የምሥ/ጎ/ሀ/ስ/ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ወጣቶች ኅብረት/ EGD Orthodox Tewhido Youth Union

  • Home
  • Ethiopia
  • Debre Mark'os
  • የምሥ/ጎ/ሀ/ስ/ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ወጣቶች ኅብረት/ EGD Orthodox Tewhido Youth Union

የምሥ/ጎ/ሀ/ስ/ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ወጣቶች ኅብረት/ EGD Orthodox Tewhido Youth Union ይህ የምሥ/ጎ/ሀ/ስ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ወጣቶች ኅብረት ዋና ገጽ ነው።

+++የኢትዮጵያ የፀሎት ቤት በሰማይ!+++ በአምስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን የተመሰረተ  ዕፁብ ድንቅ የፀሎት ቤት!
07/04/2023

+++የኢትዮጵያ የፀሎት ቤት በሰማይ!+++
በአምስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን የተመሰረተ ዕፁብ ድንቅ የፀሎት ቤት!

If churches were assessed by their risk factor, Abuna Yemata Guh would be our new Sistine Chapel. Perched 650 feet above a steep cliff in Northern Ethiopia, ...

መጋቢት 24/2015 ዓ.ም "እኔ የተዋሕዶ ድምፅ ነኝ! እናንተስ?" ልዩ ጉባኤ ይካሄዳል። "እኔ የተዋሕዶ ድምፅ ነኝ!እናንተስ?" በሚል መሪ ቃል ማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ከየካቲት 30/201...
31/03/2023

መጋቢት 24/2015 ዓ.ም "እኔ የተዋሕዶ ድምፅ ነኝ! እናንተስ?" ልዩ ጉባኤ ይካሄዳል።
"እኔ የተዋሕዶ ድምፅ ነኝ!እናንተስ?" በሚል መሪ ቃል ማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ከየካቲት 30/2015 ዓ.ም ጀምሮ የስቱዲዮ እቃ፣መኪና እና ጄኔሬተር በአስቸኳይ ለመግዛት ገቢ እያሰባሰበ መሆኑ ይታወቃል።
አገልግሎቱን ለመደገፍ
ጎ ፈንድ ሚ ማስፈንጠሪያ
https://www.gofundme.com/f/gtbbd?utm_source=customer...
ወገን ፈንድ
Www.wegenfund.com/mk01
የባንክ አካውንት ቁጥር አማራጮች
****
ንግድ ባንክ 1000010822657 (BETH.TEW.SENBET.TBET MAHIB.KID
+++++++++++++++++++++++++
ወጋገን ባንክ 0039595010103
+++++++++++++++++++++++++
አቢሲንያ ባንክ 4753388
+++++++++++++++++++++++++
ዳሸን ባንክ 0088872166011
+++++++++++++++++++++++++
አዋሽ ባንክ 01304800017700
±++++++++++++++++++++++
አሐዱ ባንክ 0003488710101
+++++++++++++++++++++
አማራ ባንክ 9900017695658
+++++++++++++++++++++
ኦሮምያ ኅብረት ስራ ባንክ 1033100028173

በ3 ሰዓታት ውስጥ 105 ሺህ የአሜሪካን ዶላር ተሰበሰበ። ++++++++++++++++++++++++++++++++++"እግዚአብሔር መልካም ነገርን አደረገልን፤ ደስም አለን!"መዝሙር 125÷3 መጋ...
27/03/2023

