የደብረ ምጥማቅ ጻድቃኔ ማርያም ገዳም ሚዲያ/Debre Mitmak Tsadqane Mariam monastery media

  • Home
  • Ethiopia
  • Debre Birhan
  • የደብረ ምጥማቅ ጻድቃኔ ማርያም ገዳም ሚዲያ/Debre Mitmak Tsadqane Mariam monastery media

የደብረ ምጥማቅ ጻድቃኔ ማርያም ገዳም ሚዲያ/Debre Mitmak Tsadqane Mariam monastery media ፈዋሿ የድሆች እና የምስኪኖች የህሙማን መጠጊያ ደብረ ምጥማቅ ጻድቃኔ ማርያም ገዳም ተአምራቷ ሁሉ የሚገለጥበት ይህ ፔጅ ነው

ዋዜማው በገዳማችን
29/05/2026

ዋዜማው በገዳማችን

ደብረ ምጥማቅ ፃድቃኔ ማርያም ገዳም
28/05/2026

ደብረ ምጥማቅ ፃድቃኔ ማርያም ገዳም

  በዚህ ሰአት ድምቅ ብላ ልጆቿን እየጠበቀች ትገኛለች
27/05/2026


በዚህ ሰአት
ድምቅ ብላ ልጆቿን እየጠበቀች ትገኛለች

26/05/2026

የመጨረሻው ምዝገባ

✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️

ታላቅ የክብረ በዓል ጉዞ ወደ
ደብረ ምጥማቅ ፃድቃኔ ማርያም ገዳም ምዝገባችንን በማጠናቀቅ ላይ ስለምንገኝ የመጨረሻው ምዝገባ ነገ ብቻ መሆኑን አውቃችሁ እንድትመዘገቡ ጥሪያችንን እናቀርባለን
የጉዞ መነሻ ሐሙስ ግንብት 20
መመለሻ አርብ ግንቦት 21 ከንግሥ መልስ
የጉዞ ዋጋ 1800
የጉዞ ስልክ ☎️ 0970101010
☎️ 0988101010

ቤተ ሳይዳ -የይቅርታ ደጅንጉሠ ነገሥት አጼ ዘርዓ ያዕቆብ ለኢትዮጵያ ካበረከቷቸው ታላላቅ በረከቶች ደብረ ምጥማቅ አንዷ ናት ። ገዳሟ በአጼ ይኩኖ አምላክ የተመሠረተች ብትሆንም የቤተ መንግሥ...
25/05/2026

ቤተ ሳይዳ -የይቅርታ ደጅ

ንጉሠ ነገሥት አጼ ዘርዓ ያዕቆብ ለኢትዮጵያ ካበረከቷቸው ታላላቅ በረከቶች ደብረ ምጥማቅ አንዷ ናት ።

ገዳሟ በአጼ ይኩኖ አምላክ የተመሠረተች ብትሆንም የቤተ መንግሥቱ የዕውቀት ማዕከልና የሀገር አቀፍ የቤተክርስቲያን ጉባኤያት መሰብሰቢያ የሆነችው ግን በዘርዓ ያዕቆብ ዘመነ መንግሥት ነው ። ንጉሡ በዘመናቸው በግብፅ የነበረው

#እስላማዊ መንግሥት ደብረ ምጥማቅ ዘግብጽን እንዳቃጠላት ሰምተው እጅግ ከማዘናቸው የተነሣ ለሐዘናቸው መጽናኛ ያችኛዋ እንዲትሠራ ጥረት ከማድረጋቸውም በላይ በሀገራችን በኢትዮጵያ ደብረ ምጥማቅ ማርያም ን ተክለዋል ገድመዋል ። «ጻድቃኔ» የሚለው በአጼ ናዖድ ምክንያት የተጨመረ ነው 🙏

ደብረ ምጥማቅ - በግብፅ ሀገር እመቤታችን በስደቷ ዘመን ካረፈችባቸው የከበሩ ቦታቸው መካከል አንዷ ናት ። በዚሁም ቦታ እመቤታችን ከግንቦት 21-25 ድረስ ላመኑትም ላላመኑትም ትገለጽላቸው እንደ ነበር የቤተክርስቲያን ታሪክ ይናገራል ።

