የደ/ብርሃን ቅ/ሥላሴ ወዳጅ

የደ/ብርሃን ቅ/ሥላሴ  ወዳጅ በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት የደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ወዳጅ ገጽ ነው

✨"ጽዮን" ✨ማለት "ጸወን - አምባ - መጠጊያ" ማለት ነው:: ጽዮን የሚለው ስም በቁሙ ለቅዱስ ዳዊት ተራራና ለኪዳኑ ጽላት ሲያገለግል በትንቢታዊ ምሥጢሩ ግን ለድንግል ማርያም፣ ለቤተ ክርስ...
30/11/2025

✨"ጽዮን" ✨ማለት "ጸወን - አምባ - መጠጊያ" ማለት ነው:: ጽዮን የሚለው ስም በቁሙ ለቅዱስ ዳዊት ተራራና ለኪዳኑ ጽላት ሲያገለግል በትንቢታዊ ምሥጢሩ ግን ለድንግል ማርያም፣ ለቤተ ክርስቲያንና ለዘለዓለማዊት ርስት ያገለግላል::

እንኳን አደረሳችሁ !
መልካም በዓል !🙏

ህዳር 21                +++ ጽዮን ማርያም+++    "ጽዮን" ማለት "ጸወን - አምባ - መጠጊያ" ማለት ነው። አንድም በምሥጢሩ "ማሕደረ አምላክ" ማለት ነው። ጽዮን የሚለው ስም...
29/11/2025