በ3 ሰዓታት ውስጥ 105 ሺህ የአሜሪካን ዶላር ተሰበሰበ።
++++++++++++++++++++++++++++++++++
"እግዚአብሔር መልካም ነገርን አደረገልን፤ ደስም አለን!"
መዝሙር 125÷3
መጋቢት 17/2015ዓ.ም ሌሊት ለማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ድጋፍ በአሜሪካ በተካሄደ ገቢ አሰባሰብ በ3 ሰዓታት ውስጥ ብቻ 105,000 የአሜሪካ ዶላር ለመሰብሰብ ተችሏል።
በአሜሪካ ማዕከል ሚዲያ ክፍል አስተባባሪነት የተደረገው የዚህ ዘመቻ ድጋፍ አድራጊዎች ለቤተ ክርስቲያን ያላቸውን ቀናዒነት እና ለቴሌቪዥን ጣቢያው አጋርነታቸውን ያሳዩበት ሲሆን ሳምንት የሚቀጥል ይሆናል።
"እኔ የተዋሕዶ ድምፅ ነኝ!እናንተስ?" በሚል መሪ ቃል ማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ከየካቲት 30/2015 ዓ.ም ጀምሮ የስቱዲዮ እቃ፣መኪና እና ጄኔሬተር በአስቸኳይ ለመግዛት ገቢ እያሰባሰበ መሆኑ ይታወቃል።
አገልግሎቱን ለመደገፍ
ጎ ፈንድ ሚ ማስፈንጠሪያ
https://www.gofundme.com/f/gtbbd?utm_source=customer...
ወገን ፈንድ
Www.wegenfund.com/mk01
የባንክ አካውንት ቁጥር አማራጮች
****
ንግድ ባንክ 1000010822657 (BETH.TEW.SENBET.TBET MAHIB.KID
+++++++++++++++++++++++++
ወጋገን ባንክ 0039595010103
+++++++++++++++++++++++++
አቢሲንያ ባንክ 4753388
+++++++++++++++++++++++++
ዳሸን ባንክ 0088872166011
+++++++++++++++++++++++++
አዋሽ ባንክ 01304800017700
±++++++++++++++++++++++
አሐዱ ባንክ 0003488710101
+++++++++++++++++++++
አማራ ባንክ 9900017695658
+++++++++++++++++++++
ኦሮምያ ኅብረት ስራ ባንክ 1033100028173

" እኔ የተዋሕዶ ድምጽ ነኝ! እናንተስ?" በሚል መሪ ቃል የማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ጣቢያን ለማጠናከር የአጭር ጊዜ፣ መካከለኛ ጊዜና ረጅም ጊዜ እቅድ አውጥተን በመንቀሳቀስ ላይ እንገኛለ.....

የብፁዕ ዶ/ር አቡነ አረጋዊ የድሬድዋና ጅቡቲ አኅጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አስከሬን ከሀሌ ሉያ ሆስፒታል ወደ መንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ሂዶ ለማረፍ በዝግጅት ላይ ነው።በ...
25/03/2023

የብፁዕ ዶ/ር አቡነ አረጋዊ የድሬድዋና ጅቡቲ አኅጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አስከሬን ከሀሌ ሉያ ሆስፒታል ወደ መንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ሂዶ ለማረፍ በዝግጅት ላይ ነው።

በመርሐ ግብሩ ላይ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና ቤተሰቦቻቸው ተገኝተዋል።
በረከታቸው ይደርብን።
Mahibere Kidusan Broadcast Service

በአዲስ አበባ ኃይሌ ጋርመንት አካባቢ መጋቢት 14/2015 ዓ.ም ቀሲስ ዐባይ መለሰ የተባሉ ካህን ቅዳሴ ጨርሰው ወደ ቤታቸው በመሄድላይ እንዳሉ በድንጋይ ተወግረው ሕይወታቸው ማለፉን የዐይን ...
25/03/2023

በአዲስ አበባ ኃይሌ ጋርመንት አካባቢ መጋቢት 14/2015 ዓ.ም ቀሲስ ዐባይ መለሰ የተባሉ ካህን ቅዳሴ ጨርሰው ወደ ቤታቸው በመሄድላይ እንዳሉ በድንጋይ ተወግረው ሕይወታቸው ማለፉን የዐይን እማኞች እንደነሩት ገልጾ የማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ዘግቧል።

የሆርሲሳ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ የነበሩት ቀሲስ ዐባይ መለሰ ሕይወታቸው ሲያልፍ ችግሩ ታወቀ እንጂ አስቀድሞ በአካባቢው አገልጋዮች ላይ ዛቻ እና ማስፈራሪያ ይደርስ እንደነበር መረጃ ሰጭዎቻችን በቦታው ለተገኘው ዘጋቢያችን ገልፀዋል።

ካህኑ በድንጋይ ተደብድበው እያሉ ምስልና ቪዲዮ ለማስረጃ ለመያዝ ቢሞክሩም በአካባቢው የፀጥታ ኃይሎች ሞባይል እየተሰበሰበ መሰረዙንም የማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ዘግቧል።

በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት በጊንብቹ ወረዳ መጋቢት 1ቀን 2011 ዓ.ም የቦይንግ 737 አውሮፕላን አደጋ በደረሰበት ቦታ ላይ ቤተክርስቲያን ለመሥራት በብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ መልካም ፈቃድ ...
11/03/2023

በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት በጊንብቹ ወረዳ መጋቢት 1ቀን 2011 ዓ.ም የቦይንግ 737 አውሮፕላን አደጋ በደረሰበት ቦታ ላይ ቤተክርስቲያን ለመሥራት በብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ መልካም ፈቃድ የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ ፡፡
+++
የዛሬ አራት ዓመት መጋቢት 1ቀን 2011 ዓ.ም የኢትዮጵያ አየር መንገድ ንብረት የሆነው ቦይንግ 737 አውሮፕላን ከአዲስ አበባ ወደ ኬንያ ጉዞ እንደ ጀመረ በምሥራቅ ሸዋ ጊንብቹ ወረዳ ልዩ ስማ ሐማ ቁንጡሽሌ በተባለ ቦታ ላይ በደረሰበት አደጋ የአውሮፕላኑ ሠራተኞች ጨምሮ 157 የተለያዩ ሀገራት ዜጎች ሕይወታቸው ማለፉ ይታወሳል። በዚሁ ዕለት ሕይወታቸውን ያጡት 17 ኢትዮጵያውያን ሲሆኑ የእነዚሁ ኢትዮጵያውያን ቤተሰቦች በየዓመቱ አደጋው በተፈፀመበትና አስከሬናቸው ባረፈበት ቦታ መታሰቢያ እያደረጉ ቆይተዋል፡፡
እነዚሁ የአደጋው ሰለባ የሆኑ ቤተሰቦች በቦታው ላይ ለመታሰቢያ የሚሆን ቤተ ክርስቲያን ለመሥራት ከ7000 ካሬ ሜትር በላይ ቦታ ገዝተው ባቀረቡት ጥያቄ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ መልካም ፈቃድ ዛሬ የ4ኛ ዓመት መታሰቢያ በሚከበርበት ቀን መጋቤ ጥበብ ቀሲስ ጌቱ ሞቲ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ልዩ ፀሐፊ ፣ መ/ሐ/ቆሞስ አባ ገ/ፃድቅ መኮንን የሀገረ ስብከቱ ስብከተ ወንጌል ክፍል ኃላፊ፣ ሊቀ ትጉኃን መንክር አቤ፣ መ/ኃ/ቀሲስ ኃ/መስቀል የጊንቢቹ ወረዳ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ እንዲሁም ከአዲስ አበባ መ/ር ዘላለም ወንድሙ ና ዘማሪያን እንዲሁም ሕይወታቸውን ያጡ ቤተሰቦች በተገኙበት የመሠረት ድንጋይ ተቀምጧል።
በመርሐግሩ ላይ በዘማሪ ፈቃዱ አማረና በዘማሪ ይትባረክ ተገኘ የማጽናኛ ዝማሬ የቀረበ ሲሆን በመምህር ዘለዓለም ወንድሙ የሚያጽናና ትምህርተ ወንጌል ተሰጥቷል ፡፡ በመቀጠልም መጋቤ ጥበብ ቀሲስ ጌቱ ሞቲ ይህን ቅዱስ ዓላማ ወገኖቻቸውን ለማሰብ ቤተክርስቲያንን ለማነጽ መነሳሳታቸው እጅግ የሚበረታታ መሆኑና ዘመን የማይሽረው ታሪክን በወገኖቻቸው ስም እያስቀመጡ መሆኑን ገልጸው የብፁዕነታቸውን አባታዊ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡
© ሐመረ ተዋሕዶ ሚዲያ

ብፁዕ አቡነ ዲዮናስዮስ በምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት የእሳት ቃጠሎ በደረሰበት በሰብሸንጎ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን በመገኘት ምእመናንን አጽናኑ።                           ...
20/02/2023