ይሄንንም የእመቤታችን የመገለጥ በዓል ለመዘከር ቤተክርስቲያን ግንቦት 21 በደማቅ ሃይማኖታዊ ሥነ ሥርዓት የእመቤታችንን የመገለጥ በዓል ታከብራለች ።

አሁናዊ የገዳሟ መልክበርካታ አበው መነኮሳት ወመነኮሳይያት በአንድነት የሚኖሩባት ። የብዙ አባቶች ሊቃውንት ካህናት መኖሪያ

በዕውቀት ዘርም
►በዜማ
►በቅኔ
►በአቋቋም
►በቅዳሴ እንዲሁም በርካታ

➡የ፬ቱ ጉባኤያት ትርጓሜ መጻሕፍት ደቀመዛሙርት የሚገኙባት መካነ አዕምሮ ወልቡና ናት ገዳማችን ጻድቃኔ ማርያም
ይምጡ በዓለ ደብረ ምጥማቅን በደብረ ምጥማቅ ጻድቃኔ ማርያም ገዳም ያክብሩ

ሊቀ ሊቃውንት የንታ ነቢየ ልዑል አዳሙ የፈለገ ጥበብ አፄ ዘርዓ ያእቆብ መታሰብያ የ፬ቱ ጉባኤያት ምስክር መምህር
ቤተ ሳይዳ - የይቅርታ ደጅ
@ነቢየ ልዑል አዳሙ

 ለደጇ ታብቃችሁ
23/05/2026


ለደጇ ታብቃችሁ

"ትምህርትና ሱባኤ አንድ ናቸው ፤ ሁለቱም ጽናት ይጠይቃሉ".....ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ!!ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ የደብረ ብርሃን ቅዱስ ባስልዮስን ደቀ...
22/05/2026

"ትምህርትና ሱባኤ አንድ ናቸው ፤ ሁለቱም ጽናት ይጠይቃሉ".....ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ!!

ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ የደብረ ብርሃን ቅዱስ ባስልዮስን ደቀ መዛሙርት ተግተውና ጠንክረው በመማር ለቅድስት ቤተክርስቲያን ሐዋርያዊ አገልገሎት መዘጋጀት እንዳለባቸው አስገነዘቡ።

ግንቦት ፲፬ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም (አቡቀለምሲስ ሚዲያ ፤ ደብረ ብርሃን)
++++ +++++ +++++ ++++++ +++++ +++++

ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያና የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብርሃን ቅዱስ ባስልዮስን ደቀ መዛሙርት ተግተውና ጠንክረው በመማር ለቅድስት ቤተክርስቲያን ሐዋርያዊ አገልገሎት መዘጋጀት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

ብፁዕነታቸው እናንተ ደቀ መዛሙርት በትምህርት ቆይታችሁ ለታሪካዊቷ ፣ ለትናንቷ ፣ ለትናንቷና ለነገይቱም ለቅድስት ቤተክርስቲያን ተስፋ በመሆናችሁ እድለኞች ናችሁና እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።

ቅዱሳን ሰማያዊ ክብርና ዋጋ ለማግኘት በየዋሻውና በየፍርኩታ የደከሙበትን በረከት በመቀበል አልጫውን ዓለም ለማጣፈጥ የተዘጋጃችሁ የነገዋ ቤተክርስቲያን ጨው ናችሁና ጠንክሩ ብለው መክረዋል።

ትምህርትና ሱባኤ አንድ ናቸው ፤ ሁለቱም ጽናት ይጠይቃሉና ከሁሉ አስቀድማችሁ ለተሰማራችሁበት ዓላማችሁ መሳካት የበኩላችሁን አስተዋጽኦ ማበርከት አለባችሁ ብለዋል።

በመርሐ-ግብሩ ላይ የኮሌጁ የተለያየ ዲፓርትመንት ሓላፊዎች እና የአስተዳደር ሠራተኞችና የኮሌጁ ደቀ መዛሙርት ተገኝተዋል።

ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ በብልጋ ከተማ በቱለፋ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤልሥር ለሚገነባው የኤግዱ ተራራ አበነ ተክለ ሃይማኖት እና ቅዱስ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን የመሠረት ድንጋይ አስቀመጡ።...
20/05/2026

ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ በብልጋ ከተማ በቱለፋ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤልሥር ለሚገነባው የኤግዱ ተራራ አበነ ተክለ ሃይማኖት እና ቅዱስ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን የመሠረት ድንጋይ አስቀመጡ።

ግንቦት ፲፪ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም (አቡቀለምሲስ ሚዲያ ፤ ደብረ ብርሃን)
++++ +++++ +++++ ++++++ +++++ +++++

ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያና የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በብልጋ ከተማ በቱለፋ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤልሥር ለሚገነባው የኤግዱ ተራራ አቡነ ተክለ ሃይማኖት እና ቅዱስ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን የመሠረት ድንጋይ አስምጠዋል።

በመርሐ ግብሩ ላይ የሀገረ ስብከቱ ምክትል ሥራ አስኪያጅና ቁጥጥር ክፍል ሓላፊ ላእከ ኄራን በቀለ ፣ የከሰም ወረዳ ቤተክህነት ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ካህናት ኤርምያስ አስደንግጥ ተገኝተዋል።

በተመሳሳይ የወረዳው ጸሐፊ መምህር ኤርምያስ ፣ የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ምሕረት ተሾመ ስለሺ እንዲሁም ሊቃውንተ ቤተክርስቲያንና ምእመናን ተገኝተዋል።

ግንቦት ወር እና ደብረ ምጥማቅ በቀድሞ የሀገራችን አጠራር ሸዋ ክፍለ ሀገር ተጉለት እና ቡልጋ አውራጃ በአሁኑ ሰሜን ሸዋ ዞን ሞጃና ወደራ ወረዳ ልዩ ስሙ   ከሀገራችን ዋና መዲና አዲስ አበ...
19/05/2026

ግንቦት ወር እና ደብረ ምጥማቅ
በቀድሞ የሀገራችን አጠራር ሸዋ ክፍለ ሀገር ተጉለት እና ቡልጋ አውራጃ በአሁኑ ሰሜን ሸዋ ዞን ሞጃና ወደራ ወረዳ ልዩ ስሙ ከሀገራችን ዋና መዲና አዲስ አበባ በ200 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ከዞኑ ዋና ከተማ ደብረ ብርሃን 80 ኪ.ሜ የሀገራችንን ሰሜናዊውን ክፍል የሚያቆራርጠውን ዋና አስፓልት ይዘው ጣርማበር ከተማ ድረስ በመጓዝ በመቀጠልም ወደ ግራ በመታጠፍ 20 ኪ.ሜ ድረስ በመጓዝ ግርማዋ ከሩቅ የሚጣራ ጉልላቷ የአኩስም ሕንፃ ቤተክርስቲያንን ቅርጽ የያዘ አምሳለ ኢየሩሳሌም ደብረ ምጥማቅ ፃድቃኔ ማርያም ገዳምን ያገኟታል ታድያ በግንቦት ወር ሲመጡ የአካባቢው ድባብ ይለወጣል ወትሮ በጸጥታ ይታወቅ የነበረው አካባቢ ትንሹም ትልቁም የእመቤታችንን እንግዶች ለመቀበል ደፋ ቀና ሲል ይመለከታሉ እመ በረከት የሆነችው ገዳማችንም የምትናፍቃቸው የሚናፍቋት ልጆቿ ከአራቱም አቅጣጫ ይመጣሉና ማረፍያቸውን ታዘጋጃለች ለነፍሳቸው የሚገባውን የወንጌል ድግስ ታሰናዳለች የገዳሙ መናንያን ልጆቻቸውን ለመቀበል ወገባቸውን አስረው ይጠብቃሉ እናም በመንፈሳዊ ሕይወት ውስጥ እጅግ በጣም ውድ የሆነውን ጊዜ "በዓለ ደብረ ምጥማቅ " ን በደብረ ምጥማቅ ፃድቃኔ ማርያም ገዳም ማሳለፍ ማለት እመቤታችን በደብረ ምጥማቅ ጉልላት ላይ ተገልጣ በረከተ ሥጋ በረከተ ነፍስ የምትሰጥበትን በረከት መካፈል መቻል መታደልም መመረጥም ነውና ይህንን ልዩ እና ውድ ቀን በደጇ ተገኝተን እንድናከብር በአማላጅነቷ ታግዘን

