Debre Zeit Meserete Kristos Church

Debre Zeit Meserete Kristos Church “ከተመሠረተው በቀር ማንም ሌላ መሠረት ሊመሠርት አይችልምና፥ እርሱም ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 3፥11

በደብረዘይት መሀል መሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን የእሮብ የአምልኮና የፈውስ ጊዜ
23/05/2026

በደብረዘይት መሀል መሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን የእሮብ የአምልኮና የፈውስ ጊዜ

ዛሬ ማታ 11:00 በደብረዘይት መሀል መሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ከአብያተ ክርስቲያናት ጋር በመተባበር የተዘጋጀ የ 13ኛ አመት የምስጋናና የአምልኮ ምሽት
21/05/2026

ዛሬ ማታ 11:00 በደብረዘይት መሀል መሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ከአብያተ ክርስቲያናት ጋር በመተባበር የተዘጋጀ የ 13ኛ አመት የምስጋናና የአምልኮ ምሽት

‎በደብረዘይት መሀል መሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን የእሁድ ማለዳ የአዋቂዎች ትመሕርትና የእሁድ ጠዋት የአምልኮና የቃል ጊዜ‎የእለቱ መልዕክት ርዕስ:- እግዚአብሔር አለ።‎‎ዕምባቆም 2:3 ራ...
21/05/2026

‎በደብረዘይት መሀል መሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን የእሁድ ማለዳ የአዋቂዎች ትመሕርትና የእሁድ ጠዋት የአምልኮና የቃል ጊዜ
‎የእለቱ መልዕክት ርዕስ:- እግዚአብሔር አለ።

‎ዕምባቆም 2:3 ራእዩ ገና እስከ ተወሰነው ጊዜ ነው፥ ወደ ፍጻሜውም ይቸኵላል፥ እርሱም አይዋሽም፤ ቢዘገይም በእርግጥ ይመጣልና ታገሠው፤ እርሱ አይዘገይም።


‎20 እግዚአብሔር ግን በተቀደሰ መቅደሱ አለ፤ ምድርም ሁሉ በፊቱ ዝም ትበል።



‎09/09/18

በደብረዘይት መሀል መሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን የአምልኮና የፈውስ ፕሮግራምበቃል ዶ/ር ሰለሞን ኢየሱስ ሁሉን ይጠቀልላልዕብ 1:10-12ሀሉ ነገር በምድር የተደረገው እያንዳንዱ ነገር ፍፃሜ...
18/05/2026

በደብረዘይት መሀል መሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን የአምልኮና የፈውስ ፕሮግራም
በቃል ዶ/ር ሰለሞን
ኢየሱስ ሁሉን ይጠቀልላል
ዕብ 1:10-12
ሀሉ ነገር በምድር የተደረገው እያንዳንዱ ነገር ፍፃሜ አለው ፍፃሜ የሌለው ኢየሱስ ብቻ ነው።
እርሱ የሁሉ መጀመሪያ ነው ለእርሱ ግን ጅማሬ የለውም
ሰማይ ምድሩ ገደብ አለው ገደብ የሌለው የናዝሬቱ ኢየሱስ ብቻ ነው። አሜን
ለጨለማ ስረዓት ገደብ አለው
ለርኩሰቱ ገደብ አለው
ገደብ የሌለው አልፋና ኦሜጋ፣ ፊተኛና ኋለኛ መጀመሪያና መጨረሻ የናዝሬቱ ኢየሱስ ብቻ ነው። አሜን

