Debre Zeit Full Gospel Believers Church-Air Force Area Chappel

Debre Zeit Full Gospel Believers Church-Air Force Area Chappel ይህ የቢሾፍቱ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተ ክርስቲያን - ቁጥር 2 አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ኦፊሺላዊ የፌስቡክ ገፅ ነው፡፡

 # በቢሾፍቱ ቁጥር ሁለት ሙሉ ወንጌል አጥቢያ ቤ/ክ 👉 የእሁድ ቋሚ ፕሮግራሞቻችን ዘውትር እሁድ - ጠዋት ከ 12:30 - 3:00 የማለዳ ፀሎት - ከ3 : 00 - 3 :50 የማለዳ ትምህርት...
26/02/2026

# በቢሾፍቱ ቁጥር ሁለት
ሙሉ ወንጌል አጥቢያ ቤ/ክ
👉 የእሁድ ቋሚ ፕሮግራሞቻችን ዘውትር እሁድ
- ጠዋት ከ 12:30 - 3:00 የማለዳ ፀሎት
- ከ3 : 00 - 3 :50 የማለዳ ትምህርት
-ከ 3:50 - 6:ዐዐ በዝማሬ የአምልኮና የእግዚአብሔር ቃል ግዜ በመቀጠል
- ከሰዓት በኋላ ከ 9:00 - 10:00 የወጣቶች አገልግሎት፣

👉 # በ ቢሾፍቱ ቁጥር ሁለት አጥቢያ ሙሉ ወንጌል ቤ/ክ በየሣምንቱ ዓርብ ቀን ላይ በሁለት ፈረቃ በ ቤተ ክርስትያን መንፈሳዊ አገልግሎቶች አሉን፣
1ኛ ✍ የጠዋቱ ክፍለ ግዜ ከ ማለዳ 3:00 - 7:00
የፀሎት፣የአምልኮ፣ የእግዚአብሔር ቃል ግዜ፣ እንዲሁም የፈውስ፣ የነፃ መውጣትና የኃይል አገልግሎት ፣ በመጨረሻም ከአርብ የፀሎት ግዜው ጋር ተያይዞ አማኞች ጌታ በህይወታቸው ያደረገላቸውን የሚመሰክሩበትና ሌሎችም የሚፅናኑበት ክፍለ ግዜ ይኖረናል፣

2ኛ ✍ የማታው ክፍለ ግዜ ላይ ከ 11:00 - 1:30 የመንፈስ ቅዱስ የፀጋ ስጦታ እንቅስቃሴ ላይ በማተኮር የፀሎት፣የአምልኮና የእግዚአብሔር ቃል ግዜ ፣ እንዲሁም በተለያዩ መንፈሳዊ ይዘት ባላቸው ህይወት ለዋጭ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ በትምህርት አማኞችን ለማስታጠቅ ቤተ ክርስትያን ትኩረት ሰጥታ እየሰራች ትገኛለች።
✍ ስለሆነም ሁሉም የቤተ ክርስትያን አማኞች እና በዚህ አገልግሎት መጠቀም የሚፈልግ ሁሉም ሰው በሚመቸው ግዜ ተገኝቶ መገልገል የሚችል መሆኑን ቤተ ክርስትያን ታሳስባለች።

“ኢየሱስ ክርስቶስ ትናንትና ዛሬ እስከ ለዘላለምም ያው ነው።”
— ዕብራውያን 13፥8
#👉 #🙏በጨመረ መንፈስ እንቀጥላለን።

ቅዳሜ ታሕሣስ 25,2018 ዓ.ም በቢሾፍቱ(ደ/ዘ) አብያተ ክርስትያናት ሕብረት የተዘጋጀ በአይነቱ ለየት ያለ " ለወንጌል እሮጣለሁ !" በሚል መሪ ቃል የእሩጫ ፕሮግራም የነበረን ሲሆን አላማ...
04/01/2026

ቅዳሜ ታሕሣስ 25,2018 ዓ.ም በቢሾፍቱ(ደ/ዘ) አብያተ ክርስትያናት ሕብረት የተዘጋጀ በአይነቱ ለየት ያለ " ለወንጌል እሮጣለሁ !" በሚል መሪ ቃል የእሩጫ ፕሮግራም የነበረን ሲሆን አላማውን ከማሳካት ጎን ለጎን የአማኞች ሕብረትና አንድነት የታየበት ልዩ ግዜ ሆኖ ተጠናቋል፣
በዕለቱም ተሳታፊ ከነበሩ ወንድሞችና እህቶች ጋር አብረን የጋራ ግዜን አሳልፈናል ።

“አስቀድሞም ወንጌል ለአሕዛብ ሁሉ ይሰበክ ዘንድ ይገባል።”
— ማርቆስ 13፥10

“ስለዚህ ሕዝቡን በብዙ ሌላ ምክር እየመከራቸው ወንጌልን ይሰብክላቸው ነበር፤”
— ሉቃስ 3፥18

✍ ለአለፉት አራት አመት  በቢሾፍቱ ቁጥር ሁለት አጥቢያ ቤተ ክርስትያን የ4ኛው ዙር  ለተከታታይ 12 ሣምንታት ቅዳሜ ቀን ሲሰጥ የነበረው የአገልጋዮች ትምህርትና ስልጠና በተሳካ ሁኔታ ቅዳሜ...
30/12/2025

✍ ለአለፉት አራት አመት በቢሾፍቱ ቁጥር ሁለት አጥቢያ ቤተ ክርስትያን የ4ኛው ዙር ለተከታታይ 12 ሣምንታት ቅዳሜ ቀን ሲሰጥ የነበረው የአገልጋዮች ትምህርትና ስልጠና በተሳካ ሁኔታ ቅዳሜ ታሕሳስ 18,2018 ዓ.ም ተጠናቋል ፣

በመጨረሻም ከዚህ ስልጠና በኋላ የአጥቢያችን አገልጋዮች ከቤተ-ክርስትያን ራዕይ አንፃር የትኩረት አቅጣጫዎቻችን ላይ መሠረት በማድረግ ለአንድ ዓላማ በአንድ ልብ አንድ አይነት መልክ ይዘን የተሰጠንን ተልእኮ ለመወጣት በአንድ መንፈስ የተነሳንበትና ለራሳችን ቃል የገባንበት ነበር፣
ተሃድሶ ሆኖልናል !!

🎤 2ኛ ጢሞቴዎስ 3
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁴ አንተ ግን በተማርህበትና በተረዳህበት ነገር ጸንተህ ኑር፥ ከማን እንደ ተማርኸው ታውቃለህና፤
¹⁵ ከሕፃንነትህም ጀምረህ ክርስቶስ ኢየሱስን በማመን፥ መዳን የሚገኝበትን ጥበብ ሊሰጡህ የሚችሉትን ቅዱሳን መጻሕፍትን አውቀሃል።
¹⁶-¹⁷ የእግዚአብሔር ሰው ፍጹምና ለበጎ ሥራ ሁሉ የተዘጋጀ ይሆን ዘንድ፥ የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ሁሉ ለትምህርትና ለተግሣጽ ልብንም ለማቅናት በጽድቅም ላለው ምክር ደግሞ ይጠቅማል።

Address

Debre Zeyit
995

Telephone

+2510118480493

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Debre Zeit Full Gospel Believers Church-Air Force Area Chappel posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share