባ በማወቅና በመረዳት በእለቱና በስፍራውም ስለነበርንበት ጉዳይ ቶሎ ቃላቸውን ለመፈፀም ይረዳል ብዬ በማሰብ ስላደረኩት የንግግር መቦካትና መጋገር ጭምር በፍቅርና በቅንነት ለምን እንዴት ላላችሁኝ ሁሉ በውስጥ መስመር ሳስረዳ ብቆይም ዛሬ ደግሞ እንዲህ ባደባባይ ይቅርታ ልጠይቃችሁ እወድዳለሁ በቃ ጥፋትና ስህተት ብቻ እንደሆነ ነው ማሳወቅ የምፈልገው::በተረፈ ግን ይህ ይቅርታዬ ከፍቅር በቀር እዳ ለሌለባችሁ ቅን ወዳጅ ቤተሰቦቼ እንጂ እድሜ ዘመናችሁን ሁሉ ስድብ ቅናት እብሪት ተንኮል ክፋት ሃሜት ክስ አድመኝነት ጠማምነት ወ.ዘ.ተ ብቻ ለተሞላችሁት አይደለምና በምናችሁም ፈፅሞም ቅር ተሰኝቼባችሁ እንደማላውቅ በዚሁ እወቁልኝ:: 'የልብ ደስታ የስንቱን ፊት ሲያበራ' በተሞላችሁት መርዝ ምክኒያት የገጣችሁ ከተቀቀለ ጎመን ወደ መክሰል ፈጣን ጉዞው ሁሌም ያሳዝነኛል እንጂ አላዝንባችሁም ያላችሁንም ለሚቀበላችሁ መስጠት መብታችሁ ስለሆነ የመላከፍና መናቸፍ እንጀራችሁን ሳላነኩርባችሁ ነው ከቤ/ክና ከመሪዎች ቀርቶ በቤ/ክ ጥበቃ ከሚያገለግሉን እኩል በስራ ሃላፊነት ስለማላያችሁ በጊዜ ከእናንተ ጋር የነበረኝን መጋጠም የለየሁት::አሉቧልታችሁ ቅንነቴን አስጥሎ እሳቴን ሊወስድብኝ የነበረ ምንም የማትፈይዱ ውራ ግለሰብ ብቻ ስለሆናችሁ ነው እናንተን ከእቁብ ቆጥሬ ከተወደድችው የክርስቶስ ሙሽራና የቤ/ክ መሪዎች እኩል ሚዛን ላይ ለማስቀመጥ ሳልደፍር ከንፁህ መንፈስ የወንጌሉን ቃል በሃይልና በስልጣን ከሚሰብኩት ፍሬያሞች ከተቀቡት ከከበሩት ብዙዎችንም ከእሳት ከሚናጠቁ የመንግስቱ ስራ ከበዛላቸው ከሚፀልዩት ከሚተነብዩት አጋንንት ከሚያስወጡት ለፈውስና ለመፍትሄ ከተጠሩት ሁሌም ተቀጣጥለው ከሚያቀጣጥሉኝ...ጋር ለመሆን የመረጥኩት ጌታም በኪነጥበቡ ከእጃችሁ ስላስጣለኝና በህይወት ስላለሁ ሁልጊዜ ነው ስለትድግናው የማመሰግነው::በቀረው ከማናችሁም የማንስ በምህረቱና በፀጋው እንጂ በማንነቴ የማልጠቅም የነበርሁ ወንድማችሁ ነኝና ሁሌም ዋጋ ሰጥታችሁ በፍቅር የምትመክሩኝ ሁሉ ከልቤ አመሰግናችኃለሁ ሁሌም እታረማለሁ ቶሎም እቀናለሁ እወዳችኃለሁ::ስለያዝነው ትልቅ ጉዳይ እና በጥንዶቹ ደግሞ ስለገጠመን ያልጠበቅነው ክስተት ዙሪያ ትክክሉን መረጃ በቅርቡ የማደርሳችሁ ይሆናል ሁላችሁም በያላችሁበት ተባረኩልኝ::

Address

Bishoftu
Debre Zeyit

Telephone

+251982420121

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Christian Press posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share