ለአለም መንግስታት ገደብ አላቸው።
ኢየሱስ ይመጣል
በዓለም ላይ የእግዚአብሔር እጅ ይመጣል
ዳንኤል 5
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሁሉን ይጠቀልላል
ያላመኑት በቁጣ ሲጠቀለሉ
ከእርሱ ጋር ያሉ የተጠሩ የተመረጡ በእምነት የኖሩ ከእርሱ ጋር ድል ይነሳሉ በክብር ይጠቀለላሉ
በታላቅ ደህንነት ዘመናቸውን ይጠቀለላል
ከእርሱ ጋር ተጣበቅ እርሱን አምልክ በክብር ትጠቀለላለህ
ሂወታችሁ የሆነ ክርስቶስ በሚገለጥበት ጊዜ በዚያን ጊዜ ከእርሱ ጋር አብራችሁ ትገለጣላችሁ።
እባካችሁ እንቁአችሁን በእሪያዎች ፊት አትጣሉ።
ኢየሱስ ከሙታን በመነሳቱ እያው ለሆነ፣ እድፈት ለሌለበት ለማይጠፋና ለማያልፍ ርስት ወልዶናል ስለዚህ ከእርሱ ጋር መጣበቅ ይሁንልን
ወደቀኝም ወደግራም አትመልከቱ
በክብር፣ በሕይወት፣ በደስታ እንጠቀለላለን
አገልግሎታችሁን ፈፅሙ በደስታ ትጠቀለላላችሁ
ቁሙ ልባችሁ ይፅና ሽልማት አላችሁ
ሁሉ ፍፃሜ አለው ሁሉ ይጠቀለላል ፍፃሜ የሌለው፣ የማይጠቀለል እርሱ ብቻ ነው። ይሄ ጌታ ይመጣል

“ጌታ ሆይ፥ አንተ ከጥንት ምድርን መሠረትህ፥ ሰማዮችም የእጆችህ ሥራ ናቸው፤
11: እነርሱም ይጠፋሉ አንተ ግን ጸንተህ ትኖራለህ፤ ሁሉም እንደ ልብስ ያረጃሉ፥
12: እንደ መጎናጸፊያም ትጠቀልላቸዋለህ ይለወጡማል፤ አንተ ግን አንተ ነህ፥ ዓመቶችህም ከቶ አያልቁም፥”
ይላል።

በቆፍቱ መሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን የእናት ቤተ ክርስቲያን የጉብኝት የምስጋናና የአንድነት ጊዜ02/09/18
16/05/2026

በቆፍቱ መሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን የእናት ቤተ ክርስቲያን የጉብኝት የምስጋናና የአንድነት ጊዜ

02/09/18

በደብረዘይት መሀል መሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ከአብያተ ክርስቲያን ጋር በመተባበር የሚዘጋጅ የመፅሐፉ ሰዎች የተሰኘ የመፅሐፍ ቅዱስ ጥናት የሀሙስ ምሽት ፕሮግራም
13/05/2026

በደብረዘይት መሀል መሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ከአብያተ ክርስቲያን ጋር በመተባበር የሚዘጋጅ የመፅሐፉ ሰዎች የተሰኘ የመፅሐፍ ቅዱስ ጥናት የሀሙስ ምሽት ፕሮግራም

በደብረዘይት መሀል መሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን የእሮብ የአምልኮ የፀሎትና የፈውስ ፕሮግራም28/08/18ብድራት ያለው ህይወት ²ነገ 4:8_44²ነገ 8:1_68 አንድ ቀንም እንዲህ ሆነ፤ ኤ...
12/05/2026

በደብረዘይት መሀል መሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን የእሮብ የአምልኮ የፀሎትና የፈውስ ፕሮግራም28/08/18

