Haymanote abew-ሐይማኖተ አበው

Haymanote abew-ሐይማኖተ አበው ይህ ፔጅ ለኦርቶዶክሳውያን መንፈሳዊ ህይዎት ጠቃሚ የሆኑ ጽሁፎች ከቅዱሳን አበው መጻህፍት እየተቀነጨቡ የሚለቀቁበት ነው ላይክ፣ ፎሎው እና ሸር ያድርጉ

31/05/2025

ቅዱስ ጊዮርጊስ

በ፸ ነገሥታት መካከል ብቻውን ቁሞ "እኔ ክርስቲያን ነኝ የማመልከውም አምላኪየ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።" ብሎ ሲመሠክር ወጣትነት እና የሥጋ ፍርሀት አልገደበውም።
ይልቁንም ዓላውያን ነገሥታት "በክፉ አሟሟት እንዳትሞት ለአጵሎን ሠዋ" ባሉት ጊዜ በፍቅረ እግዚአብሔር ተናዶ፦
" ከክርስቶስ ፍቅር ማን ይለየኛል? መከራ፣ ወይስ ጭንቀት፣ ወይስ ስደት፣ ወይስ ራብ፣ ወይስ ራቁትነት፣ ወይስ ፍርሃት፣ ወይስ ሰይፍ ነውን?"ሮሜ.፰፥፴፭

እያለ እየዘመረ ወደ ሞት ሄዴ።
ገና የ፳ ዓመት ወጣት ቢሆንም አበባ ሰውነቱ አላሳሳውም።
ነገሥታቱ ብዙ መደለያ አቅርበው ሊያባብሉት ሞከሩ ግን ከክርስቶስ ፍቅር የሚለየው መደለያ አልተገኘም።
ሹመትም ገንዘብም ለጊዮርጊስ ኢምንቶች ናቸው።
ስለ ክርስቶስ ስም ብሎ ሁሉን ንቆ መከራ ስለተቀበለ ዛሬ የሁላችን አባት ሆነ።
ክብሩም በሰማይና በምድር የሚነገርለት ቅዱስ ነውና ሊቀ ሰማዕታት፣ፍጡነ ረድኤት ተባለ።
ተፈጭቶ ለነፋስ የተበተነው ሰውነቱ ብፁዕ እየተባለ በሰው ሁሉ እስትንፋስ የሚመሰገን ሆነ።
ሰማዕትነት በምንም የማትወሰድ ፍጽምት ሂሊና ናት።

source; ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

30/05/2025

ሁለተኛው ምዕራፍ; በአቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ

ጌታ እንዲህ ብሏል '' እጀጠባብህን ሊወስድ ለሚወድ መጎናጸፊያህን ደግሞ ተውለት ማንም ሰው አንድ ምዕራፍ ትሄድ ዘንድ ቢያስገድድህ ሁለተኛውን ከርሱ ጋር ሂድ።'' ማቴ 5; 40_41

ከዚሁ ጋር ተመሳሳይ በሆነው ትዕዛዙ ውስጥ ዳሩ ግን ቀኝ ጉንጭህን በጥፊ ለሚመታህ ሁሉ ሁለተኛውን ደግሞ አዙርለት። '' ብሏል። ማቴ 5; 39

በእነዚህ ሁሉ ጌታ ''ተበደሉ እንጂ አትበድሉ ተሰቀሉ እንጂ የምሰቅሉ አትሁኑ እናንተ አትበቀሉ'' እያለን ነው።

30/05/2025

.................የዘሪው የሃሳብ ዘር...........

እኔነቴ፤ ለኔ በሚጠቅሙኝ ይልቁንም ለኔ በሚያስፈልጉኝን ጉዳዮች ላይ ትኩረቴን እንዳላደርግ ይከለክለኛል። ይሀውም በእግዚአብሔር መንገድ እንዳልጓዝ በማድረግ ነው።
ይልቁንም ሃሳቦቸ ሁሉ ለኔ ዘላቂ(የዘላለም) ትርፍ በማያስገኙልኝ ጥራጊ ጉዳዮች የተሞሉ ናቸው። በእግዚአብሔር ቃል ሚዛንነት ሲመዘኑም ረብ የሌላቸው ናቸው።

እኔነቴ ግን በእነዚህ ምድራዊ ሃሳቦችና ግቦች እኔን ከማድከም አልደከመም።

አንዳንድ ጊዜ በሮቹ በተቆለፉ እስር ቤት ዉስጥ ያለው ይመስል ከአፍአ ሲታዩ እጂግ ጠቃሚ በሚመስሉ በቈኤት የሌላቸው ምድራዊ ሃሳቦች ተከብቤ ከሃሳቦች መውጫ ቀዳዳ በማማተር እጨነለቃሁ።