✍️ወደ ገዳሙ ለመምጣት ከአዲስ አበባ ላምበረት መናሀርያ በቀጥታ ፃድቃኔ ማርያም ድረስ ስላለ በየትኛውም ቀን መምጣት ይችላሉ

በቅንነት መልእክቱን ሼር ያድርጉት

17/05/2026

+. እግዚአብሔር መንፈስ ነው .+


የመንፈስ ቀላል ትርጕሙ «በአካላዊነት ጎልቶ ለዐይን የማይታይ» ፣ «ከመታየት በላይ» ማለት ነው። ቃሉ ወደ አካለ እግዚአብሔር ተጠግቶ ሲነገር የበለጠ ሐሳቡን ከፍ አድርጎ ይገልጣል። እግዚአብሔር የር’ቀ’ቶች ኹሉ መነሻ ስለኾነ - አእምሮአችን ከሚያሰበው ር’ቀ’ት በላይ ረቂቅ ነው። መንፈስ የሚለውም ራሱ የእኛን አስተውሎት/መረዳት ታሳቢ ተደርጎ የተነገረ እንጂ እግዚአብሔርን በኾነው ልክ የሚገልጠው ኾኖ አይደለም። እግዚአብሔር ከምንም - ስለ እሱ ከምናስበውም ከምንናገረውምም በላይ ነው!! እግዚአብሔርን በኾነው ልክ የሚገልጠው እግዚአብሔር ብቻ ነው ፤ እግዚአብሔር በእግዚአብሔርነቱ የሚገለጥለትም አካል የተገለጠውን ለመረዳት እግዚአብሔር መኾን አለበት ፤ እግዚአብሔር የሚገልጠውን እግዚአብሔርነት ማወቅ ለማንም አልተሰጠም። ለማንም አይቻልምና።

ስለ እግዚአብሔር ያለን ዕውቀት እኛ ስለ እሱ ማወቅ የቻልነው መጠን ነው ፤ ይኽም ቢኾን በራሳችን የመጣ ሳይኾን ተገልጦልን ያወቅነው ነው። ያወቅነውም እግዚአብሔርን የማወቃችን ድንበር አይደለም። ከእግዚአብሔር መልካምነት ጋር - ነፍስ በንጽሕና ወደ እሱ በመቅረብ ስትተባበር ፥ ፈቃደ ግብረ ባሕርያቱን ስትሳተፍ እየተገለጠላት የሚኼደው ዕውቀቷ የነበራትን ዕውቀት የሚበልጥ ይኾናል። የዕውቀቷ ፍጻሜም የነበሯት ዕውቀቶች ተቋጭተው ከእነሱ በበለጠ አለማወቅ በ’መ’ያ’ዝ ይኾናል!! የነፍስ ዕውቀት ስለ እግዚአብሔር ምንም አለማወቅ ውስጥ በመግባት ይፈጸማል!! ከእሱ ጋር መኖሯ በቂዋ ስለሚኾን የማወቅ ጥማቷም ይቆረጣል!!

«እግዚአብሔር መንፈስ ነው» የዚኽ ሐሳብ ተሸካሚ ቃል ነው። መንፈስ ምንድነው!? እንደ እውነታው የዚኽን ቃል ደረቅ መዝገበ ቃላዊ ፍቺን ከማስቀመጥ ውጪ ፥ ሐሳቡን በኾነው ልክ ለልብ ማስረዳት አይቻለም ፤ መንፈስ የሚለው ሐሳብ ላይ በሰው ዘንድ ያ’ለ አለመረዳት አ’ለ - «ያ አለመረዳት እግዚአብሔር በነፍሳችን ውስጥ ያለው ቦታ ነው» ለማለት «እግዚአብሔር መንፈስ ነው» ተብሏል።