ብድራት ያለው ህይወት
²ነገ 4:8_44
²ነገ 8:1_6

8 አንድ ቀንም እንዲህ ሆነ፤ ኤልሳዕ ወደ ሱነም አለፈ፥ በዚያም ታላቅ ሴት ነበረች፤ እንጀራ ይበላ ዘንድ የግድ አለችው፤ በዚያም ባለፈ ቍጥር እንጀራ ሊበላ ወደዚያ ይገባ ነበር።
9 ለባልዋም፡— ይህ በእኛ ዘንድ ሁልጊዜ የሚያልፈው ቅዱስ የእግዚአብሔር ሰው እንደ ሆነ አውቃለሁ።
10 ትንሽ ቤት በሰገነቱ ላይ እንሥራ፤ በዚያም አልጋ ጠረጴዛ ወንበርና መቅረዝ እናኑርለት፤ ወደ እኛም ሲመጣ ወደዚያ ይገባል አለችው።
11 አንድ ቀንም ወደዚያ በመጣ ጊዜ ወደ ቤቱ ገብቶ በዚያ ዐረፈ።
12 ሎሌውንም ግያዝን፡— ይህችን ሱነማዊት ጥራ፡ አለው።
13 በጠራትም ጊዜ በፊቱ ቆመች። እርሱም፡— እነሆ፥ ይህን ሁሉ አሳብ አሰብሽልኝ፤ አሁንስ ምን ላድርግልሽ? ለንጉሥ ወይስ ለሠራዊት አለቃ ልንገርልሽን? በላት አለው፤ እርስዋም፡— እኔ በወገኔ መካከል ተቀምጫለሁ ብላ መለሰች።
14 እርሱም፡— እንግዲህ ምን እናድርግላት? አለ። ግያዝም፡— ልጅ የላትም፤ ባልዋም ሸምግሎአል ብሎ መለሰ።
15 እርሱም፡— ጥራት፡ አለ። በጠራትም ጊዜ በደጃፉ ቆመች።
16 እርሱም፡— በሚመጣው ዓመት በዚህ ወራት ወንድ ልጅ ትታቀፊአለሽ አለ፤ እርስዋም፡— አይደለም ጌታዬ፥ የእግዚአብሔር ሰው ሆይ፥ ባሪያህን እንዳትዋሻት እለምንሃለሁ አለች።
17 ሴቲቱም ፀነሰች፥ በዚያም ወራት በአዲሱ ዓመት ኤልሳዕ እንዳላት ወንድ ልጅ ወለደች።
18 ሕፃኑም አደገ፥ አንድ ቀንም እህል አጫጆች ወዳሉበት ወደ አባቱ ወጣ።
19 አባቱንም፡— ራሴን ራሴን አለው፤ እርሱም ሎሌውን፡— ተሸክመህ ወደ እናቱ ውሰደው፡ አለው።
20 አንሥቶም ወደ እናቱ ወሰደው፤ በጕልበትዋም ላይ እስከ ቀትር ድረስ ተቀመጠ፥ ሞተም።
21 ወጥታም በእግዚአብሔር ሰው አልጋ ላይ አጋደመችው፥ በሩንም ዘግታበት ወጣች።
22 ባልዋንም ጠርታ፡— ወደ እግዚአብሔር ሰው በፍጥነት ደርሼ እመለስ ዘንድ አንድ ሎሌና አንድ አህያ ላክልኝ አለችው።
23 እርሱም፡— መባቻ ወይም ሰንበት ያይደለ ዛሬ ለምን ትሄጂበታለሽ? አለ። እርስዋም፡— ደኅና ነው አለች።
24 አህያውንም አስጭና ሎሌዋን፡— ንዳ፥ ሂድ፤ እኔ ሳላዝዝህ አታዘግየኝ አለችው።
25 እንዲሁም ሄደች፥ ወደ እግዚአብሔርም ሰው ወደ ቀርሜሎስ ተራራ መጣች። የእግዚአብሔርም ሰው ከሩቅ ባያት ጊዜ ሎሌውን ግያዝን፥ እነኋት ሱነማዊቲቱ መጣች፤
26 ትቀበላትም ዘንድ ሩጥና፡— በደኅናሽ ነውን? ባልሽ ደኅና ነውን? ልጅሽስ ደኅና ነውን? በላት፡ አለው። እርስዋም፡— ደኅና ነው አለች።
27 ወደ ተራራው ወደ እግዚአብሔር ሰው በመጣች ጊዜ እግሮቹን ጨበጠች፤ ግያዝም ሊያርቃት ቀረበ፤ የእግዚአብሔርም ሰው፡— ነፍስዋ አዝናለችና ተዋት፤ እግዚአብሔርም ያንን ከእኔ ሰውሮታል አልነገረኝምም፡ አለ።