ሃሳቦች እራሳቸውን አስጊጠው በወርቅ፣ በብርና በአልማዝ የተሸለመ ንጉስን መስለው ፤ እኔን ለማገልገል ንጉስ ለባለሟሉ የላካቸውን አገልጋዮች መስለውና ውብና የተወደዱ ሁነው በአእምሮየ(በውስጡ ሰውነቴ) ሚዛን ፊት ይቀርባሉ።

ሃሳቦችን በልምድ፣ በእውነትና በኅሊና ሚዛን መዝኖ መቀበል ወይም አለመቀበል ብቸኛው ስራው የሆነው አእምሮየ(የውስጡ ሰውነቴ) እነዚህን አጊጠውና ተውበው የቀረቡለትን ሃሳቦች ግን በሦስቱም ሚዛኖች ሳይመዝን እንደመልካም እንግዳ በተመረጠ ስፍራ ማረፊያ ያዘጋጅላቸዋል።

የውስጡ ሰውነቴም ሃሳቦችን ተቀብሎ ቦታ በሰጣቸው መጠን ሃሳቦቹ ተደላድለው ሌላ እነሱን የመሰሉ ሃሳቦችን ይወልዳሉ። ግዘፍ ነስተውም በቃላት፣ በስሜት ከፍ ሲልም በድርጊት ወደመገለጽ ያድጋሉ በዚሁ ሲገለጹም ደጋግሜ እመለከታለሁ።

እኔም ብዙ ግዜ የሃሳቦቸን ውጤት የምረዳው ከዚ ደረጃ ላይ ሲደርሱ ነው። ቃላቶቸና ምግባሮቸንም(ድርጊቶቸን) በእግዚአብሔር ሚዛን ስመዝናቸው ቀለውና ተዋርደው ይገኛሉ።

ረብ የለሽ ሃሳቦች ተዘሩ የሚታጨዱትም እንዲሁ ሆኑ። ሰው የዘራውን ያጭዳልና። መራራ ዘርቶ ወይን የሚያጭድ ማነው። ቃላቶችና ምግባሮችን(ድርጊቶችን) ለማስተካከል ተደጋግሞ ቢሞከርም ማስተካከል አልተቻለም። ፍሬውን ሳይሆን የሚዘራውን ማስተካከል ይቀድማልና። ዘሪው መምረጥ የሚችለው መጀመሪያ የሚዘራውን ነው። የሚታጨደው ፍሬው ግን የማይቀየር ነው።

የውስጡ ሰውነቴም ቁልፉ ያለው የሃሳቦች ሚዛን ጋር እንደሆነ ተረዳ። ስለዚህም ለእያንዳንዷ በሰወች አእምሮ የምትፈጠር ሃሳብ "እሳትና ውሃ አቅርቤልሃለው ወደፈለከው እጅህን ስደድ" በሚለው የእግዚአብሔር ቃል ሚዛን ፤ ማለትም ማንኛውንም ሃሳብ በእግዚአብሔር ቃል፣ በእውነትና በመልካም ኅሊና ሚዛን መዝኖ መቀበል ወይም አለመቀበል(reject) ከሀሳብ ዘር ለሚታጨደውን ፍሬ መወሰኛ ማሕተም ነው።

ስለዚህም ከሃሳብ ዘር የሚታጨደው ፍሬ ቃልና ድርጊት(ንግግር እና ድርጊት) መክፈቻ ቁልፉም የሃሳብ ዘር ሚዛን እንደሆነ ተረዳሁኝ።

ተጻፈ በ ገብረ ማርያም...

ይካቲት 29, 2017 ዓ.ም

እንዳይፈረድብህ በባልንጀራህ ላይ አትፍረድበአንድ ወቅት በግብጽ ገዳማት አንድ ወጣኒ መነኩሴ “ጥፋት አጠፋ፣ ሥርዓተ ገዳም አፋለሰ” ተብሎ መናንያኑ ጉዳዩን እንዲያዩና እንዲወስኑበት ከየበአታቸ...
17/06/2024