ህዳር 21
+++ ጽዮን ማርያም+++
"ጽዮን" ማለት "ጸወን - አምባ - መጠጊያ" ማለት ነው። አንድም በምሥጢሩ "ማሕደረ አምላክ" ማለት ነው። ጽዮን የሚለው ስም በቁሙ ለቅዱስ ዳዊት ተራራ : ለኪዳኑ ደግሞ ጽላት ሆኖ ሲያገለግል ትንቢታዊ ምሥጢሩ ግን ለድንግል ማርያም፣ ለቤተ ክርስቲያንና ለዘላለማዊት ርስት ያገለግላል።
እግዚአብሔር ከዘመነ አበው በኋላ በጊዜው ለእስራኤላውያን ክብር፣ ሞገስ፣ አምባ የምትሆናቸውን ታቦተ ጽዮንን በቅዱስ ሙሴ አማካኝነት ሰጥቷቸዋል። (ዘጸ. ፴፩፥፲፰)
ከዚያም ለአምስት መቶ ዓመታት ከእነርሱ ጋር በመሆኗ በፈጣሪና በእነርሱ መካከል ድልድይ ሆና ኖራለች።
ከዚያም ባለቤቱ መድኃኔዓለም ሲፈቅድ በዘመነ ሳባ በቀዳማዊ ምኒልክ (እብነ መለክ - እብነ ሐኪም) አማካኝነት ወደ ኢትዮጵያ መጥታለች። እነሆ በሃገራችን የሦስት ሺህ ዓመት ቆይታዋን ልትደፍን የቀራት ጥቂት ዓመታት ብቻ ናቸው። ጌታ እንደ ፈቀደ ቅዱስ መስቀሉንና ታቦተ ጽዮንን ይዘን ይሔው በቸርነቱ እንኖራለን።
በነገራችን ላይ በዚህ ዘመን ታቦተ ጽዮንን ለመውሰድና ለመስረቅ የሚፈልጉ ብዙ ቀሳጢዎች እንዳሉ እናውቃለን። ነገር ግን አያስጨምቀንም። ምክንያቱም የመጣችውም የምትጠበቀውም በፈቃደ እግዚአብሔር ነውና እንጸልያለን እንጂ አንጨነቅም። በተለያየ ወሬም ራሳችንን ውጥረት ውስጥ አንከትም። ባለቤቱ እንድትሔድ ከፈቀደ ደግሞ ማንም ጉልበተኛ አያስቀራትም።
ታቦተ ጽዮን ብዙ ጊዜ "ጽላተ ኪዳን፣ ታቦተ ሕጉ" እየተባለች ትጠራለች። "ጽሌ" ማለት "ሰሌዳ" እንደ ማለት ሲሆን "ጽላት" ደግሞ በብዙ ቁጥር ነው። "ኪዳን" ደግሞ በፈጣሪና በሰው ልጆች መካከል ያለ "ውል - ስምምነት" ነው።
"ታቦት" ማለት "ማሕደር - ማደሪያ" እንደ ማለት ነው። ሕጉ የተጻፈባቸውን ሰሌዳ "ጽላት" ስንላቸው የጽላቱ ማደሪያ ደግሞ "ታቦት" ይባላል። ጽላት (ታቦትን) ያመጣ ፈጣሪ ነው። በሐዲስ ኪዳንም ምሥጢርና ሐተታ ቢኖረውም ሁለት ቦታ ላይ ስለ ታቦት ተጠቅሶ እናገኘዋለን። (፪ቆሮ. ፮፥፲፮ ፣ ራእይ. ፲፩፥፲፱)
++ ኅዳር 21 የምናከብርበት ዋናው ዓለማ ++
፩ኛ. ታቦተ ጽዮን (ጽላተ ኪዳን)- ለሊቀ ነቢያት ቅዱስ ሙሴ መሰጠቷን እናስባለን። ይህ ሲሆንም ቅዱስ ሙሴ አርባ መዓልት አርባ ሌሊት ጾሞ እንደ ተቀበለ እያሰብን ማለት ነው።
(ዘጸ. ፴፩፥፲፰ ፣ ዘዳ. ፱፥፲፱)
፪ኛ. በሊቀ ካህኑ ኤሊ ዘመን ታቦተ ጽዮን በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ በአሕዛብ (ኢሎፍላውያን) እጅ ተማርካለች። ነገር ግን ዳጐን የሚባለውን የአህዛብ ፃኦት የሰባበረችበትን ቀን እናስታውሳለን ።
(፩ሳሙ. ፭፥፩)
፫ኛ. በዘመነ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት በአሚናዳብ ሠረገላ ሁና ከአቢዳራ ቤት ስትመጣ ቅዱሱ ንጉሥ በታላቅ ሐሴት በፊቷ ዘመረ፤ አገለገለ። ምድራዊ ክብሩን እስኪረሳ ድረስ ለታቦተ አምላክ ተቀኘላት። በዚህም ምክንያት ሚስቱ ሜልኮል ንቃው ማኅጸኗ ተዘግቷል እስክትሞትም ደረስ አልወለደችም ነበር እንዲል።