❝.. ወአልቦ ዘየአምሮ ለወልድ ዘእንበለ አብ ፤ ወለአብኒ አልቦ ዘየአምሮ ዘእንበለ ወልድ - ከአብ በቀር ወልድን የሚያውቅ የለም፥ ከወልድም በቀር አብን የሚያውቅ የለም❞ [ማቴዎስ ፲፩፥፳፯]። ማወቅ ከተነገረስ የአብ ዕውቀት/መታወቅ ወልድ ላይ ፥ የወልድ ዕውቀትም/መታወቅ አብ ላይ ታውቆ ይቀራል። «ወለዘፈቀደ ወልድ ይከሥት ሎቱ - ወልድ ሊገልጥለት ከሚፈቅድ በቀር / ወልድ ሊገልጽለት ለወደደው ይገልጥለታል» የሚለው ቀጣይ ንባብ - በአሚን አኹን ለእኛ የተገለጠው ፥ እኛነታችን ስለ እግዚአብሔር ማወቅ የቻለው የዕውቀት መጠን ነው እንጂ አብ ወልድን ፥ ወልድም አብን የሚያውቅበት ማወቅ ለእኛ ተሰጥቷል ማለት አይደለም። አብ አብነቱ ወልድ ላይ ፥ ወልድም ወልድነቱ አብ ላይ የቀረ ነው!!

አካል ከሕሊናት ኹሉ ለራቀ ለአምላካችን ለልዑል እግዚአብሔር ሲነገር ፥ እኒኹ ኹሉ ታሳቢ ተደርገው ነው። የእግዚአብሔር አካል ሲባል ወደ ሕሊናችን የሚመጣው ሥዕል የእኛ መሰሉ ቅርጽ ከኾነ የእግዚአብሔርን እግዚአብሔርነት መዘንጋት ነው የሚኾነው። እንደሚታወቀው መገለጦች ኹሉ የተሰጡት ለሰዎች ነው ፤ እነዚያ መገለጦች ደግሞ በሰው መረዳት ልክ የኾኑ ናቸው ፤ ለእኛ ተመጥነው የተሰጡ መገለጦችን ያለቀላቸው የእግዚአብሔር ውክያ አድርጎ መውሰድ ይኽን የምሥጢር ድንበር መዝለል ነው።

አንድ እና ኹለት የለውም እግዚአብሔር አካላዊ ነው። በኹኔታዎች [በተፈጣሪያኑ ውስጥ ያለ ፥ እነሱም ጸንተው ያሉበት] ውጥረት እና ጽምረት የሚመላለስ/ተገላጭ ኀይልም [በእሱ የሚኾን ቢኾኖም] አይደለም ፤ አማን በአማን እግዚአብሔር አካላዊ ነው። ሰው ኹነን አካላዊነትን ከእኛ አካልነት ውጪ መረዳት አይቻለንምና ፥ የእግዚአብሔር አካል በእኛ አካል አንጻር ተገልጿል። ይኽ ማለት ቀጥታ የእኛ አካል የእግዚአብሔር አካል ተመስያ ነው ማለት አይደለም። አካለ እግዚአብሔር በእኛ ሕሊና ከሚሣለው አካል የወጣ ፥ በማንም የማይመረመር የአካሎች ኹሉ ፍጻሜ የኾነ ፍጹም አካል ነው።

በቅዱሳት መጻሕፍት ስለ እግዚአብሔር አካል የተነገሩ ምንባባት በዚኽ አግባብ የምንረዳቸው ናቸው። እግዚአብሔር ከተጻፈው ከሚጻፈው ፥ ከታሰበው ከሚታሰበው ፥ ከተነገረው ከሚነገረው ኹሉ በላይ ነው። እንደ እግዚአብሔርነቱ ማንም ምንም ማለት አይችልም ነበር ፤ ግን ከቸርነቱ የተነሣ ለኹለቱ [መላእክት እና ሰዎች] ፍጡራን ስለ እሱ ሊሉ በሚችሉበት መጠን ፣ ሊረዱት በሚችሉበት መጠን ማንነቱን ገልጦላቸዋል። አኹን ያለን መገለጥ/መረዳት ስለ እግዚአብሔር እኛ ልናውቀው የቻልነው መጠን ነው።