እንዳይፈረድብህ በባልንጀራህ ላይ አትፍረድ
በአንድ ወቅት በግብጽ ገዳማት አንድ ወጣኒ መነኩሴ “ጥፋት አጠፋ፣ ሥርዓተ ገዳም አፋለሰ” ተብሎ መናንያኑ ጉዳዩን እንዲያዩና እንዲወስኑበት ከየበአታቸው ተጠሩ፡፡ ከተጠሩት መነኮሳት መካከል አንዱ ጥቁሩ ኢትዮጵያዊው ሙሴ ጸሊም ነበር፡፡ እርሱም ሁሉም ከተሰበሰቡ በኋላ ዘግይቶ በተቀደደ አቁማዳ አሸዋ በጀርባው አዝሎ አሸዋውን ከኋላው እያፈሰሰ መጥቶ በመሃላቸው ተገኘ፡፡
የተሰበሰቡት መነኮሳትም አባ ሙሴን ይህን ስለምን አደረግከው ብለው በጠየቁት ጊዜ በሀዘን ተውጦ “በጀርባዬ የማላያቸውን ስፍር ቁጥር የሌላቸው ኃጢአቶቼን ተሸክሜ ሳለሁ በወንድሜ ለመፍረድ መጥቻለሁ” አላቸው፡፡ መነኮሳቱም እጅግ ተጸጸቱ፡፡ ጉባኤውም ፍርዱን ትቶ ተበተነ፡፡
“እንዳይፈረድብህ በባልንጀራህ አትፍረድ” የሚለውን የወንጌል ቃልም በተግባር አስተማራቸው፡፡ ልብን በሚነካ በዚህ በጎ ትምህርቱም መነኮሳቱን ከመፍረድ ሃጢአት ታደጋቸው፡፡

ብርጭቆውን ወይስ ባሕሩን ማሰብባንድ ወቅት በሕይወቱ ደስታን ያጣው ታዳጊ ወጣት አንድ የዕድሜ ባለጸጋን ሽማግሌ ሕይወት እንዳማረረችው ገልጾ መፍትሄ እንዲጠቁሙት ጠየቃቸው፡፡ ሽማግሌው የወጣቱን...
16/06/2024

ብርጭቆውን ወይስ ባሕሩን ማሰብ

ባንድ ወቅት በሕይወቱ ደስታን ያጣው ታዳጊ ወጣት አንድ የዕድሜ ባለጸጋን ሽማግሌ ሕይወት እንዳማረረችው ገልጾ መፍትሄ እንዲጠቁሙት ጠየቃቸው፡፡ ሽማግሌው የወጣቱን ሀሳብ በጥሞና ካደመጡ በኋላ በእፍኙ ሙሉ ጥሬ ጨው በብርጭቆ ውሃ ጨምሮ በጥብጦ እንዲጠጣው አዘዙትና “ጣምናው እንዴት ነው?” በማለት ጠየቁት፡፡ ፊቱን አኮሳትሮ “በጣም አስቀያሚ ነው!” ሲል መለሰላቸው፡፡

ሽማግሌው ፈገግታ እያሳዩት ወጣቱን ወደ ባሕር ዳርቻ ወስደው ሌላ ጭብጥ ሙሉ ጨው ባሕሩ ውስጥ እንዲጨምርበት አመላከቱት፡፡ በመቀጠልም ከባሕሩ ጨልፎ እንዲጠጣ ካደረጉ በኋላ “ጣዕሙ እንዴት ነው?” ሲሉ በድጋሜ ጥያቄ አቀረቡለት፡፡ “ጥሩ ነው” በማለት መለሰ ታዳጊው፡፡ አስከትለውም “የጨው ኮምጣጣነትና ያ አስቀያሚው ስሜት ተለይቶሃል?” በማለት ጠየቁት፡፡ “በፍጹም” ሲል መለሰ ወጣቱ፡፡

ከዚህ ሁሉ የተግብር ትምህርት ቀጥሎ ሽማግሌው የወጣቱን እጅ ይዘው ከጎኑ ተቀመጡና ይሄንን መከሩት፡፡ በሕይወት ጎዳና የምታደርጋቸው ትግሎች እንደ ንጹህ ጥሬ ጨው ናቸው፡፡

ነገር ግን የስቃዩ መጠን ተመሳሳይ ቢሆንም የምንሸከመው ስቃይ የሚወሰነው በምንይዝበት ዕቃ መጠን ይወሰናል፤ ችግሩን የምናስተናግድበት አግባብም የሚፈጥረውን ጫና በዛው ልክ ይለያየዋል፡፡ ችግሩ ሲጠናብህ ልታደርገው የሚገባው ዋናው ነገር ምልከታህን ማስፋት ብርጭቆውን ሳይሆን ባሕሩን መሆን ነው ትልቁ የአኗኗር መላው፡፡ እናም ብርጭቆ መሆንህን አቁመህ ባሕሩን ሁን በማለት አሰናበቱት

telegram link

Address

Debre Tabor
Debre Tabor

Telephone

+251962895365

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Haymanote abew-ሐይማኖተ አበው posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Haymanote abew-ሐይማኖተ አበው:

Share