(፩ዜና. ፲፭፥፳፭)
ሊቃውንትም ይህን ሲያመሰጥሩ "ቅድስትድንግል ማርያምን በትንቢት መነጽር ተመልክተው እንዲህ ብለዋል፦
"ሰላም ለኪ ማርያም እምነ
ዘሰመይናኪ ጸወነ
ሶበ እምርሑቅ ርእየ ዘጽላሎትኪ ስነ
ለቢሶ ዳዊት ልብሰ ክብር ዘየኀይድ ዓይነ
ቅድመ ታቦተ ሕግ ኃለየ ወዓዲ ዘፈነ እንዲል ።
፬ኛ. በቅዱስ ሰሎሞን(መፍቀሬ ጥበብ) ዘመንም ግሩም የሆነ ቤተ መቅደስ ተሰርቶላት ስትገባ ታላቅ ሐሴት ሆኖ ነበር። እግዚአብሔርም በደመና ወርዶ ንጉሱን አነጋግሮ ነበር (፪ኛ ዜና ፭፥፩ ፩ኛ ነገ ፰*፩)።
፭ኛ. በዚያ ዘመን ንጉስ ሚኒሊክ (ዕብነ ሐኪም) ታቦተ ፅዮንን ይዞ ገብቷል።
፮ኛ. በዘመነ አፄ ባዜን (፬ኛው ክ.ዘ.መ) አማናዊት ጽዮን ቅድስት ድንግል ማርያም ወደ አክሱም ፅዮን በስደት መጥታ ገብታለች። በዚህም ጊዜ ሁለቱ ጺዮኖች (ታቦተ ፅዮን እና ፅዮን ማርያም) ሲገናኙ አክሱም ከክብራቸው የተነሳ በብርሃን አሸብርቃለች።
፯ኛ. በ፬ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በአብርሃ ወአፅብሓ ዘመን አስራ ሁለት መቅደስ ያሏትን ቤተ መቅደስ ለእመብርሃን ሰርተዋል: በጌታችንም ተቀድሷል።
፰ኛ. በአረመኔዋና የቤተ ክርስቲያን ቀንደኛ አውዳሚ በሆመችው በዮዲት ጉዲት ቤተ መቅደሷ ስትፈርስ ወደ ዝዋይ ትሰደድ ነበር በኋላም ቤተ መቅደሷ ሲሰራ ተመልሳ እንደመጠችም በኅዳር ፳፩ ቀን ትከበር ነበር።
እንግዲህ ኅዳር 21 ቀን እነዚህን ምክንያቶች እያሰብን በደማቅ ሁኔታ እናከብራለን።
እንግዲህ ከፍጡራን በላይ ከፈጣሪ በታች የሆነች እናታችንን ስናስብ "ቅድስት" ማለታችን እንደሌሎች ቅዱስን በእኩል ደረጃ እያሰብን ሳይሆን ትርጉሙ ይለያል፣ የእርሷም ቅድስና ልዬ ነውና፦ ቅድስተ ቅዱሳን : ንፅሕተ ንፁሓን: ብርክት እምብሩካን: ኅሪት እምኅሩያን እያልን እንጠራታለን።
ወዳጄ! "ስለ ፅዮን ዝም አንልም" እንዲል ዳዊት በመዝሙሩ እኛ የምንጮኸው ለዝና አልያም ደግሞ መናፍቃንን ለማናደድ የሚመስላቸው ፀረ ተዋህዶ የሆኑ ተዋስያንና ጥገኞች፣ ባህላቸውን እንኳ የማያውቁ ነገር ግን እኛን እየታከኩ ልደት በለው ትንሳኤ ያከብሩና ዞረው ደግሞ እኛን ለመተቸት ይመጣሉ። ክብርና ምስጋና ለመድኃኔዓለም ይሁንና ከአስርቱ ትዕዛዛት አንዱ "እናት እና አባትህን አክብር" ብሎ ትዕዛዝ የሰጠ አምላክ አሁን ደግሞ የነገራት ሁሉ በኩር የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱ ንፅሕተ ንፁሓን: ቅድስት: ንዑድ ክብርት የሆነች እናቱን አክብሮ እንድናከብራት "ለፅዮን የማይገዛ ትውልድ ይጠፋል " ብሎ ለማያከብሯት በማስጠንቀቅም ለእኛ ለምናከብራት ደግሞ እነሆ ትውልድ ሁሉ በፊትሽ ይማልላሉ (ሰአሊለነ ቅድስት እያሉ ይጮሃሉ) ብሎ በግልፅ አስቀምጦልናል።
አሜን ማርያም ሆይ! ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይሉሻል!!!
፨፨እንኳን ለዓመቱ ህዳር ፅዮን በሰላም አደረሳቹህ መልካም በዓል ይሁንላቹህ የዓመት ሰው ይበለን!!!