ብፁዕ አቡነ ዲዮናስዮስ በምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት የእሳት ቃጠሎ በደረሰበት በሰብሸንጎ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን በመገኘት ምእመናንን አጽናኑ።
+++
በምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሥር በደጀን ወረዳ ውስጥ በሚገኘው የሰብሸንጎ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ላይ በኤሌክትሪክ ምክንያት በተፈጠረ የእሳት አደጋ በተፈጠረው ውድመት እና አንድ ሰው ኅልፈት ምክንያት ብፁዕ አቡነ ዲዮናስዮስ በቦታው በመገኘት ምእመናንን አጽናንተዋል።

በምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት በደጀን ወረዳ ቤተ ክህነት ጽሕፈት ቤት ሥር በ1267 ዓ.ም የተመሠረተው ደብረ መድኃኒት ሰብሸንጎ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን በርካታ ካህናትና ምእመናን ያሉበት ደብር ሲሆን የካቲት 12 ቀን 2015 ዓ.ም በግምት ከቀኑ 7:00 ሰዓት ከውስጥ በተነሳ የኤሌክትሪክ እሳት አደጋ ሙሉ በሙሉ ወድሟል።

በአካባቢው ያሉ ምእመናን የወረዳ ቤተ ክህነቱ፣ የወረዳው የጸጥታ አካላትና የወረዳው መንግስት የተለያዩ ተቋማት ቢረባረቡም ማትረፍ አለመቻሉ የተገለጸ ሲሆን በእሳት አደጋ ቃጠሎ ምክንያትም የአንድ ወጣት ሕይወት ሊያልፍ ችሏል።
ብፁዕ አቡነ ዲዮናስዮስ የምሥራቅ ጎጃም እና ጀርመን እና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ የክልሉ የመንግስት ተወካዮች፣ የዞን የመንግሥት ተወካዮች ፣የደጀን ወረዳ የመንግስት አካላት፣ የወረዳው የፖሊስ ኃላፊና አጋሮቹ የወረዳው ቤተ ክህነት ሠራተኞች በቦታው በመገኘት በቤተ ክርስቲያኑ ቃጠሎ ምክንያት በሞት የተለየውን ወጣት ቤተሰብን፣ ካህናቱን እና ምእመናኑን አጽናንተዋል።

ብፁዕነታቸውም "ልጃችን በሞት ቢለየንም በትንሣኤ እንደሚነሳ እናምናለን እጅግ የእግዚአብሔርን ፍቅር በሞቱ ገልጾ አሳይቶናል አልሞተም ሕያው ነው" በማለት ለቤተሰቦቹ ከአፅናኑ በኋላ ለካህናቱና ለምእመናኑ "አይዟችሁ ተባብረን ቤተክርስቲያኑን እንሰራዋለን" ሲሉ መክረው አስተምረው ተመልሰዋል ሲል የምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት ዘግቧል።

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!                                 +++                               አሳዛኝ ዜና!በምስራቅ ጎጃም ...
20/02/2023

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
+++
አሳዛኝ ዜና!

በምስራቅ ጎጃም ዞን ደጀን ወረዳ የታላቁ ሸብሸንጎ መድኃኒዓለም ገዳም ቤተ-ክርስቲያን ላይ የእሳት ቃጠሎ አደጋ ደርሶበታል፡፡

አደጋው የተፈጠረው በቀን 12/06/2015 ዓ.ም ከቀኑ 10 ሰዓት አካባቢ ሲሆን የቃጠሎው መንስኤ የኤልክትሪክ አደጋ መሆኑን የደጀን ወረዳ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ዘግቧል፡፡ አደጋውን ለመከላከል ህዘብ የተረባረበ ቢሆንም በቀላሉ መከላከል እንዳልተቻለ እና በአደጋው እሳት ለማጥፋት ሲሞክር የነበረ የአንድ ሰው ህይወት መጥፋቱ ታውቋል፡፡

ብፁዕ አቡነ ዲዮናስዮስ የታላቁ ዐብይ ጾምን አስመልክቶ ለአገልጋዮች አባታዊ                             መመሪያን ሰጡ።                                 ++...
20/02/2023

ብፁዕ አቡነ ዲዮናስዮስ የታላቁ ዐብይ ጾምን አስመልክቶ ለአገልጋዮች አባታዊ
መመሪያን ሰጡ።
+++
ብፁዕ አቡነ ዲዮናስዮስ የጀርመንና አካባቢው እንዲሁም የምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የዐብይ ጾምን መንፈሳዊ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ለአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች፣ ሰባኪያነ ወንጌል እንዲሁም ለሊቃነ መናብርት አባታዊ መመሪያ ሰጥተዋል።

