Zemari Tadele Fetula Abu

Zemari Tadele Fetula Abu Thunks To GOD

የመጽሐፍ ጥቆማ  "ጌታ ሆይ! አንተ ውበትን የምትፈልግ ሳይሆን ውበትን የምትፈጥር ሙሽራ ነህና፤ ወደ እኔም ና። በሲካር ጉድጓድ አጠገብ ለዚያች ሴት እንደተገለጠህላት፣ ዛሬም በልቤ ደጃፍ ተገ...
01/04/2026

የመጽሐፍ ጥቆማ
"ጌታ ሆይ! አንተ ውበትን የምትፈልግ ሳይሆን ውበትን የምትፈጥር ሙሽራ ነህና፤ ወደ እኔም ና። በሲካር ጉድጓድ አጠገብ ለዚያች ሴት እንደተገለጠህላት፣ ዛሬም በልቤ ደጃፍ ተገልጠህ 'ውሃ ስጪኝ' በለኝ። ጥማቴን የምታውቅ አንተ ብቻ ነህ፤ ምስጢሬን የምታውቅ አንተ ብቻ ነህ። የነፍሴ ሙሽራ ሆይ! በቃልህ ውሃ እጠበኝ፤ በጸጋህ ሽቶ አውደኝ። ያንቺን ታሪክ አውቃለሁ ባልከኝ ጊዜ ኃጢአቴን ሳይሆን ክብሬን እንደመለስክልኝ አውቃለሁና አሁንም 'የምነግርሽ እኔ እርሱ ነኝ' በለኝ። ከስድስቱ ወንዶች (ከዓለም ስሕተትና ከሥጋ ፍላጎት) አውጥተህ ሰባተኛ ወንድ (የፍጹምነት ሙሽራ) ሆነህ ተዋሐደኝ።
ማድጋዬን (ምድራዊ ጭንቀቴን) ጥዬ፣ ስለ ፍቅርህ ምስክር ሆኜ እሮጥ ዘንድ፤ የዘላለም ሕይወት ውሃን በውስጤ አፍልቅልኝ። አንተ ታማኝ ሙሽራ ነህና አትተወኝ፤ አንተ ውበት ፈጣሪ ነህና አትናቀኝ። እንደ ሰማርያዋ ሴት የነፍስ ትድግናን አድርግልኝ። የነፍሴ ሙሽራ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! እንደ ሰማርያዋ ሴት እኔም በሕይወቴ ቀትር ላይ ቆሜአለሁ። ዙሪያዬን የሚከበኝ የዓለም ጫጫታ ቢበዛም ውስጤ ግን እንደ በረሃ ደርቆ ቀርቷል። ለዘመናት የነፍሴን ጥማት ለማርካት ያልሄድኩበት መንገድ ያልቀዳሁበት ጉድጓድ አልነበረም። ጌታ ሆይ! አንተ ምስጢርን የምታውቅ ልብንና ኩላሊትን የምትመረምር አምላክ ነህና ማዳንህን እሻለሁ"
(ከመጽሐፉ የተወሰደ)
ይህን መጽሐፍ በማንበብ መልካም ገበያን ይገብዩ

የድንግል ፍቅር እንደ ምድራዊ ፍቅር አያልቅም፣ አያረጅም፤ እንዲያውም በምንለምናት ቁጥር እንደ አዲስ ይለመልማል። ስብራታችንን የምትጠግኚው በሰማያዊ 'ክር' (በምልጃሽ) ነው። ድንግል ሆይ! ...
28/02/2026

የድንግል ፍቅር እንደ ምድራዊ ፍቅር አያልቅም፣ አያረጅም፤ እንዲያውም በምንለምናት ቁጥር እንደ አዲስ ይለመልማል። ስብራታችንን የምትጠግኚው በሰማያዊ 'ክር' (በምልጃሽ) ነው። ድንግል ሆይ! 'ኡፍፍፍ' ብዬ ትንፋሼን ስተነፍስ፣ በዚያ ትንፋሽ ውስጥ የአንቺ ስም መዓዛ አለው። ዛሬም የልቤን ጓዳ ባዶነት አይተሽ 'ወይን የላቸውም' እንዳልሽው ሁሉ፣ 'ሰላም የለውም፣ ጽናት የለውም' ብለሽ ለልጅሽ ንገሪልኝ። አንቺን ሳስብ ደስተኛ የምሆነው፣ የምታውቂኝ እናቴ ስለሆንሽ ብቻ ሳይሆን፣ ወደ ልጅሽ ፊት የምታቀርቢኝ አማላጄ ስለሆንሽ ነው።

በስንት ህመም
ልቤ ታሞ አፌ ይዋሻል
ፊቴ ደምቆ ያልተጎዳው
ለሰው ይመስላል
አማላጄ ታውቂዋለሽ የልቤን
ስንቱን እሳት እንደቻልኩኝ ለብቻዬን

ልፅናና እንጂ ስላለሺኝ መፅናኛዬ
ታውቂው የለ ምን ልንገርሽ ይሄን ብዬ

Zemarit Mirtnesh Tilahun (New Ethiopian Orthodox Tewahedo Mezmur)© Mirtnesh Tilahun Official Page is the only Channel that has exclusive rights for all mezmu...