   ስምኅዳር ዐሥራ ሁለት በዚች ቀን የመላእክት አለቃ   የበዓሉ መታሰቢያ ነው፣  እንደ የተራዳበት ቀን ነው፣     ተዓምር ያደረገበት ነው፣   መታሰቢያ ነው፣ የኢትዮጵያ ንጉሥ   የዕረፍ...
21/11/2025



ስም
ኅዳር ዐሥራ ሁለት በዚች ቀን የመላእክት አለቃ የበዓሉ መታሰቢያ ነው፣
እንደ የተራዳበት ቀን ነው፣ ተዓምር ያደረገበት ነው፣ መታሰቢያ ነው፣ የኢትዮጵያ ንጉሥ የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው፣ የሊቀ ጳጳሳት እረፍቱ ነው።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞



ኅዳር ዐሥራ ሁለት በዚች ቀን ለሰው ወገን የሚያዝንና የሚራራ በ #እግዚአብሔር ጌትነት ዙፋን ፊት ሁልጊዜ በመቆም ለፍጥረቱ ሁሉ የሚማልድ የመላእክት አለቃ በሰማያትም ለሚኖሩ ኃይሎች ሁሉ አለቃቸው ለሆነ ለ የበዓሉ መታሰቢያ ነው።

“ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ።” ዳን 10፡13

👉🏻 #ሚካኤል ማለት 'መኑ ከመ አምላክ' እንደ እግዚአብሔር ያለ ማነው የሚል ትርጉም አለው። ይህም እንደ እግዚአብሔር ያለ በባሕርይው ቅዱስ የሆነ ፣ እንደ እግዚአብሔር ያለ ንጹሐ ባሕርይ ፣ እንደ እግዚአብሔር ያለ ፍጹም ማነው የሚል ነው። ቅድስና ፣ ንጽሕና እና ፍጹምነት የባሕርይ ገንዘቡ የሆነ ከእግዚአብሔር በቀር የለምና።

👉🏻 ሚካኤል ፍጥረቱ በዕለተ እሑድ ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ዘፍ 1፡3 ላይ “እግዚአብሔርም ብርሃን ይሁን አለ።” ብሎ ብርሃንን በፈጠረ ጊዜ ሕልውና መላእክት ታውቋል። እንዴት ቢሉ ሰሚ በሌለበት ተናጋሪ አይናገርና እንዲሁ ልዑል እግዚአብሔር አስቀድሞ ሰሚአን የሆኑ መላእክትን ስለፈጠረ ብርሃንን በነቢብ (በመናገር) ፈጥሯል።

የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም በዛሬው ዕለት ቀን ይታሰባል። ይህ ቅዱስ መልአክ መጋቤ ብሉይ እየተባለ ይጠራል። በብሉይ ብዙ ገቢረ ተዓምራትን እየሠራ በጎላ በተረዳ አበው ነቢያትን ስለተራዳና ከእግዚአብሔር ተልኮ ድንቅ ድንቅ ሥራዎችን በማድረጉ ይህ ስያሜ ተሰጥቶታል።

#ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበረ መልአክ ጸሎትና አማላጅነት ይማረን ለዘላለሙ አሜን።

17/11/2025



የደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ዓምደ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ለሚያስገነባው ባለ 5 ወለል የመማሪያ #ሕንጻ

ኅዳር ፯ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም

++++++++++++++++++

😍ተመስገን አምላኬ  🙏🙏🙏
16/11/2025

😍ተመስገን አምላኬ 🙏🙏🙏

16/11/2025
11/11/2025
07/10/2025
‹‹ወርሃ ፅጌ›› ፅጌ ማለት አበባ ማለት ሲሆን በዚህ ወር የፅጌሬዳ አበባ የሚፈካበት ወር ነው። ይቺ 40 ቀን "ወርሃ ፅጌ" በመባልም ይጠራል።ፅጌሬዳ በመአዛው እጅግ ያስደስታል ለአይንም ይማ...
07/10/2025