-------------------------------
📜ያገምሩ ኵሎ ወአልቦ መኑሂ ዘያገምሮሙ ብርሃናት ቀዳማውያት ፤ ዘኢየአምር መኑሂ ዘከመ እፎ ውእቱ ክዋኔሁ ፤ ወኢያገምሮሙ ልቡና ፤ ወኢያስተጋብኦሙ ሕሊና ፤ ይሬእዩ ኵሎ ፥ ወኢያስተርእዩ ፤ ወአልቦ ዘይትማሰሎሙ ፤ ወይትዔረዮሙ ሕያዋን እሙንቱ እለ ኢይመውቱ ፤ ወኢይትዌለጡ ፤ ርኁቃን እምነ ኵሉ ወቅሩባን ለኵሉ ለባውያን ፤ ወማእምራን ፈድፋደ እምነ ኵሉ ፤ ኢፍጡራን ፤ ወኢይትረከቡ በሐልዮ ወበለብዎ ፤ ርኁቃን ወልዑላን እሙንቱ ፤ አምጻእያኒሆሙ ለኵሉሙ ፍጡራን እም ኀበ ኢሀልዎ ኀበ ሀልዎ፨
☞ኹሉን ይወስናሉ እንጂ የሚወስናቸው ምንም ምን የለም ፤ ኹኔታቸው እንዴት እንደኾነ ማንም የማያውቅ በቅድምና የነበሩ ብርሃናት ናቸው። ልቡና አይመረምራቸውም ፤ ሕሊና አይወስናቸውም ፤ ኹሉን ያያሉ እነርሱ ግን አይታዩም ፤ የሚመስላቸው የሚተካከላቸው የለም ፤ የማይሞቱ የማይለወጡ ሕያዋን ናቸው። ከኹሉ [መረዳህ] የራቁ ለኹሉ [በመግቦት/በሃይማኖት] የቀረቡ ናቸው ፤ ከኹሉ ይልቅ ዕውቀት የባሕርያቸው ነው። ያልተፈጠሩ ናቸው ፤ በማሰብ በመመርመር አይገኙም ፤ ከ’መ’መ’ርመር የራቁ የረቀቁ ናቸውና። ፍጥረታትን ኹሉ ካለመኖር ወደ መኖርያመጡ እነርሱ ናቸው፨
📜➬ ሃይማኖተ አበው ዘሱንትዩ ፻፱ ፥ ፫

ምሥጢሬ አይታወቅም ፤ ነገር ግን የአንተ አእምሮ ሊቀበለው የሚችለውን ምሥጢር አነግርሃለኹ።
➬ መጽሐፈ ቀሌምንጦስ

“ ”
— የዮሐንስ ወንጌል ፬፥፳፬ / 4፥24
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
©️ጉባኤ ደብረ ምጥማቅ

ታላቅ መንፈሳዊ ጉዞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ዱ አምላክ አሜን በየዓመቱ በታላቅ ድምቀት የሚከበረው በዓለ ደብረ ምጥማቅ በታላቋ ፣ጥንታዊቷ የበረከት የፈውስ አምባ ደብረ ምጥማቅ ፃ...
16/05/2026

ታላቅ መንፈሳዊ ጉዞ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ዱ አምላክ አሜን
በየዓመቱ በታላቅ ድምቀት የሚከበረው

በዓለ ደብረ ምጥማቅ በታላቋ ፣ጥንታዊቷ የበረከት የፈውስ አምባ ደብረ ምጥማቅ ፃድቃኔ ማርያም ገዳም የ2018 ዓ.ም ክብረ በዓል ለማክበር ወደ ገዳማችን የሚመጡ ውድ ልጆቿን ለመቀበል በዝግጅት ላይ ትግኛለች ስለሆነም በጉዞ ለመምጣት ለምትሹ
የጉዞ መነሻ ቦታ መገናኛ
ፒያሳ
እስጢፋኖስ
ጣፎ አደባባይ
☎️ 0910138955
ቀድመው ይደውሉ

Address

Debre Birhan

Telephone

+251973006568

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የደብረ ምጥማቅ ጻድቃኔ ማርያም ገዳም ሚዲያ/Debre Mitmak Tsadqane Mariam monastery media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share