13/08/2026
የትምህርት መርሃ-ግብር ሀሙስ ማታ 30/11/18
ፀሎት፡- እ/ት ቃልኪዳን ሙሉ
ቃል፡- ወ/ም ሙሉጌታ በልዳ
የቃል ክፍል፦ ዮሃ 5:24-47
Ø በሁለት ልንከፍለው እንችላለን ፣ ከቁጥር 24-30 ያለው ኢየሱስን መከተል ምን ማለት ነው፣ ውጤቶቹን ምን ምን ናቸው? የሚለውን ሲያስዳስሰን ከ 31-47 ያለው ደግሞ ኢየሱስ አምላክ የመሆኑን ምስክርነት ያሳየናል
ክፍል-1 ቁጥር 24-30 ኢየሱስን መከተል ምን ማለት ነው፣ ውጤቶቹን ምን ምን ናቸው ?
Ø እውነት እውነት እላችኋለው (በግሪኩ Amen Amen) ፣ በዮሀንስ ወንጌል ውስጥ 27 ጊዜ ጥቅም ላይ የዋለ ሲሆን ቀጥሎ ለሚነገረው ነገር አጽንዖት ለመስጠት ሲባል የሚገባ ነው
Ø ጌታ ኢየሱስ ቃሌን የሚሰማ የላከኝንም የሚያምን ከሞት ወደ ህይወት ተሻገረ ይላል፣ መዳን ቅጽበታዊ እና የአሁን ነው እንጂ ከሞትን በኋላ የምናውቀው አይደለም
Ø አንዳንዶቻችን መዳን አይሰማንም ስንል እንሰማለን ነገር ግን መዳን የስሜት ሳይሆን የቦታ (Position) ለውጥ ጉዳይ ነው ፣ ለዚህ የኖህ መርከብን እንደ ጥሩ ምሳሌ የሚጠቀሙ አሉ። ኖህ ከጥፋት ውሃ መዳኑን ያወቀው በስሜቱ ሳይሆን በመርከቢቷ ላይ በመሆኑ ነው። የኛም መዳን የተረጋገጠው በኢየሱስ ላይ በመሆናችን ነው።
Ø ቁጥር 25 ላይ ሙታን የሚላቸው በስጋ የሞቱ ሳይሆኑ በመንፈስ ሙታን የሆኑ ናቸው።፣
የእግዚአብሔርን ልጅ ድምጽ ይሰማሉ- ህይወት የሚሰጠውን ጌታ ሰምተው ምላሽ ይሰጣሉ፣ ቅጽበታዊ የሆነ ፣ መንፈሳዊ መዳን ነው (Instant Spiritual Resurrection) ነው።
Ø ቁጥር ቁጥር 25 ኢየሱስን የእግዚአብሔር ልጅ ሲለው ቁጥር 27 ላይ ግን የሰው ልጅ ብሎ ይጠራዋል። ይህ የሆነው፣ በፍርድ ወንበር ላይ የሚቀመጠው ኢየሱስ ሰው የሆነው፣ የሰውነትን ድካም የሚረዳው፣ ከሃጢያት በቀር እንደኛ በሁሉ የተፈተነው እና የሚራራው ኢየሱስ እንደሆነ ለማሳየት ነው።
Ø ቁጥር 29 ላይ በመቃብር ያሉት፥ የሞቱ ሰዎችን በሙሉ፣ ያመነውንም ያላመነውንም የሚያመለክት ነው።
መልካም ያደረጉ፦ ሲል በመልካም ስራ የዘላለም ህይወት ይገኛል ማለት ሳይሆን፣ የልጁን ድምጽ ከመስማት የሆነ ማመን እና ከማመን የሆነ መልካም ስራ ማለት ነው
ክፉ ያደረጉ፥- እንዲሁ ለመጣው ድምጽ ምላሽ ያልሰጡ፣ ከዚህም የተነሳ የኑሮ ዘይቤያቸውን ሓጢያት የተጫነው ፣ በክፉ ስራቸው የቀጠሉ ናቸው።
Ø ቁጥር 30 ፍርዴ ቅን ነው ማለት፡ ሌላ ይግባኝ ሰሚ የማያስፈልገው ትክክለኛ (Genuine) ነው።
ክፍል-2 ቁጥር 31-47 ኢየሱስ አምላክ የመሆኑ ምስክሮች
እኔ ስለ ራሴ ብመሰክር ምስክሬ እውነት አይደለም ማለቱ እንደ ህጋችሁ ማለቱ ነው፣ ሙሴ በዘዳ 17:6 ላይ ምስክር ቢያንስ በሁለት አሊያም በሶስት እንደሚጸና ይደነግጋል።
1. አብ፡ ቁጥር 32 ስለ እኔ የሚመሰክረው ሌላ ነው ሲል ሌላ የሚለው በግሪክ አሎስ (Alos) የሚለው ቃል ጥቅም ላይ የዋለ ሲሆን በአይነት ተመሳሳይ (Another of the same kind) መሆኑን ያሳያል። የእርሱ ምስክርነት ደግሞ እውነት ነው