‹‹ወርሃ ፅጌ›› ፅጌ ማለት አበባ ማለት ሲሆን በዚህ ወር የፅጌሬዳ አበባ የሚፈካበት ወር ነው። ይቺ 40 ቀን "ወርሃ ፅጌ" በመባልም ይጠራል።
ፅጌሬዳ በመአዛው እጅግ ያስደስታል ለአይንም ይማርካል እመቤታችንም በአበባው እንመስላታለን ጉድፍ የሌለባት ለነፍስም ለስጋም ደስ ምትል ውበት የስጋ ድንግልና የነፍስም ድንግል ናትና በእሷ መልክ ይሰየማል።
በነገረ ማርያምም እደተፃፈው እመቤታችን መውለጃዋ ቀን ሲደር በአረጋዊው ዮሴፍ ማረፊያ ቦታ ፈልጎ ከብዙ ድካም በኋላ በከብቶች በረት በሚያርፉበት ግርግም ተወለደ በጨርቅ ጠቅልላም አስተኛችው።
ጌታችን ኢየሱስም ሁለት አመት ሲሞላው ኄሮድስ ህፃኑን ክርስቶስን ሊገድለው ስለፈለገ መልአኩ "ተነስተህ እናቱን ና ብላቴናውን ይዘህ ወደ ግብፅ ሽሽ "ብሎ ለዮሴፍ ነገረው።
እመቤታችንም ልጇን ይዛ ከዮሴፍ ጋር ወደ ግብፅ ከመስከረም-26-ህዳር-6 ተሰደደች።
ፆመ ፅጌ የአዋጅ ፆም አይደለም የእመቤታችን ፍቅር ያለው ሰው በውዴታ ስደቷን ስቃዮዋን ለማስታወስ የፈለገ ብቻ በውዴታ የሚፆመው ፆም ነው።
ፆመ ፅጌ የድንግልን ስደት ለምለም አካላቷ ያልጠና ሰውነቷ ጥፍሯ እስኪነቀል ድረስ በሀሩሩ በውርጭኝ ያለ ሀጢያቷ እንግልት በማየቷ በረከትን ለማግኘት እንፆማለን ማለት ነው።
የተባረከ ፆም እንዲሆን ፍቃዷ ይሁንልን🙏

"እናንተ ደካሞች…" እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፡-“እናንተ ኃጢአት ሸክም የሆነችባችሁ፣ እናንተ ጭንቀት አላኖር አላስቀምጥ ያላችሁ፣ እናንተ ሐዘን የደቆሳችሁ፣ እናንተ ትእዛዛቴን በመተላለፍ ቅ...
03/10/2025

"እናንተ ደካሞች…"

እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፡-“እናንተ ኃጢአት ሸክም የሆነችባችሁ፣ እናንተ ጭንቀት አላኖር አላስቀምጥ ያላችሁ፣ እናንተ ሐዘን የደቆሳችሁ፣ እናንተ ትእዛዛቴን በመተላለፍ ቅስማችሁን የተሰበራችሁ፣ እናንተ በሐፍረት ካባ ተከናንባችሁ የምትቆዝሙ፣ እናንተ ከእንግዲህ ወዲህ አበቃልኝ በቃኝ ብላችሁ ያንገሸገሻችሁ፣ እናንተ ለመናገር እንኳን ድፍረት ያጣችሁ … ምንም እንኳን ዝሙት ብትሠሩም፣ ምንም እንኳን ዋሽታችሁ ቢሆንም፣ ምንም እንኳን ሰርቃችሁ ቢሆንም፣ ምንም እንኳን መናገር የማትችሉት ከባድ የምትሉት ኃጢአት ብትሠሩም፣ ምንም እንኳን “ከእንግዲህ ወዲህ በቃ እግዚአብሔር ይቅር አይለኝም” ብትሉም የእኔ ፍቅር የእኔ ቸርነት ይህን ሁሉ ኃጢአታችሁን፣ ይህን ሁሉ ሸክማችሁን፣ ይህን ሁሉ ሐዘናችሁን፣ ይህን ሁሉ ከባድ የምትሉትን ነገራችሁን መደምሰስ የሚችል ነውና ኑ፡፡