ብፁዕነታቸው በዕለቱ እንደገለጹት ዐቢይ ጾም የመሻገርና የድል ጾም እንደመሆኑና አሁን ያለንበት ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያን ፈተና፣ ስደት፣ ልዩ ልዩ መከራዎችን ለመሻገር በይቅርታና በፍቅር በአንድነት ልብ በመጾም በመጸለይ መትጋ እንደሚገባ ገልጸዋል።

በተጨማሪም መንፈሳዊ አገልግሎቱ ዘመኑን በዋጀና በተቀላጠፈ ሁኔታ በሁሉም አጥቢያዎች ለምዕመናን ተደራሽ በማድረግ ከሀገረ ስብከቱ ጀምሮ በየደረጃው ለአሉት አስተዳደር ክትትልና ቁጥጥር በማድረግ በአገልግሎት በመሳተፍ መንፈሳዊ አገልግሎቱ እንዲከናወን ብፁዕነታቸው አሳስበዋል። መረጃው የምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት ነው።

ማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት

ዓለም አቀፍ የእርዳታ አሰባሳቢ ኮሚቴ በአስቸኳይ እንዲቋቋም ተወሰነ::                                           +++በዚህ ፈተና ጊዜ ቤተ ክርስቲያንን አናስደፍርም፣...
16/02/2023

ዓለም አቀፍ የእርዳታ አሰባሳቢ ኮሚቴ በአስቸኳይ እንዲቋቋም ተወሰነ::
+++
በዚህ ፈተና ጊዜ ቤተ ክርስቲያንን አናስደፍርም፣ የቤተ ክርስቲያንን ጥሪ ተቀብለን ቤተ ክርስቲያንን እናስከብራለን በማለት ውድ ሕይወታቸውን በመስዋዕትነት ላቀረቡ ሰማዕታት ቤተሰቦች፣ የአካልና የሥነ አእምሮ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖችንን ለመደገፍና የቤተ ክርስቲያን ተቋማትን መልሶ ለመገንባት ዓለም አቀፍ የእርዳታ አሰባሳቢ ኮሚቴ በአስቸኳይ እንዲቋቋም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ወስኗል።
Follw us on:
Twitter: https://twitter.com/GojjamEast
Telegram: https://t.me/EGDOTUMembers

የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት አስተዳደር ጉባኤ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይቶ ልዩ ልዩ ውሳኔዎችን አስተላለፈ ።**********************************የካቲት ፱ቀ...
16/02/2023

የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት አስተዳደር ጉባኤ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይቶ ልዩ ልዩ ውሳኔዎችን አስተላለፈ ።
**********************************
የካቲት ፱ቀን ፳ ፻ ፲ወ፭ ዓ.ም
""""""""""""""""""""""""""
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ
**************
በብፁዕ ከቡነ አብርሃም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅና በባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የሚመራው የጠቅላይ ቤተክህነት አስተዳደር ጉባዔ በወቅታዊ
የቤተክርስቲያን ጉዳዮች ዙሪያ ዛሬ የካቲት ፱ ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም ባደረገው መደበኛ ስብሰባ ልዩልዩ ውሳኔዎችን አስተላለፈ።
ጉባኤው በቤተክርስቲያናችን የተደረሰውን ስምምነት አስመልከቶ በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ የተሰጠውን ሰፊና ጥልቅ ማብራሪያ ካዳመጠ በኋላ በጉዳዩ ዙሪያ ሰፊ ውይይት በማድረግ የሚከተሉትን ውሳኔዎች አስተላልፏል።
፩ኛ በትላንትናው ዕለት በቅዱስ ሲኖዶስና ተወግዘው በተለዩት አባቶች መካከል የተደረሰውን ስምምነት በማድነቅ ተቀብሎታል። ለአፈጻጸሙም የሚጠበቅበትን ሁሉ ለማበረሰከት ቃል ገብቷል።
፪ኛ እርቀ ሰላሙ በአጭር ጊዜ እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን ወክለው ለተወያዩ ብፁዓን አባቶች፣
ተወግዘው ተለይተው ለነበሩ አባቶች ከሁሉም በላይ ለቤተክርስቲያን አንድነት ቅድሚያ በመስጠት ለፈጸሙት ታሪካዊ ስምምነት አድናቆቱንና ምስጋናውን አቅርቧል።
፫ኛ ቅዱስ ሲኖዶስ፣ቅዱስ ፓትርያርኩ ፣ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና ብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው
የቅድስት ቤተክርስቲያንን ሉአላዊ ክብርና ቀኖናዊ ሥርዓቱን ለማስጠበቅ የከፈሉትን መስዋዕትነት በማድነቅ ስምምነቱ የቤተክርስቲያናችንን መብት ባስከበረ መልኩኩ እንዲፈጸም በማድረጋቸው የተሰማውን ልባዊ ደስታ ከመግለጽ ጋር ስምምነቱን ተከትሎ ለሚከናወነው ተቋማዊ ዕድገት የበኩሉን አስተዋጽኦ ሁሉ በፍጺም ትጋት ለመፈጸም ዝግጁነቱን ገልጿል።።
፬ኛ ክቡር የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አቢይ አህመድ ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሀገር ናት በማለት የሚገልጹትን ሀቅ በማጠናከር እርቀ ሰላሙን ተከትሎ "ሙሽራው ክርስቶስ እስከሚመጣበት ድረስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አንድነቷ ተጠብቆ ይኖራል።" በማለት እርቀ ሰላሙ ከልብ እንዲከናወን ያደረጉትን ጥረት በማድነቅ ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ልባዊ ምስጋናውን አቅርቧል።
፭ኛ የቤተክርስቲያን ቀኖና አይጣስም አንድነቷ አይናጋም በማለት ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያንን ለማስከበር ክቡር መስዋዕትነት ለከፈላችሁ የዘመኑ ሰማዕታት፣ለዕስርና ለእንግልት የተዳረጋችሁ ኦርቶዶክሳዊያን፣ለግርፋትና ለአካል ጉዳት የተዳረጉ ልጆቻችን ሁሉ ክብርና ምስጋና ይገባቸዋል ያለው ጉባኤው ለሰማዕታት መንግስተ ሰማያትን እንዲያወርስልን፣የአካልና የሥነ አእምሮ ጉዳት ለደረሰባቸው ምሕረትን ለልዑል እግዚአብሔር ይስጥልን ወዳጅ ዘዶቻቸውንም ያጽናናልን፣የታሰሩትንም ያስታልን በማለት የታሰሩ የቤተክርስቲያን ልጆችን ለማስፈታት በሚደረገው ጥረት የሚጠበቅበትን ሁሉ ለማበርከት ቃል ገብቷል።
፮ኛ በዚህ ፈታኝ ወቅት የቤተክርስቲያንን ሉዓላዊነትና ቀኖናዊ አንዴነትን ለማስከበር በተደረገው ተጋድሎ ከቅድስት ቤተክርስቲያን ጎን በጽናት የቆማችሁ በየደረጃው የምትገኙ የአህጉረ ስብከት ሥራ አስኪያጆችና የጽሕፈት ቤት ሰራተኞች፣የቤተክርስቲያን አገልጋዮች፣ ማኅበራት፣ወጣት ልጆቻችን ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የመገናኛ ብዙሃን ድርጅት፣ለቤተክርስቲያናችን የሕዝብ ግንኙት መምሪያ፣ለማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት በሚዲያው ዘርፍ ለተሰማሩሩ ልዩልዩ የሚዲያ ተቋማት አክቲቪስቶችና ጸሐፊያን፣ ለሕግ ባለሙያዎችን ለሕግ አገልግሎት መምሪያ፣ ለሊቃውንት ጉባኤ፣ ለኦሬንታል አብያተ ክርስቲያን አሌክሳንደሪያ ኮፕቲክ፣ ሕንድ ፣ ሶርያ ፣ የሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ፣ ለሮም ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን፣ ለዓለም አብያተ ክርስቲያን ጉባኤ ሌሎች ዓለም አቀፍ ተቋማት፣የውጭ ጉዳይ መምሪያ፣ ለቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት ፣ መምህራንና ለሩሲያ ፖርላማ ተወካይ ቤተክርስቲያናችን ልባዊ ምስጋናዋን ታቀርባለች።
