በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት "የደብረ ብርሀን ደ/ገነት ቅዱስ ዑራኤል ቤተክርስቲያን ገፅ ተከታዮች"

  • Home
  • Ethiopia
  • Debre Birhan
  • በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት "የደብረ ብርሀን ደ/ገነት ቅዱስ ዑራኤል ቤተክርስቲያን ገፅ ተከታዮች"

በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት "የደብረ ብርሀን ደ/ገነት ቅዱስ ዑራኤል ቤተክርስቲያን ገፅ ተከታዮች" የኦርቶዶክስ አስተምሮ፣

07/09/2025
03/05/2024
26/05/2023

ታላቅ የክብረ በዓል ጥሪ ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል ልጆችና ወዳጆች በሙሉ!!

እነሆ በደብረ ብርሃን ከተማ የሚገኘው የጮሌ ደብረ ገነት ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን ቅዳሴ ቤት ግንቦት 22 ቀን 2015 ዓ.ም በታላቅ ድምቀት ይከበራል።

ደብረ ገነት ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አባታዊ ፈቃድ መልአከ ገነት ቀሲስ ኃይሌ አየለ በአስተዳዳሪነት ከተመደቡ ጀምሮ በርካታ መሠረታዊ ዕድገትና የልማት ውጤቶች ተመዝግበዋል።

በደብሩ አስተዳዳሪ በሳል አመራር ፣ በትጉሃን አገልጋዮች እና በምእመናን ያላሰለሰ ጥረት በ3 ወራት ውስጥ የአንቀጸ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርሰቲያን የወለዱ በኩረ ልማት መገለጫ ነው።

የዘንድሮውን የቅዳሴ ቤት በዓል አከባበር የተለየ የሚያደርገው የዘርዓ ያዕቆብ እመቤት የጻድኔ ቅድስት ማርያም ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ምርቃት እና ዓመታዊ የቅዳሴ ቤት በሚመረቅበት ማግስት መሆኑ በዓሉን ልዩና የላቀ ድምቀት እንደሚሰጠው ተመላክቷል።

በኢትዮጵያ ለ3ኛ ጊዜ የተተከለው በድርሳነ ዑራኤል ደርደሬ ተብሎ በተገለጸው ቦታ የሚገኘው የደብረ ገነት የቅዱስ ዑራኤል ዓመታዊ ዓመታዊ ክብረ በዓል በድምቀት የሚከበር ስለሆነ በዓሉን ከደብ ምጥማቅ ጻድቃኔ ማርያም በዓል በኋላ ከዋዜማው ጀምሮ በደብረ ብርሃን ደብረ ገነት ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን በመገኘት እና በዓሉን በማክበር የበረከቱ ተሳታፊ እንዲትሆኑ በታላቅ መንፈሳዊ አክብሮት ተጋብዛችኋል!!

በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት የደብረ ብርሃን ደብረ ገነት ቅዱስ ዑራኤል ሰበካ ጉባኤ ጽሕፈት ቤት!!!

መረጃውን ሼር በማድረግ ለሌሎችም እናዳርስ!!!

እግዚአብሔር ይመስገን!
10/08/2022

እግዚአብሔር ይመስገን!

እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ! ዑራኤል የሚለው ስም `ዑር' እና 'ኤል' ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። ዑራኤል ማለት ትርጉሙ “የብርሃን ጌታ...
29/07/2022

እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ!

ዑራኤል የሚለው ስም `ዑር' እና 'ኤል' ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። ዑራኤል ማለት ትርጉሙ “የብርሃን ጌታ”፣ ”የአምላክ ብርሃን" ማለት ነው። ቅዱስ ዑራኤል ከ7ቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ ሲሆን ከፍጥረተ ዓለም ጀምሮ በመብረቅና በነጎድጓድ ላይ የተሾመ መልአክ ነዉ። በመሆኑም መባርቅት ለጥጋብና ለበረከት እንዲበርቁ፣ ነጎድጓድም ለሰላም እንዲሆን ያሰማራል። መጽ/ሄኖክ 6÷2 ምሥጢረ ሰማይና እውቀትንም ሁሉ ለሄኖክ የገለጸለት የፀሀይን የጨረቃን የከዋክብትንና የሰማይ ሰራዊትን ብርሃንን የሚመራ እርሱ መሆኑን ለሄኖክ ነግሮታል። መጽ/ሄኖክ 28÷13

• ቅድስት ድንግል ማርያምን፣ ከልጇ ከአምላካችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ወደ ግብጽ ስትሰደድ መንገድ የመራ፤

• ክርስቶስ ለዓለም ቤዛ በተሰቀለ ጊዜ፣ ክቡር ደሙን በብርሃን ጽዋ ተቀብሎ፣ በብርሃነ መነሳንስ በዓለም ላይ የረጨ፤

•እውቀት ለተሰዎረባቸው ለነቢዩ ዕዝራ ሱቱኤል ጽዋ ጥበብን ያጠጣ፤

• አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በመልአኩ አማላጅነት ብዙ ድርሰት የደረሱት መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል ጽዋ ሕይወትን ስላጠጣቸው ነው፣

• በቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ የተመሰረቱ ገዳማት በቅዱስ ዑራኤል መሪነት ነው፤

የመልአኩ የቅዱስ ዑራኤል በዓላት በዓመት 3 ናቸው።

• ጥር 22 በዓለ ሲመቱ፣

• መጋቢት 27 የጌታ ደሙን ለዓለም የረጨበት፣

• ሐምሌ 21 እና 22 ቅዳሴ ቤቱ የሚከበርበት።

በጸሎቱ ለተማጸነ ከአምላኩ በረከትን ምህረትን የሚያሰጥ አዛኝ እሩህሩህ መልአክ ነው።
የቅዱስ ዑራኤል አማላጂነት አይለየን፤ ሁላችንንም ይጠብቀን፡፡

01/06/2022
31/05/2022
18/05/2022
18/05/2022
16/04/2022

Address

Debre Birhan

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት "የደብረ ብርሀን ደ/ገነት ቅዱስ ዑራኤል ቤተክርስቲያን ገፅ ተከታዮች" posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share