ቢቆጠር ኖሮ በደሌ ቢቆጠር ኖሮ ኃጢአቴቢቆጠር ኖሮ በደሌ ቢቆጠር ኖሮ ኃጢአቴእንዴት እቆም ነበረ በፊትህ አባቴ [፪]እስከነ ድካሜ ወደ አንተ መጥቼድንግዝግዙ ቀረ አየሁኝ አጥርቼትናንትናን ሳታ...
26/02/2026

ቢቆጠር ኖሮ በደሌ ቢቆጠር ኖሮ ኃጢአቴ
ቢቆጠር ኖሮ በደሌ ቢቆጠር ኖሮ ኃጢአቴ
እንዴት እቆም ነበረ በፊትህ አባቴ [፪]

እስከነ ድካሜ ወደ አንተ መጥቼ
ድንግዝግዙ ቀረ አየሁኝ አጥርቼ
ትናንትናን ሳታይ በዛሬ መዝነህ
ተቀብለኽኛል ፍሪዳህን አርደህ
ወደ አንተ የመጣ ወደ አንተ የመጣ
ወደ ውጪ አይወጣ

🔴 በማኅቶት ቲዩብ የተለቀቁ ተወዳጅ መዝሙሮችን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፡፡ 👇 👇 👇 https://bit.ly/3C2YHGp🔴 NEW 🔴 አዲስ የንስሃ ዝማሬ ቁጥር 3 " ቢቆጠር ኖሮ " ዘማሪ ዲያቆን አ...

ቅዱስ ገብርኤል በፈተና ወቅት ጽናትን፣ በሐዘን ወቅት መጽናናትን የሚሰጥ የብርሃን ጓደኛ ነው፤ ጌታችን በመቃብር በነበረ ጊዜ ድንጋዩን አንከባሎ ትንሣኤውን ላበሰሩት ሴቶች ብርታትን እንደሰጠ፣...
26/02/2026

ቅዱስ ገብርኤል በፈተና ወቅት ጽናትን፣ በሐዘን ወቅት መጽናናትን የሚሰጥ የብርሃን ጓደኛ ነው፤ ጌታችን በመቃብር በነበረ ጊዜ ድንጋዩን አንከባሎ ትንሣኤውን ላበሰሩት ሴቶች ብርታትን እንደሰጠ፣ ዛሬም አንተ በሐዘን ድንጋይ ስር ብትወድቅ ገብርኤል መጥቶ ያን የመከራ ድንጋይ ያንከባልልሃል። ጨለማው ሲበረታብህ "እሰይ ነጋ" የምትልበትን የትንሣኤ ብርሃን የሚያሳይህ እርሱ ነው። በአማላጅነቱ ለሚታመኑት ሁሉ ገብርኤል ፈጣንና ታማኝ ረዳት ነው።

“ሁለቱም አንድ አካል ይሆናሉ፤ ይህ ነገር ጥልቅ፤ ረቂቅ ምሥጢር ነው፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለሁ፡፡”          ሃይማኖተ አበው ዘስምዓትበዛሬው ዕለት ...
13/01/2025

“ሁለቱም አንድ አካል ይሆናሉ፤ ይህ ነገር ጥልቅ፤ ረቂቅ ምሥጢር ነው፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለሁ፡፡”

ሃይማኖተ አበው ዘስምዓት

በዛሬው ዕለት ጥር ፬/፳፻፲፯ ዓ.ም. በደብረ መጽሔት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን ሥርዓተ ጋብቻችሁን የፈጸማችሁትን የሰንበት ትምህርት ቤታችን አባል የሆንሽው ሃና ኡርጋ (ወለተ ወልድ) እና የቤተ ክርስቲያናችን አገልጋይ ዲያቆን ያሬድ ሃይለ ሚካኤል (ተስፋ ሚካኤል) የፈጸማችኹትን ጋብቻ፤ የአብርሃምንና የሳራን ጋብቻ የባረከ አምላክ፤ የትዳር ሕይወታችሁን ይባርክላችሁ፥ ያጣምራችሁ፥ ያዋሕዳችሁ።

