15/06/2020
የውስጡ ሰውነታችን ዕለት ዕለት ይታደሳል። የማይታየውን እንጂ የሚታየውን
ባንመለከት፥ ቀላል የሆነ የጊዜው መከራችን የክብርን የዘላለም ብዛት ከሁሉ መጠን ይልቅ
ያደርግልናልና፤ የሚታየው የጊዜው ነውና፥ የማይታየው ግን የዘላለም ነው። ድንኳን
የሚሆነው ምድራዊ መኖሪያችን ቢፈርስ፥ በሰማይ ያለ በእጅ ያልተሠራ የዘላለም ቤት
የሚሆን ከእግዚአብሔር የተሠራ ሕንጻ እንዳለን እናውቃለንና። በዚህ ውስጥ በእውነት
እንቃትታለንና፥ ከሰማይም የሚሆነውን መኖሪያችንን እንድንለብስ እንናፍቃለንና ለብሰን
ራቁታችንን አንገኝም። በእውነትም የሚሞተው በሕይወት ይዋጥ ዘንድ ልንለብስ እንጂ
ልንገፈፍ የማንወድ ስለ ሆነ፥ በድንኳኑ ያለን እኛ ከብዶን እንቃትታለን። ነገር ግን ለዚሁ
የሠራን እግዚአብሔር ነው እርሱም የመንፈሱን መያዣ ሰጠን። እንግዲህ ሁልጊዜ
ታምነን፥ በእምነት እንጂ በማየት አንመላለስምና በሥጋ ስናድር ከጌታ ተለይተን በስደት
እንዳለን የምናውቅ ከሆንን፥ ታምነናል ይልቁንም ከሥጋ ተለይተን በስደት መኖር
በጌታም ዘንድ ማደር ደስ ይለናል። ስለዚህ ደግሞ ብናድር ወይም ተለይተን ብንሆን
እርሱን ደስ የምናሰኝ ልንሆን እንቀናለን። መልካም ቢሆን ወይም ክፉ እንዳደረገ፥
እያንዳንዱ በሥጋው የተሠራውን በብድራት ይቀበል ዘንድ ሁላችን በክርስቶስ በፍርድ
ወንበር ፊት ልንገለጥ ይገባናልና።
እንዴት ድንቅ ክፍል ነዉ! (ወገኖች ይህንን ክፍል እያንዳንዱን ቃል በማጤን በጥሞና
አንብቡት) ጳውሎስ ጌታን ኢየሱስን ከሙታን ያስሳዉ እግዚአብሔር እኛን አማኞችን ከእርሱ
ጋር እንደሚያስነሳን በመግለፅ የውጭዉ ሰዉነታችን ቢጠፋም (በምንም ሁኔታ ዉስጥ ቢያልፍ)
የዉስጥ ሰዉነታችን ግን እንደሚታደስ ይናገራል፡፡ ስለዚህም ይህ እንደ ድንኳን የሚሆነዉ
መኖሪያ (ሰዉነት) ቢፈርስ እንኳን ከዚህ እጅግ የሚበልጥ መኖሪያ (የማይሞት ሰዉነት)
እንዳለን እናዉቃለን ማለት ነዉ፡፡ ምንም እንኳን ይህ የሚጠፋዉ ድንኳን ከብዶን ብንቃትትም
ለዚህ የሰራን እግዚአብሔር ነዉና የማይሞተዉን እንደምንለሰብስ እርግጥ መሆኑን ለማረጋገጥ
የመንፈሱን መያዣ እንደሰጠን ያስረዳል፡፡ ይህ ማንም ሊወስድብን የማይችል ታላቅ
የእግዚአብሔር የፀጋዉ ስጦታ (ደህንነት) ነዉ፡፡ ታዲያ የአማኞችን ዝግጁነት የሚጠይቀዉ
ጉዳይ ምንድን ነዉ?
ስሞት ገነት ይሆን የምገባዉ ወይስ ሲኦል የሚለው ጥያቄ ነዉ? አይደለም!
ለዘላለም ህይወት ብቁ የሚያደረገኝን ሥራ አልሰራሁም የሚለው ይሆን? አይደለም!
አማኞች ተዘጋጅተዉ (ሊኖሩ የተገባቸውን ህይወት ኖረዉ) ወደ ጌታ እንዲሄዱ የሚጠይቀዉ
ጉዳይ ከላይ በተመለከትነዉ ክፍል በቁጥር10 ላይ የተገለፀዉ ነዉ፡፡(ይቀጥ...)