፯ኛ የቤተክርስቲያናችን ጉዳት ጉዳታችን ነው ከቤተክርስቲያናችን ጎን በጽናት እንቆማለን ፤ችግሩን የቤተክርስቲያንን መብትና ጥቅም በሚያስከብር መልኩ በሰላማዊ መንገድ እንፈታዋለን በማለት ሊገለጽ የማይችል ተጋድሎና እልህ አስጨራሽ ፈተናዎችን በጽናት አልፋችሁ ይህን ዕርቀ ሰላም እውን ያደረጋችሁ የመፍትሔ አፈላላጊና የሽምግልና ሥራ የሰራችሁ ባለሀብቶችና አትሌቶች ልፋታችሁ እንኳን ፍሬ አፍርቶ ለማየት በቃችሁ እንኳንም ደስ አላችሁ። በማለት ልባዊ ምስጋናችን እናቀርብላችኋለን።
፰ኛ በዚህ ፈተና ጊዜ ቤተክርስቲያንን አናስደፍርም፣
የቤተክርስቲያንን ጥሪ ተቀብለን ቤተክርስቲያንን እናስከብራለን በማለት ውድ ሕይወታቸውን በመስዋዕትነት ላቀረቡ ሰማዕታት ቤተሰቦች፣የአካልና የሥነ አእምሮ ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖችን ለመደገፍና የቤተክርስቲያን ተቋማትን መልሶ ለመገንባት ዓለም አቀፍ የርዳታ አሰባሳቢ ኮሚቴ በአስቸኳይ እንዲቋቋም ወስኗል።
፱ኛ የሚቋቋመው ዓለም አቀፍ የርዳታ አሰባሳቢ ኮሚቴ በተቋም ደረጃ በማዕከላዊ የቤተክርስቲያናችን አስተዳደር የሚቋቋም ብቻ እንዲሆን ይደረጋል።ከዚህ ውጪ በማኅበር፣በግልና በቡድን የሚቋቋም የርዳታ አሰባሳቢ ኮሚቴ ፍጹም ተቀባይነት የሌለው መሆኑ ታውቆ ድጋፍ ማድረግ የሚፈልጉ ወገኖች ሁሉ የቤተክርስቲያያችን ማዕከላዊ አስተዳደር
በሚያሳውቀው ሕጋዊ አካል ብቻ ድጋፍ እንዲያደርጉና መላው ኦርቶዶክሳዊያን ይህን የተቀደሰ ዓላማ ለማሳካት ርብርብ እንዲያደርጉ ጥሪ እያቀረብን ለዚሁ ዓላማ የሚውል የባንክ ሒሳብ በአገር ውስጥና በውጪ ሀገራት የሚከፈት ይሆናል።
፲ኛ በቤተክርስቲያናችን ታሪክም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ይህን የመሰለ ፈተና ገጥሞ በማያውቅበት ጊዜ ከቤተክርስቲያናችን ጎን በመቆም ለቀኖናና ለአንድነታችን መከበር በጽናት የቆማችሁ የእስልምናና የኘሮቴስታንት ዕምነት ተከታይ ወንድሞቻችን ሁሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሀገር መሆኗን በተግባር በሚያረጋግጥ ተጋድሎ በሀቅ ከጎናችን ስለቆማችሁ ልባዊ ምስጋናችንን በቅድስት ቤተክርስቲያናችን ስም እናቀርብላችኋለን።
፲ ፩ኛ በዚህ ፈታኝ ወቅት ጉዳት በደረሰባቸው አካባቢዎች የስብከተ ወንጌል ስምሪት ተደርጎ ተጎጂዎችን የመጽናናት ፣የማስተማርና የመጎብኘት ሥራ በአስቸኳይ እንዲካሔድ ለዚሀህም አስፈላጊው የቅድመ ዝግጅት ሥራ እንዲከናወን ወስኗል።
፲፪ኛ በዚህ የቤተክርስቲያንን መብትናጥቅም በማስከበር ሒደት ውስጥ የመንግስትን ሥልጣን መከታ በማድረግ በህገ ወጥ መንገድ ግድያ የፈጸሙ፣የአካል ጉዳት ያደረሱ፣ድብደባና ወከባ የፈጸሙ አካላትን ለህግ ተጠያቂነት ማቅረብ ለነገ የማይባል ተግባር በመሆኑ እነዚህን አካላት ለህግ ለማቅረብ የሚደረገውን ጥረት በመደገፍ ምዕመናንና ምዕመናት እንዲሁም ወጣት የቤተክርስቲያያችን ልጆቻችን አስፈላጊውን ድጋፍ እንድተታደርጉ ጥሪአችንን እያቀረብን
የቤተክርስቲያናችን የሕግ አገልግሎት መምሪያና ጠበቆቻችን ይህን ጉዳይ በልዩ ትኩረት በመከታተል
የህግ ተጠያቂነትን ተግባራዊ እንዲያደርጉ የአስተዳደር ጉባኤው የወሰነ ሲሆን ውሳኔውም ለቋሚ ሲኖዶስ በመሸኛ እንዲላክ ብሏል።
፲፫ኛ የተጀመረው የሰላም ሂደት ፍሬ አፍርቶ ተጨባጭ ውጤት እስከሚገኝና ሁሉም ነገር ወደ ቦታው እስከሚመለስ ድረስ ኦርቶዶክሳዊያን ልቻችን ሁሉ አስከ ሁን ድረስ ስተታደርጉት እንደቆያችሁት ሁሉ ቤተክርስቲያናችሁን በጽናት እንድትጠብቁ ጉባኤው አደራ ብሏል።
በመጨረሻም ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጃችን በዚህ ክፉ ወቅት በፍፁም ትጋት፣ብቃትን በተተተግባር ባመላከተው የአመራር ችሎታቸው በጥብአት የፈጸሙት ተጋድሎን ከልብ የምናደንቅ ሲሆን ለቀጣይ ሥራቸው መሳካት ከብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጃችን ጎን በመቆም ሌት ተቀን ለመስራት ፍጹም ዝግጁ መሆናችንን ስናረጋግጥ በፍጹም ደስታና ትህትና መሆኑን እንገልጻለን በማለት የዕለቱን ስብሰባ በጸሎት አጠናቋል።
የ/ኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
Follow us on
Twitter: https://twitter.com/GojjamEast
Telegram: https://t.me/EGDOTUMembers

