01/04/2026
የመጽሐፍ ጥቆማ
"ጌታ ሆይ! አንተ ውበትን የምትፈልግ ሳይሆን ውበትን የምትፈጥር ሙሽራ ነህና፤ ወደ እኔም ና። በሲካር ጉድጓድ አጠገብ ለዚያች ሴት እንደተገለጠህላት፣ ዛሬም በልቤ ደጃፍ ተገልጠህ 'ውሃ ስጪኝ' በለኝ። ጥማቴን የምታውቅ አንተ ብቻ ነህ፤ ምስጢሬን የምታውቅ አንተ ብቻ ነህ። የነፍሴ ሙሽራ ሆይ! በቃልህ ውሃ እጠበኝ፤ በጸጋህ ሽቶ አውደኝ። ያንቺን ታሪክ አውቃለሁ ባልከኝ ጊዜ ኃጢአቴን ሳይሆን ክብሬን እንደመለስክልኝ አውቃለሁና አሁንም 'የምነግርሽ እኔ እርሱ ነኝ' በለኝ። ከስድስቱ ወንዶች (ከዓለም ስሕተትና ከሥጋ ፍላጎት) አውጥተህ ሰባተኛ ወንድ (የፍጹምነት ሙሽራ) ሆነህ ተዋሐደኝ።
ማድጋዬን (ምድራዊ ጭንቀቴን) ጥዬ፣ ስለ ፍቅርህ ምስክር ሆኜ እሮጥ ዘንድ፤ የዘላለም ሕይወት ውሃን በውስጤ አፍልቅልኝ። አንተ ታማኝ ሙሽራ ነህና አትተወኝ፤ አንተ ውበት ፈጣሪ ነህና አትናቀኝ። እንደ ሰማርያዋ ሴት የነፍስ ትድግናን አድርግልኝ። የነፍሴ ሙሽራ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! እንደ ሰማርያዋ ሴት እኔም በሕይወቴ ቀትር ላይ ቆሜአለሁ። ዙሪያዬን የሚከበኝ የዓለም ጫጫታ ቢበዛም ውስጤ ግን እንደ በረሃ ደርቆ ቀርቷል። ለዘመናት የነፍሴን ጥማት ለማርካት ያልሄድኩበት መንገድ ያልቀዳሁበት ጉድጓድ አልነበረም። ጌታ ሆይ! አንተ ምስጢርን የምታውቅ ልብንና ኩላሊትን የምትመረምር አምላክ ነህና ማዳንህን እሻለሁ"
(ከመጽሐፉ የተወሰደ)
ይህን መጽሐፍ በማንበብ መልካም ገበያን ይገብዩ