22/03/2021
አዛኝ ፍቅር - ማክሰኞ፣ የካቲት 30/2013 ዓ.ም.
እንኳን ወደ የኢትዮጵያ ሉተራዊት ቤተ ክርስቲያን፤ የዕለት እንጀራ መጣችሁ!
የእግዚአብሔር ቃል - ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል፤ ቅዱስ ማርቆስ እንደፃፈው፤ ምዕራፍ 1፤ ቁጥር 13፡-
በምድረ በዳም ከሰይጣን እየተፈተነ አርባ ቀን ሰነበተ ከአራዊትም ጋር ነበረ፥ መላእክቱም አገለገሉት። (ማርቆስ 1፡13)
አዛኝ ፍቅር
“በእኔ ቦታ ሆነህ፤ አንድ ኪሎ ሜትር ካልተጓዝህ፤ እኔን አትረዳም፡፡”
እንደዚህ ያለ አሳብ ኖሮህ ወይም ኖሮሽ ያውቃልን? በየቀኑ፤ ችግሮች፣ መከራዎችና ፈተናዎች ያጋጥሙናል፡፡ በየቀኑ፤ ብዙ ሰዎች፤ የሚቀርቡንም ጭምር፤ ግማሹንም የምናልፍባቸውን ሁኔታዎች አያውቁም፡፡ አንዳንድ ጊዜ፤ እኛን እንዳይጠይቁን በጣም ሥራ በዝቶባቸው ወይም በጣም ለእራሳቸው በመጠንቀቅ ላይ ስላተኮሩ ሊሆን ይችላል፡፡ በሌሎች ጊዜያት፤ የምናስበውን፣ የሚሰማንንና የደረሰብንን በመደበቅ በውስጣችን ከመያዛችን የተነሳ ሊሆን ይችላል፡፡
ማንም ብትሆኑ ማንም ወይም ምንም ቢገጥማችሁ፤ እጅግ በጣም ቀርቦ የሚያውቃችሁ አንድ ሰው አላችሁ፡፡ ስሙም ኢየሱስ ነው፡፡ እናንተ ያላችሁበት እና የምታልፉበት የሕይወት እውነታዎች ያልነካው አይደለም፡፡ እናንተ የሚያስቸግሯችሁን ነገሮች መነሻዎች ሁሉ ያውቃል፡፡ በአመፅ የሚበጠብጧችሁን ነገሮች ሁሉ ያውቃል፡፡ እናንተን ባስቸገሯችሁ ቦታዎች ሆኖ ሁሉን አልፎበታል፡፡ እናንተ በምታልፉባቸው ድካሞችና ፈተናዎች ሁሉ አልፏል፡፡ ከኃጢአት በስተቀር፤ ሁሉም ነገር ደርሶበታል፡፡ እርሱ በሁሉም ነገሮች ስላለፈ፤ ሊጠብቃችሁና ሊከላከልላችሁ ይችላል፡፡
ሊጠብቃችሁና ሊከላከልላችሁ ተወለደ፡፡ የዲያብሎስን ሥራ ሊያፈርስ፤ ወደዚህ ዓለም መጣ፡፡ የዲያቢሎስ ሥራ ኃጢአት ነው፤ የመጨረሻ ግቡም የእኛ መኮነን (ኩነኔ መግባት) ነው፡፡ ነገር ግን፤ ኢየሱስ ዲያቢሎስን ተዋግቶልን አሸነፈልን፡፡ በእግዚአብሔር ፊት ሊያፀድቀን፤ በጭራሽ ኃጢአትን ባላደረገው ኢየሱስ ላይ፤ እግዚአብሔር የእኛን ኃጢአት በኢየሱስ ላይ አደረገ፡፡ ኢየሱስ የእኛን ሥቃይና ሰቆቃ ተቀበለ፤ ሞታችንንም ሞተ፡፡ ኃጢአታችንን፣ ሥቃያችንንና ሞታችንን ወስዶ፤ የእርሱን የፅድቅ ሕይወት ሰጠን፡፡ ኢየሱስ በመሥቀል ላይ እስኪሞትልን ድረስ ስለታዘዘ፤ በእርሱ የሚታመኑ ሁሉ፤ ፍፁም ቅዱሳን (ንፁሀን) ናቸው፡፡ እግዚአብሔር በደለኞች ናችሁ ብሎ አይፈርድብንም፡፡
