አቡቀለምሲስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

  • Home
  • Ethiopia
  • Debre Birhan
  • አቡቀለምሲስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

አቡቀለምሲስ  በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሚዲያ This is the Official page of Abukelemsis Media.

አቡቀለምሲስ ማለት “ረአየ ኅቡኣት አበ ራዕይ አበ ትንቢት” ማለት ሲሆን የተሰወረውን የተደበቀውን ፣የተከደነውን፣ የሚገልጥ/የሚያወጣ ማለት ነው ።

መሠራታዊ ዓለማው ፦በሀገረ ስብከታችን ብሎም በመላ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን የተሰወሩ ገዳማትን ፣የተደበቁ ሊቃውንትን፣ የተከደኑ ታሪኮችን ፣የተሸሸጉ ቅርሶችን ማውጣት እና የጎበጠውን አዲሱን ትውልድ በሥነ ምግባር በመቅረፅ ለቤተ ክርስቲያን ልሳን በመሆን የጥንታዊቷ እና የታሪካዊቷ ቤተ ክርስቲያናችን ተፅዕኖ ፈጣሪነት ይመለስ ዘንድ አይነተኛ ድምፅ መሆን ነው ።


ስለሆነም መረጃዎችን ከትክክለኛው ከቅድስት ቤተክርስቲያን ልሳን ለማግኘት ተከታዮን የዩቲዩብ፣ የፌስ ቡክ ፣ቴሌግ

ራም እና ኢንስታግራም አካውንታችን ሰብስክራይብ እና ላይክ በማድረግ የሚዲያችን ቤተሰብ ይሁኑ!! ሌሎችም ሰብስክራይብ እንዲያደርጉ መንፈሳዊ ሓላፊነትዎን ይወጡ፡፡

24/05/2026
"ዘለዓለማዊ ሕይወትን ለመውረስ ፣ ለበጎ ሥራ ስለተጠራችሁና ስማችሁ በመንግሥተ ሰማያት ስለተጻፈ ደስ ይበላችሁ"......የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ!!በእንሳ...
24/05/2026

"ዘለዓለማዊ ሕይወትን ለመውረስ ፣ ለበጎ ሥራ ስለተጠራችሁና ስማችሁ በመንግሥተ ሰማያት ስለተጻፈ ደስ ይበላችሁ"......
የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ!!

በእንሳሮ ወረዳ የሳላይሽ ደብረ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን ግንባታው ተጠናቆ ቅዳሴ ቤቱ በብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ ቡራኬ ተከበረ።

ግንቦት ፲፮ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም (አቡቀለምሲስ ሚዲያ ፤ ደብረ ብርሃን)
++++ +++++ +++++ ++++++ +++++ ++++

በእንሳሮ ወረዳ ለ9ኝ ዓመታት ሲገነባ የቆየው የሳላይሽ ደብረ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ-ምሕረት ቤተክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያና የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ተባርኮ ቅዳሴ ቤቱ ተከበረ።

በመርሐ ግብሩ ላይ ለታደሙ ሕዝበ ክርስቲያን ክቡር መጋቤ ሐዲስ ነቅዐ ጥበብ አባቡ የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ፣
"ልዑል ማደሪያውን ቀደሰ እግዚአብሔር በመካከሏ ነውና አትታወክም"ጨበሚል ኃይለ ቃል ትምህርተ ወንጌል ሰጥተዋል።

የእግዚአብሔርን ትእዛዝ አፍርሶ ከገነት ከመውጣቱ በፊት
ክብር ቢሉ ልጅነትን ቦታ ቢሉ ገነትን የተሰጠው የመጀመሪያው ክቡር ፍጥረት የሰው ልጅ ነው ብለዋል ክቡር ሥራ አስኪያጁ።

ሁለተኛዋ ልዑል ማደሪያውን ቀደሰ የተባለው እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም መኾኗን ገልጸው ሰማይና ምድር የማይወስኑት የተሸከመች ማደሪው ትኾን ዘንድ መርጧታል ከፍ ከፍም አድርጓታል።

እመቤታችን እነኋት እናትህ እነሆ ልጅሽ ብሎ ከጌታችን የተሰጠችን የመስቀሉ ሥር ውድ ስጦታ ናት ዛሬም በእናትነት ምልጃዋና በቃል ኪዳኗ የታመነ ምልጃዋ አይለየውም የእናትነት ፍቅሯም ይበዛለታል ብለዋል።

ሌላኛው የእግዚአብሔር ስም የሚመለክበት ወንዶች በ40 ቀን ሴቶች በ80 የክርስቶስን ልጅነት የምናገኝበፈባት ቅድስት ቤተክርስቲያን በመኾኗ እግዚአብሔር ፈቅዶላችሁ ይኽንን ቤተ መቅደስ በመሥራታችሁ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።

