አቡቀለምሲስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

  • Home
  • Ethiopia
  • Debre Birhan
  • አቡቀለምሲስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

አቡቀለምሲስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ  ቤተ ክርስቲያን  የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሚዲያ አቡቀለምሲስ ማለት ረአየ ኅቡኣት አበ ራዕይ አበ ትንቢት ማለት ሲሆን የተሰወረውን የተደበቀውን የተከደነውን የሚገልጥ ማለት ነው።

27/05/2026

የቅዱስ ዑራኤልን በዓል
በደብረ ብርሃን ደብረ ገነት ቅዱስ ዑራኤል ቤተክርስቲያን
ግንቦት 22

በዴባር ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን የመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል የቅዳሴ ቤት በዓል ተከበረ።ግንቦት ፲፱ ቀን ፳፱፲፰ ዓ.ም(አቡቀለምሲስ ሚዲያ: ደብረ ብርሃን)+++++++++++...
27/05/2026

በዴባር ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን የመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል የቅዳሴ ቤት በዓል ተከበረ።

ግንቦት ፲፱ ቀን ፳፱፲፰ ዓ.ም(አቡቀለምሲስ ሚዲያ: ደብረ ብርሃን)

++++++++++++++++++

በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሀገረ ማርያም ወረዳ ቤተ ክህነት ሥር የሚገኘው የዴባር ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን የብሥራታዊው መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ቅዳሴ ቤቱ ተከብሯል።

በዓሉን አስመልክቶ የወረዳው ቤተ ክህነት ዋና ጸሐፊና ሒሳብ ሹም መምህር ሸዋንግዛው ደምሰው" እስከ ቢታንያም አወጣቸው እጆቹንም አንስቶ ባረካቸው" በሚል ኃይለ ቃል ትምህርተ ወንጌል ሰጥተዋል፡፡

የደብሩ ዋና አስተዳዳሪ መልአከ ብሥራት ቀሲስ ከተማ በቀለ በቤተ ክርስቲያኑ ስለ ተሠሩ የተሰሩ መሰረተ የልማት ሥራዎች ጥቅል ሪፖርት አቅርበዋል።

በበዓሉ ላይ የወረዳው ቤተ ክህነት ስብከተ ወንጌል ሓላፊ መምህር ያሬድ ካሳ፣ ከተለያዩ አድባራት ገዳማት በመጡ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና በደብሩ ሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች ያሬዳዊ ዜማ እንዲሁም በርካታ ሕዝበ ክርስቲያን በተገኙበት በድምቀት ተከብሮ ውሏል።

25/05/2026

የበዓለ ንግሥ ጥሪ
ግንቦት 21 በታሪካዊቷ ደብረ ምጥማቅ ጻድቃኔ ቅድስት ማርያም ገዳም

25/05/2026
ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ በደነባ ከተማ በግንባታ ላይ የሚገኘውን የደነባ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ሕንጻ ቤተክርስቲያን ጎበኙ።ግንቦት ፲፯ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም (አቡቀለምሲስ ሚዲያ ፤ ደብረ ብርሃ...
25/05/2026

ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ በደነባ ከተማ በግንባታ ላይ የሚገኘውን የደነባ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ሕንጻ ቤተክርስቲያን ጎበኙ።

ግንቦት ፲፯ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም (አቡቀለምሲስ ሚዲያ ፤ ደብረ ብርሃን)
++++ +++++ +++++ ++++++ +++++ ++++

በሲያደብርና ዋዩ ወረዳ በግንባታ ላይ የሚገኘውን የደነባ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ሕንጻ ቤተክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያና የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ጎብኝተዋል።

ቤተክርስቲያኑ በ2011 ዓ.ም የካቲት 23 ቀን በ2011 ዓ.ም የመቃኞው ቅዳሴ ቤት መከበሩንና ዋናው ቤተክርስቲያን በመስከረም ወር 2017 ዓ.ም ግንባታው መጀመሩን
የደነባ ማኅደረ ስብሐት በኣታ ለማርያም ገዳም አስተዳዳሪ መልአከ ጽዮን አባ ኃይለ ሚካኤል በዳኔ ገልጸዋል።

ብፁዕነታቸው ሕንጻ ቤተክርሰቲያኑን ከጎበኙ በኋላ ባስተላለፉት
መልእክት ለቤተክርስቲያኑ ግንባታ አቅማቸው በፈቀደ ሁሉ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ለሚገኙ ምእመናን በሰማያዊ መግሥቱ ዋጋችሁን ይከፈላችሁ ብለው ለቤተክርስቲያኑ ግንባታ 50 ሺህ ብር ድጋፍ አድርገዋል።

በጉብኝት መርሐ-ግብሩ ላይ የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ
ክቡር መጋቤ ሐዲስ ነቅዐ ጥበብ አባቡ ፣ የሀገረ ስብከት ምክትል ሥራ አስኪያጅና ቁጥጥር ክፍል ሓላፊ ላእከ ኄራን በቀለ ደመረ ተገኝተዋል።

በተመሳሳይ የብፁዕነታቸው አቡነ ቀሲስ መልአከ ስብሐት ቆሞስ አባ ወልደ ማርያም ዘጎርጎርዮስ ፣ የሲያደብርና ዋዩ ወረዳ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ካህናት ይባቤ ተቻለ እና የእንሳሮ ወረዳ ቤተክህነት ሥራ አስኪያጅ መልአከ ሰላም ድረስልኝ ጌታነህ ተገኝተዋል።

25/05/2026

ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ በግንባታ ላይ የሚገኘውን የደነባ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ጎብኝተዋል።

25/05/2026
25/05/2026

የበዓለ ንግሥ ጥሪ

25/05/2026

ማኅበራዊ ሚዲያ!!

24/05/2026

በእንሳሮ ወረዳ ለ9ኝ ዓመታት ሲገነባ የቆየው የሳላይሽ ደብረ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ-ምሕረት ቤተክርስቲያን ቅዳሴ ቤቱ ተከበረ!!

Address

Debre Birhan
0000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አቡቀለምሲስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to አቡቀለምሲስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሚዲያ:

Share