ኢየሱስ የሚጠብቃችሁ፤ ወደፊት ሊመጣ ካለው ፍርድ ብቻ ሳይሆን፤ በየቀኑ ከሚደርስባችሁ ከማንኛውም ነገር፤ በኃይሉ ሊጠብቃችሁ ዝግጁም ነው፡፡ ይህ ማለት ግን፤ እንደገና ከቶ አትፈተኑም፣ መከራ አትቀበሉም ወይም አትፈተኑም ማለት አይደለም፡፡ ነገር ግን፤ ፈተናዎች ሲመጡ፤ የኢየሱስ ጥበቃ፤ ከፀሎት የቀረበ ነው፡፡
ኢየሱስ ይረዳል (ጠበቅ ተደርጎ ሲነበብ)፡፡ ከዲያቢሎስ ሥራ ነፃ ሊያወጣህ፤ ነፃ ሊያወጣሽ ሞተና ከሞት ተነሣ፡፡ ለየትኛውም ችግርህ፤ በማንኛውም ጊዜ ወደ እርሱ ሂድ፡፡ ለየትኛውም ችግርሽ፤ በማንኛውም ጊዜ ወደ እርሱ ሂጂ፡፡ ከዲያቢሎስ ጋር ያለህን ውጊያ ለመቋቋም፤ ብርታት እንዲሰጥህ ጠይቀው፤ ኢየሱስ ብርታቱን ይሰጥሃል፡፡ ከዲያቢሎስ ጋር ያለሽን ውጊያ ለመቋቋም፤ ብርታት እንዲሰጥሽ ጠይቂው፤ ኢየሱስ ብርታቱን ይሰጥሻል፡፡ ዲያቢሎስም ይሸሻል፡፡
ፀሎት፡- ሰማያዊ አባት፤ እግዚአብሔር ሆይ፤ ወደ ፈተና አታግባኝ፤ ከክፉው አድነኝ እንጂ፡፡ አሜን፡፡
ይህን የዕለት እንጀራ ስለተካፈሉ እናመሰግናለን! ለቤተሰብዎ እና ለጓደኞችዎ በማካፈል ወይም share በማድረግ፤ እንዲሁም ማየት የተሳናቸው፤ የድምፁን ፋይል እንዲሰሙ፤ መስማት የተሳናቸው፤ ፅሁፉን እንዲያነቡ በማመቻቸት፤ መንፈሳዊ ሕይወታቸው እንዲታነፅ ይርዱ!
ለተጨማሪ የእግዚአብሔር ቃል አገልግሎት፡- 0930-107598 ወይም 0964-326486 ላይ ይደውሉ፡፡ [email protected] ላይ ይፃፉልን፡፡
ቢሾፍቱ (ደብረ ዘይት)፣ ኢያሱ ሜዳ፣ የባቡር ሐዲድ ተሻግሮ፣
ምስራቅ ሸዋ ዞን፣ ኦሮምያ ክልል፣ ኢትዮጵያ፡፡
የእንግሊዘኛውን ቅጂ ለማግኘት https://wels.net/dev-daily/ የሚለውን ሊንክ ይጎብኙ፡፡
To access the English version, check out this link https://wels.net/dev-daily/
አዛኝ ፍቅር - ማክሰኞ፣ የካቲት 30/2013 ዓ.ም.እንኳን ወደ የኢትዮጵያ ሉተራዊት ቤተ ክርስቲያን፤ የዕለት እንጀራ መጣችሁ! የእግዚአብሔር ቃል - ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል፤ ቅዱስ ....