ከአፍሪካ ትልቋ እና አንጋፋዋ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን✝️ ላይ እየተደረገ ካለው መከፋፈል ጀርባ ምን አለ? ሲል አልጀዚራ ሚዲያ የሰራውን                     ...
16/02/2023

ከአፍሪካ ትልቋ እና አንጋፋዋ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን✝️ ላይ እየተደረገ ካለው መከፋፈል ጀርባ ምን አለ? ሲል አልጀዚራ ሚዲያ የሰራውን
ዘገባ እነሆ፡፡
+++
"የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን✝️ ከአፍሪካ ትልቋ እና አንጋፋዋ ነች። ነገር ግን ባለፈው ወር ሦስት ጳጳሳት 'የኦሮሚያ እና ብሔረሰቦች ሲኖዶስ' ብለው የሰየሙትን የራሳቸውን ፓትርያርክ ካቋቋሙ በኋላ በመካከላቸው መለያየት ተፈጥሯል።
📌እርምጃው በአንዳንድ ክልሎች ለሳምንታት ሁከት፣ መከፋፈልና ብጥብጥ አስከትሏል።መንግስት ሰላማዊ ሰልፎችን ከልክሏል ማህበራዊ ሚዲያዎችን ገድቧል። ነገር ግን ውድቀቱ አሁንም በቤተክርስቲያኒቱ እና በሀገሪቱ ላይ አሉታዊ ተጽእኖ ሊኖረው ይችላል፡፡
ለመሆኑ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን✝️ ውስጥ ካለው መከፋፈል በስተጀርባ ያለው ምንድን ነው?" ይላል ዘገባው፡፡

Ethiopia's Orthodox Tewahedo Church is one of the largest and oldest in Africa.But there's been a split within its ranks after three Bishops formed their own...

Address

Debre Mark'os

Telephone

+251703454317

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የምሥ/ጎ/ሀ/ስ/ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ወጣቶች ኅብረት/ EGD Orthodox Tewhido Youth Union posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share