2. ዮሃንስ፦ በዮሃ 3:18 እንዲሁም 1:29-34 ዮሃንስ ስለ ኢየሱስ መስክሯል። ኢየሱስ እኔ የሰው ምስክርነት አልቀበልም ነበር፣ የአብና የወልድ ምስክርነትም በቂ ነው ብሎ የዮሃንስን ምስክርነት የሚጠራበትን ምክንያት ሲናገር እናንተ እንድትድኑ ነው ይላል።
Ø ዮሃንስን ሲገልጠው ፡ የሚነድ መብራት (Lamp) እንደነበረ ፣ እየነደደ ፣እየተቃጠለ በሓጢያታቸው ላይ መብራቱን (Lamp) (ከእውነተኛው ብርሃን ከኢየሱስ ዮሃ 1:4-5) እየወሰደ ያበራ ነበር።
ጥቂት ዘመን፦ ኢየሱስ ይሄን በሚናገርበት ወቅት በጊዜ ቅደም ተከተል (Chronology) ዮሃንስ በወህኒ ነበር፣ እናም በዚህ ሰው ልትጠቀሙ እና ወደ እውነት እና ብርሃን ወደ ሆነው ጌታ ልትመጡ አልወደዳችሁም
3. ስራው፦ ይህ እኔ የምሰራው ስራ አብ እንደላከኝ የሚናገር ነው።
ስራ የሚለው ምን ነው የሚለው ላይ ሁለት አመለካከቶች አሉ 1. ኢየሱስ ከብሉ ጀምሮ፣ በስጋ በተገለጠበት ወራት እንዲሁም ከትንሳኤው በኋላ የሰራቸውን እና የሚሰራቸውን ነው የሚሉ አሉ ደግሞ በስጋ ምድር ላይ በነበረበት ወቅት የሰሯቸውን ወይኑን ወደ ውሃ መለወጥ፣ 38 አመት ሽባ የነበረውን ሰው መፈወስን የመሳሰሉ ከጌታ ፍቅርና ርህራሄ የመነጩ፣ መረጋገጥ የቻሉ እንዲሁም የሰውን የተፈጥሮ ሃይል ያለፉ ስራዎች ሊሆን ይችላል።
ቁጥር 37 ድምጹን አልሰማችሁም፦ ማር 9:2-7,ዮሃ 12:8, ማቴ3:17 ላይ የአብ ድምጽ ምስክር ሆኗል ለኢየሱስ፣ ግን ሊሰሙት አልወደዱም ነበር መልኩን አላያችሁም፡ አምላክ ስጋ ለብሶ በመካከላችሁ ሲመላለስ አላያችሁም
4. መጽሃፍት፥- ትመረምራላችሁ ሲል በጣም በጥልቀት (Diligently) ህግን ያጠኑ እንደነበር ማሳያ ነው። የአይሁድ ሰዎች ትንቢትን በጣም ይመረምሩ ነበር ፣ሁሉም ሊባል በሚችል ደረጃ በቃላቸው ሳይቀር ይይዙት ነበር። ሄሮድስ በማቴ 2:3-4 ንጉሱ ወዴት እንደሚወለድ ጻፎችን እና የካህናት አለቆችን ሲጠይቅ ወዲያው ነው ሚል 5:2ን ጠቅሰው ከቤተልሄም ይሁዳ እንደሆነ የነገሩት። ስለ ኢየሱስ የተነገሩና በኢየሱስ የተፈጸሙ ወደ 300 የሚጠጉ ትንቢቶች በብሉይ አሉ ፣እነዚህንም ያውቋቸዋል ግን ህይወት እንዲሆንላቸው ወደ ኢየሱስ ሊመጡ አይወዱም።
ይሄ ሁሉ ምስክር ካለ ለምን አይቀበሉትም?
1. ቁጥር 42 እግዚአብሔርን ስለማይወዱት፣ ይህ ደግሞ የህግ ማዕከል ነው
2. በራሱ ስም ሳይሆን በአብ ስም ስለመጣ
3. የእግዚአብሔርን ክብር ሳይሆን የሰውን ክብር ስለምትፈልጉ ነው። በዚህ ጉዳይ የምከሳችሁ እኔ ሳልሆን ተስፋ የምታደርጉት ሙሴ ነው ምክንያቱም ሙሴን ራሱ አላመናችሁትም ብታምኑት ኖሮ ስለ እኔ የጻፈውን ታሙና ትቀበሉ ነበር
ምን እንማር፦
1. ስራችን ማንነታችንን ይመሰክራል። የምትናገረውን እንዳልሰማ የምትሰራውን እያየው ነው እንደሚሉት እንዳይሆን ለስራችን መጠንቀቅ ያስፈልጋል። ያዕ2 ፥18
2. የእግዚአብሔርን ቃል የምናጠናው ወደ ኢየሱስ ለመምጣት ሊሆን ይገባል
3. ክብር የምንቀበለው ከማን ነው፣ ከሰው ወይስ ከእግዚአብሔር?