ኑና ላሳርፋችሁ፤ ኑና ስለ እናንተ የቆሰለውን እጄ ተደገፉ፤ ኑና ፍቅሬን ቅመሱ፤ ኑና ቸርነቴን አጣጥሙ፤ ኑና ሸክማችሁን ሁሉ በእኔ ላይ አራግፉ፡፡ ብቻ እናንተ ፈቅዳችሁ ኑ እንጂ ከእኔ አቅም በላይ የሆነ ሸክም የለባችሁምና አትስጉ፡፡

ኑና ሥርየተ ኃጢአትን ልስጣችሁ፤ ኑና ዕረፍተ ነፍስን ሰጥቼ ላሳርፋችሁ፤ ኃጢአታችሁ እንደ አለላ ብትሆን እንኳ እንደ አመዳይ አነጻላችኋለሁ፤ እንደ ደምም ብትቀላ እንደ ባዘቶ አጠራላችኋለሁ፡፡ ስለዚህ ኃጢአታችሁን እየቆጠራችሁ ከምትቆዝሙ ቀና በሉና ወደ እኔ ኑ፡፡ እኔ የዋህ በልቤም ትሑት ነኝና ልጆቼ ወደ እኔ ቅረቡ፡፡ እኔም ልቅረባችሁ፡፡ “ቀንበሬን ተሸከሙ” ስላችሁ በሩቁ አትፍሩኝ፡፡ ቀንበሬ ልዝብ ሸክሜም ቀሊል ነውና፡፡ ደግሞም ይህ ቀንበር አንገታችሁን ለማለዘብ (ለመላጥ) ሳይሆን በቀጭኒቱ መንገድ ወደ ግራም ወደ ቀኝም ሳትሉ እኔ ወዳዘጋጀሁላችሁ ርስት መንግሥት የምታደርስ ናትና በሩቁ አትፍሯት፡፡

ስለዚህ እናንተ ደካሞች፣ እናንተ ዓቅመ ቢሶች፣ እናንተ ከእኔ ውጪ ምንም ማድረግ የማትችሉ በገዛ ደሜም የገዛኋችሁ ልጆቼ ወደ እኔ ኑ፤ እኔም ማዳን ብቻ ሳይሆን አሳርፋችኋለሁ፡፡”

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

02/10/2025

+++++++++++++++++++++++++++++++++++++ https://youtu.be/Wqgq1KebrOo 🇪🇹 "የቤተክርስቲያን የሆነውን ብቻ" 🇪🇹ተቋሙን በገንዘብ ለማገዝ፡- የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 👉1000...

ወደ ቀድሞ ነገር እንመለስ🎤የአምላክን እናት እናወድስከፍቅሯ እርቃችሁ የምትኖሩማርያም ፊደል ናት ኑ ተማሩ🙏💖† † †ብዙዎች ተማሩ ስሟን እየጠሩበአባታቸው መንግስት እንደፀሐይ በሩክብር ልዕልና...
01/10/2025

ወደ ቀድሞ ነገር እንመለስ🎤
የአምላክን እናት እናወድስ
ከፍቅሯ እርቃችሁ የምትኖሩ
ማርያም ፊደል ናት ኑ ተማሩ🙏💖
† † †
ብዙዎች ተማሩ ስሟን እየጠሩ
በአባታቸው መንግስት እንደፀሐይ በሩ
ክብር ልዕልናዋን ገብርኤል ነግሮናል
ካወደሷት ጋራ ለክብሯ ቆመናል
‹‹ማርያም ፊደል ናት››
🥰

Address

Debre Birhan

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የደ/ብርሃን ቅ/ሥላሴ ወዳጅ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share