ዳዊት የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ለመሥራት ቢያቅድም እግዚአብሔር እንዳልፈቀደለት አንስተው ልጁ ሰሎሞን የሠራውን ቤተ መቅደስ እንደባረከለት አንስተው ዛሬ በብፁዕነታቸው የተባረከውን ቤተ መቅደስ እርስበርሳችሁ በወንድማማችነት ፍቅር በመተሳሰብ ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን የምትቀበሉበት ያድርግላችሁ ሲሉ ተናግረዋል።

የቅዱሳን ገዳማት መገኛ ነው ሳላይሽ የሚለውን ስያሜ ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ልምላሜዋን በሩቅ አይተው በመሔዳቸው ሳላይሽ ብለው እንዳወጡላት አንስተውቦታው ታሪካዊና የሊቃውንት መፍለቂያ ነው ብለዋል።

የሕንጻ ቤተ ክርስቲያኑን የሥራ ሪፖርት የሲያደብርና ዋዩ ወረዳ ቤተክህነት ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ካህናት ይባቤ ተቻለ የሕንጻ ቤተክርስቲያኑ ግንባታ ሚያዝያ 16 ቀን 2009 ዓ.ም የመሠረት
ድንጋይ እንደተቀመጠ አንስተዋል።

በዛሬው ዕለት በብፁዕነታቸው ተባርኮ ለምረቃ የበቃው ቤተ ክርስቲያን ከ41 ሚሊዮን 8 መቶ 95 ሺህ ብር በላይ ወጭ መፍጀቱንና አቶ ጸጋ አሳመረ የሕንጻ ቤተክርስቲያኑን የግንባታ ወጭ ከ አብዛኛውን በመሸፈን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን ገልጸዋል።

ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ ባስተላለፉት ቃለበረከት ይኽንን ቤተ ክርስቲያን በመሥራታችሁ ዘለዓለማዊ ሕይወትን ትወርሱ ዘንድ ለበጎ ሥራ ስለተጠራችሁና ስማችሁ በመንግሥተ ሰማያት ስለተጻፈ ደስ ይበላችሁ" ብለዋል።

ሰምሽን የጠራ ፣ ዝክርሽን ያዘከረ ቤተክርስቲያንሽን የሠራ ያሠራ እምርልሻለሁ ብሎ በገባላት ቃል ኪዳን መሠረት ስማችሁ በወርቅ ቀለም ተጽፎ ለታሪክና ለትውልድ ሲተላለፍ ይኖራል መልካም ሥራ የክፉ ቀን ስንቅ ስለኾነ ዋጋችሁ በሰማይ ታላቅ ነውም ብለዋል።

ይኽ ቦታ በራስ እምሩ ኃይለ ሥላሴ የተመሠረተ የፍቅርና የበረከት የታሪክና የገድል ቦታ ሲኾን እናንተም ነገር አላፊ ሆደ ሰፊ ኾናችሁ በፍቅርና በአንድነት በመተባበር የአባቶቻችሁ ፈልግ መከተል አለባችሁ ሲሉ መክረዋል።

ብፁዕነታቸው ቅድስት ቤተክርስቲያን በካህናት አገልግሎትና ጸሎት በምእመናን ፍቅርና ኅብረት ፣ በቅዱሳን ምልጃና ተራዳኢነት ሰማያዊና ምድራዊ አገልግሎቷ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

ፍቅረ እግዚአብሔር ፍቅረ ቢጽና ፍቅረ ሀገር የበዛላቸው ለቤተ ክርስቲያኑ ግንባታ አብዛኛውን ወጭ ለሸፈኑት ለአቶ ጸጋ አሳመረ (ወልደ መድኅን) ብፁዕነታቸው ምሥጋና አቅርበው ለ85 ዓመቱ የእድሜ ባለጸጋ ላእከ ሰላም ተብለው እንዲጠሩ የማእረግ ስም ሰጥተዋል።

በክብረ በዓሉ ላይ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ምክትል ሥራ አስኪያጅና ቁጥጥር ክፍል ሓላፊ ላእከ ኄራን በቀለ ፣ የብፁዕነታቸው አቡነ ቀሲስ መልአከ ስብሐት ቆሞስ አባ ወልደ ማርያም ዘጎርጎርዮስ ተገኝተዋል።

በተመሳሳይ የደነባ ማኅደረ ስብሐት በኣታ ለማርያም ገዳም አሰተዳዳሪ መልአከ ጽዮን አባ ኃይለ ሚካኤል በዳኔን ጨምሮ በርካታ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ፣ የአካባቢው ምእመናን ተገኝቸዋል።

መርሐ-ግብሩን የእንሳሮ ወረዳ ቤተክህነት ሥራ አስኪያጅ
መልአከ ሰላም ድረስልኝ ጌታነህ ያስተባበሩት ሲኾን ለሳላይሽ ደብረ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ-ምሕረት ቤተክርስቲያን ቀሪ ሥራዎች ማስፈጸሚያ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የአካውንት ቁጥር 1000231346701 ድጋፍ አድርጉልን ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።

Address

Debre Birhan
251

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አቡቀለምሲስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to አቡቀለምሲስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሚዲያ:

Share