28 እርስዋም፡— በውኑ ከጌታዬ ልጅን ለመንሁን? እኔም አታታልለኝ አላልሁህምን? አለች።
29 ግያዝንም፡— ወገብህን ታጠቅ፥ በትሬንም በእጅህ ይዘህ ሂድ፤ ሰውም ብታገኝ ሰላም አትበል፥ እርሱም ሰላም ቢልህ አትመልስለት፤ በትሬንም በሕፃኑ ፊት ላይ አኑር፡ አለው።
30 የሕፃኑም እናት፡— ሕያው እግዚአብሔርን! በሕያው ነፍስህም እምላለሁ! አልተውህም አለች፤ ተነሥቶም ተከተላት።
31 ግያዝም ቀደማቸው፥ በትሩንም በሕፃኑ ፊት ላይ አኖረው፤ ነገር ግን ድምፅ ወይም መስማት አልነበረም፤ እርሱንም ሊገናኘው ተመልሶ። ሕፃኑ አልነቃም ብሎ ነገረው።
32 ኤልሳዕም ወደ ቤት በገባ ጊዜ እነሆ፥ ሕፃኑ ሞቶ በአልጋው ላይ ተጋድሞ ነበር።
33 ገብቶም በሩን ከሁለቱ በኋላ ዘጋ፥ ወደ እግዚአብሔርም ጸለየ።
34 መጥቶም በሕፃኑ ላይ ተኛ፤ አፉንም በአፉ፥ ዓይኑንም በዓይኑ፥ እጁንም በእጁ ላይ አድርጎ ተጋደመበት፤ የሕፃኑም ገላ ሞቀ።
35 ተመልሶም በቤቱ ውስጥ አንድ ጊዜ ወዲህና ወዲያ ተመላለሰ፤ ደግሞም ወጥቶ ሰባት ጊዜ በሕፃኑ ላይ ተጋደመ፤ ሕፃኑም ዓይኖቹን ከፈተ።
36 ግያዝንም ጠርቶ፡— ይህችን ሱነማዊት ጥራ፡ አለው። ጠራትም፥ ወደ እርሱም በገባች ጊዜ፡— ልጅሽን አንሥተሽ ውሰጂ፡ አላት።
37 ገብታም በእግሩ አጠገብ ወደቀች በምድርም ላይ ተደፋች፤ ልጅዋንም አንሥታ ወጣች።
38 ኤልሳዕም ዳግመኛ ወደ ጌልገላ መጣ፥ በምድርም ላይ ራብ ነበረ፤ የነቢያትም ልጆች በፊቱ ተቀምጠው ነበር፥ ሎሌውንም፡— ታላቁን ምንቸት ጣድ፥ ለነቢያት ልጆችም ወጥ ሥራ፡ አለው።
39 አንዱም ቅጠላቅጠል ያመጣ ዘንድ ወደ ሜዳ ወጣ፥ የምድረበዳውንም ሐረግ አገኘ ከዚያም የበረሀ ቅል ሰበሰበ፥ ልብሱንም ሞልቶ ተመለሰ፥ መትሮም በወጡ ምንቸት ውስጥ ጨመረው፤ ምን እንደ ሆነ ግን አላወቁም።
40 ሰዎቹም ይበሉ ዘንድ ቀዱ፤ ወጡንም በቀመሱ ጊዜ፡— የእግዚአብሔር ሰው ሆይ፥ በምንቸቱ ውስጥ ሞት አለ፡ ብለው ጮኹ፤ ይበሉም ዘንድ አልቻሉም።
41 እርሱም፡— ዱቄት አምጡልኝ አለ፤ በምንቸቱም ውስጥ ጥሎ፡— ይበሉ ዘንድ ለሕዝቡ ቅዱ፡ አለ። በምንቸቱም ውስጥ ክፉ ነገር አልተገኘም።
42 አንድ ሰውም ከበኣልሻሊሻ የበኵራቱን እንጀራ፥ ሀያ የገብስ እንጀራ፥ የእህልም እሸት በአቁማዳ ይዞ ወደ እግዚአብሔር ሰው መጣ፤ እርሱም፡— ይበሉ ዘንድ ለሕዝቡ ስጣቸው፡ አለ።
43 ሎሌውም፡— ይህን እንዴት አድርጌ ለመቶ ሰው እሰጣለሁ? አለ። እርሱም፡— ይበላሉ ያተርፋሉም ብሎ እግዚአብሔር ተናግሮአልና ይበሉ ዘንድ ለሕዝቡ ስጣቸው፡ አለ።
44 እንዲሁም በፊታቸው አኖረው፥ እንደ እግዚአብሔርም ቃል በሉ፥ አተረፉም።