መልካም ምኞት ይመኛሉ የፍሬ ተዋሕዶ ሰንበት ትምህርት ቤት አባላት በሙሉ።

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን+++++++++++++++ልዩ መንፈሳዊ ጉባኤ++++ለ፡- ልጆቼ ሁሉ+++አስቀድሜ መንፈሳዊ የአክብሮት ሰላምታዬን እያቀረብኩ እኔ ፍሬ ተዋሕ...
30/07/2024

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
+++++
+++++
+++++
ልዩ መንፈሳዊ ጉባኤ
++++
ለ፡- ልጆቼ ሁሉ
+++
አስቀድሜ መንፈሳዊ የአክብሮት ሰላምታዬን እያቀረብኩ እኔ ፍሬ ተዋሕዶ የተሰኘሁ የደብረ ዘይት ደብረ መጽሔት ቅድስት ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤት በአምላካችን በልዑል እግዚአብሔር ቅዱስ ፈቃድ የተመሰረትኩበትን 33 ኛ ዓመት የምስረታ በዓሌን በልዩ መንፈሳዊ ዝግጅት ስለማከብር እሁድ ሐምሌ 28/2016 ዓ.ም ከቅዳሴ በኋላ በአውደምሕረት ላይ ከቤተሰቦቻችሁ እና ወዳጆቻችሁ ጋር ተገኝታችሁ ልጆቼ በተለየ ሁኔታ ያዘጋጁትን የነፍስ ማዕድ በጋራ እንድንቋደስ ስል በምትወደን እኛም በምንወዳት በእናታችን በቅድስት ኪዳነምሕረት ስም መንፈሳዊ ጥሪዬን አቀርባለሁ፡፡
++++
++++
አክባሪያችሁ
++++
የደብረ መጽሔት ቅድስት ኪዳነምሕረት ቤ/ክ የፍሬ ተዋሕዶ ሰ/ት/ቤት
++++
++++

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን++++++ታላቅ የክብረ በዓል ጥሪ+++++በደብረ መፅሔት ቅድስት ኪዳነምሕረት ቤተ ክርስቲያን በእለተ እሁድ ሐምሌ 7/2016 ዓ.ም የቅድ...
10/07/2024

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
++++++
ታላቅ የክብረ በዓል ጥሪ
+++++
በደብረ መፅሔት ቅድስት ኪዳነምሕረት ቤተ ክርስቲያን በእለተ እሁድ ሐምሌ 7/2016 ዓ.ም የቅድስት ሥላሴ ዓመታዊ ክብረ በዓል በታላቅ ድምቀት ይከበራል፡፡ ስለሆነም በዕለቱ በመገኘት በዓሉን በጋራ አክበረን በረከቱን እንቋደስ ትላለች ቅድስት ቤተክርስቲያን፡፡

YE FIRE TEWAHIDO LIJOCH
29/06/2024

YE FIRE TEWAHIDO LIJOCH

እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ ሕንፀተ ቤታ (ሕንፀታ) በሰላም አደረሳችኹሰኔ ፳፩ (ሕንፀታ ወቅዳሴ ቤታ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን) ከእመቤታችን ፴፫ቱ በዓላት አንዱ ነው፡...
28/06/2024

እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ ሕንፀተ ቤታ (ሕንፀታ) በሰላም አደረሳችኹ

ሰኔ ፳፩ (ሕንፀታ ወቅዳሴ ቤታ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን) ከእመቤታችን ፴፫ቱ በዓላት አንዱ ነው፡፡

ጌታችንም ከእመቤታችን እና ከቅዱሳን መላእክት ጋር ከሰማየ ሰማያት ወርዶ እመቤታችንን ታቦት፣ ሐዋርያትን ልዑካን አድርጎ፣ እርሱ ሠራዒ ካህን ኾኖ ቀድሶ ካቈረባቸው በኋላ ‹‹እምይእዜሰ አንትሙኒ ከመዝ ግበሩ፤ ከዛሬ ጀምሮ እናንተም እንደዚህ አድርጉ›› ብሎ አዝዟቸው በክብር በምስጋና ወደ ሰማይ ዐርጓል፡፡ ከዚህ በኋላ ሐዋርያት ከጌታ እንዳዩት በዓለም ዞረው ቤተክርስቲያንን አንፀዋል።

እግዚአብሔር አምላክ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ፍቅር፥ ረድኤት፥ ጸጋ - የቡሩካን ሐዋርያቱን በረከት ያሳድርብን! አሜን🙏

Address

Debre Zeyit
23233

Telephone

+251913507382

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Zemari Tadele Fetula Abu posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Zemari Tadele Fetula Abu:

Share