26/02/2026
# በቢሾፍቱ ቁጥር ሁለት
ሙሉ ወንጌል አጥቢያ ቤ/ክ
👉 የእሁድ ቋሚ ፕሮግራሞቻችን ዘውትር እሁድ
- ጠዋት ከ 12:30 - 3:00 የማለዳ ፀሎት
- ከ3 : 00 - 3 :50 የማለዳ ትምህርት
-ከ 3:50 - 6:ዐዐ በዝማሬ የአምልኮና የእግዚአብሔር ቃል ግዜ በመቀጠል
- ከሰዓት በኋላ ከ 9:00 - 10:00 የወጣቶች አገልግሎት፣
👉 # በ ቢሾፍቱ ቁጥር ሁለት አጥቢያ ሙሉ ወንጌል ቤ/ክ በየሣምንቱ ዓርብ ቀን ላይ በሁለት ፈረቃ በ ቤተ ክርስትያን መንፈሳዊ አገልግሎቶች አሉን፣
1ኛ ✍ የጠዋቱ ክፍለ ግዜ ከ ማለዳ 3:00 - 7:00
የፀሎት፣የአምልኮ፣ የእግዚአብሔር ቃል ግዜ፣ እንዲሁም የፈውስ፣ የነፃ መውጣትና የኃይል አገልግሎት ፣ በመጨረሻም ከአርብ የፀሎት ግዜው ጋር ተያይዞ አማኞች ጌታ በህይወታቸው ያደረገላቸውን የሚመሰክሩበትና ሌሎችም የሚፅናኑበት ክፍለ ግዜ ይኖረናል፣
2ኛ ✍ የማታው ክፍለ ግዜ ላይ ከ 11:00 - 1:30 የመንፈስ ቅዱስ የፀጋ ስጦታ እንቅስቃሴ ላይ በማተኮር የፀሎት፣የአምልኮና የእግዚአብሔር ቃል ግዜ ፣ እንዲሁም በተለያዩ መንፈሳዊ ይዘት ባላቸው ህይወት ለዋጭ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ በትምህርት አማኞችን ለማስታጠቅ ቤተ ክርስትያን ትኩረት ሰጥታ እየሰራች ትገኛለች።
✍ ስለሆነም ሁሉም የቤተ ክርስትያን አማኞች እና በዚህ አገልግሎት መጠቀም የሚፈልግ ሁሉም ሰው በሚመቸው ግዜ ተገኝቶ መገልገል የሚችል መሆኑን ቤተ ክርስትያን ታሳስባለች።
“ኢየሱስ ክርስቶስ ትናንትና ዛሬ እስከ ለዘላለምም ያው ነው።”
— ዕብራውያን 13፥8
#👉 #🙏በጨመረ መንፈስ እንቀጥላለን።