በደብረዘይት መሀል መሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን የእሁድ ማለዳ የአዋቂዎች ትመሕርትና የእሁድ ጠዋት የአምልኮና የቃል ጊዜ25/08/2018ፀሎት:- መ/ር በላይ አየለአምልኮ:-ወ/ም ኤልያስቃል...
05/05/2026

በደብረዘይት መሀል መሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን የእሁድ ማለዳ የአዋቂዎች ትመሕርትና የእሁድ ጠዋት የአምልኮና የቃል ጊዜ

25/08/2018
ፀሎት:- መ/ር በላይ አየለ
አምልኮ:-ወ/ም ኤልያስ
ቃል:- ወ/ም ተመስገን
ሉቃ 2:22-32
ርዕስ:- እውነተኛ ካህን/ደቀመዝሙር ማነው?
ሉቃስ ይህንን መልዕክት በጥንቃቄና ማስረጃ ቴዎፍሎስ ለተባለ ሰው እንደፃፈ ይገልፃል።
በዚህ ክፍል ሉቃስ ስምዖን ስለተባለ ኃያል ሰው ይናገራል። ከዚህ በመነሳት 5 የስምዖንን ባህሪዎች እናያለን
1. ፃድቅ ነበረ/በእግዚአብሔር ይታመናል
እግዚአብሔር ላይ የሚታመን በሁኔታዎች በእግዚአብሔር ላይ ያለው ነገር የማይለዋወጥ።
እዮብ ፃድቅ ነበረ በሂወቱ በላፈው ወጀብና ማዕበል ሁሉ በእግዚአብሔር ላይ የነበረው እምነት የፀና ነበር።
2. ትጉ ነበር
እግዚአብሔር ለሰጠን ለጠራን ለሾመን
ትጋት ለአንድ ስራ በሙሉ ኃይል በሙሉ ልብ በጥንቃቄ የተሰጠንን አደራ መወጣት ነው።
ምሳሌ የሰው የከበረ ሀብቱ ትጋቱ ነው ይላል። ሐዋሪያት በጸሎትና በቃል ይተጉ ነበር
እግዚአብሔር በሰጠን ፀጋ ልንተጋ ይገባል።
3. የእግዚአብሔር መንፈስ በሱ ላይ ያለ
የመንፈስ ፍሬ በሂወቱ የተገለጠ
4. በመንፈስ ቅዱስ ይመራ ነበር
ስምዖን በመንፈስ ይመራ ስለነበር ጌታ ኢየሱስን ተገናኘው፣ አቀፈው።
ዛሬ እኛን ማን ይሆን እየመራን ያለው ሮሜ 8:14 በእግዚአብሔር መንፈስ የሚመሩ እነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ናቸው። ማነው የሚመራን ልጆች ከሆንን መንፈሱ ሊመራን ይገባል
ገላ 5:18 በመንፈስ ስንመራ ከሕግ በላይ እንሆናለን
በአዲስ ኪዳን እንዲመራን የተሰጠን መንፈስ ቅዱስ ነው።
5. ከእግዚአብሔር ቃል ጋር ያለን ቁርኝት
እግዚአብሔር ዛሬ ኪዳናችንን ያድስ
እግዚአብሔር ለጸሎታችን ምላሽ ያልሰጠው ለምንድነው እንደቃሉ ስለማንፀልይ? የእ
ቆላ 3:16 ምንድነው በእኛ ሕይወት የሞላው? እኛ ግን እንድንሞላ የተሰጠን ቃሉ ነው።

በደብረዘይት መሀል መሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን የእሮብ ሙሉ ቀን የአምልኮ የፀሎት የአርነትና የቃል ጊዜ                  21/08/18የእለቱ መልእክት ርዕስ:- ከልካዩ ዞር ይላ...
03/05/2026

በደብረዘይት መሀል መሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን የእሮብ ሙሉ ቀን የአምልኮ የፀሎት የአርነትና የቃል ጊዜ
21/08/18

የእለቱ መልእክት ርዕስ:- ከልካዩ ዞር ይላል

ሮሜ1:8-13 እምነታችሁ በዓለም ሁሉ ስለ ተሰማች አስቀድሜ ስለ ሁላችሁ አምላኬን በኢየሱስ ክርስቶስ አመሰግናለሁ።
9-10 በልጁ ወንጌል በመንፈሴ የማገለግለው እግዚአብሔር ምስክሬ ነውና፤ ምናልባት ብዙ ቆይቼ ወደ እናንተ አሁን እንድመጣ በእግዚአብሔር ፈቃድ መንገዴን እንዲያቀናልኝ እየለመንሁ ሁልጊዜ ስጸልይ ስለ እናንተ ሳላቋርጥ አሳስባለሁ።
11 ትጸኑ ዘንድ መንፈሳዊ ስጦታ እንዳካፍላችሁ ላያችሁ እናፍቃለሁና፤
12 ይህንም ማለቴ በመካከላችን ባለች በእናንተና በእኔ እምነት አብረን በእናንተ እንድንጽናና ነው።
13 ወንድሞች ሆይ፥ በሌሎቹ አሕዛብ ደግሞ እንደ ሆነ በእናንተም ፍሬ አገኝ ዘንድ ብዙ ጊዜ ወደ እናንተ ልመጣ እንዳሰብሁ እስከ አሁን ግን እንደ ተከለከልሁ ታውቁ ዘንድ እወዳለሁ።

በደብረዘይት መሀል መሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን የእሁድ ማለዳ የአዋቂዎች ትመሕርትና የእሁድ ጠዋት የአምልኮና የቃል ጊዜ 18/08/18በ እግዚያብሔር ምህረት መኖር መዝሙር 63:3 ምሕረትህ...
28/04/2026

በደብረዘይት መሀል መሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን የእሁድ ማለዳ የአዋቂዎች ትመሕርትና የእሁድ ጠዋት የአምልኮና የቃል ጊዜ 18/08/18

በ እግዚያብሔር ምህረት መኖር

መዝሙር 63:3 ምሕረትህ ከሕይወት ይሻላልና፡ ከንፈሮቼ ያመሰግኑሃል።

እግዚያብሔር ምህረት ያደረገለት ሰው ለሌላው ምህረት የሚያደርግ ነው።

ምህረትን ለማያደርግ እግዚያብሔር ምህረት አያደርግለትም::

ያዕቆብ 2:13
ምሕረትን አለማያደርግ ምሕረት የሌለበት ፍርድ ይሆናልና፤ ምሕረትም በፍርድ ላይ ይመካል።

በደብረዘይት መሀል መሠረተ ክርሰቶስ ቤተክርስቲያን ከአብያተ ክርስቲያናት ጋ በመተባበር የተዘጋጀ የመፅሐፍ ቅዱስ ጥናት የሐሙስ ምሽት ፕሮግራም ²ኛ ቆሮንቶስ
27/04/2026

በደብረዘይት መሀል መሠረተ ክርሰቶስ ቤተክርስቲያን ከአብያተ ክርስቲያናት ጋ በመተባበር የተዘጋጀ የመፅሐፍ ቅዱስ ጥናት የሐሙስ ምሽት ፕሮግራም ²ኛ ቆሮንቶስ

Address

Debre Zeyit

Opening Hours

02:00 - 06:00

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Debre Zeit Meserete Kristos Church posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Debre Zeit Meserete Kristos Church:

Share

Category