Christian Abrham

Christian Abrham Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Christian Abrham, Religious Center, Addis Abeba, Bahir Dar.

▹ከዚህ እርካሽ ዓለም ቅዱስ ካልሆነ ግንኙነት እምነት ከሌለብት ንግግር እግዚአብሄር ከማይክበርብት እሩጫ ፍቅር ከሌለበት ስጦታ ተመስጦ ከሌለው ዝማሬ ምፅዋት ከሌለበት ሃብት እንድንርቅ እግዚአብሄር ይርዳን ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች!! 𝐄𝐓𝐇𝐈𝐎𝐏𝐈𝐀-🟩🟨🟥 እዳ ከፋይ የሔዋን እዳ ከፋይ=
_
በሔዋን ምክንያት የገነት ደጅ ተዘጋ ዳግመኛም ስለድንግል ማርያም ተከፈተልን፣ከዕፀ ሕይወት እንበላ ዘንድ አደለን።
_
▹ሔዋን እጸ በለስ ከበላች በኋላ ርግማንን ለመሸከም ተገደደች ከገነት እንድትወጣም ተፈረደባት፣በዚህም ምክንያት የምድረ ፋይዳ እዳ ባለቤት ሆነች፣
▹የውርስ ሐጥያት ያልነካት እመቤታችን ቅድስ ድንግል ማርያም የሔዋንን እዳ አስወገደች፣የሔዋንን እዳ ትከፍል ዘንድ እናቱን መረጠ፣አባ ሕርያቆስ በቅዳሴው እውነተኛ የሕይዎት መብልና መጠጥ ናት ስለወለድሽልን ድንግል ማርያም ሆይ እንወድሻለን፣ብሎ እንደተናገረው ይህ ምግብና መጠጥ፣የሔዋንን እዳ ከንቱ አደረገው።
▹እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ገና በመሕጸን እያለች ነበር የሔዋንን እዳ መክፈል የጀመረችው።
▹ሐና እመቤታችንን ቅድስት ድንግል ማርያምን ጸንሳ እያለች ነበር ወደሊባኖስ የተሠደደችው።
▹እመቤታችን በቤተ መቅደስም ጠላትቿ ነበሩ ልጇ እስከሚያሳርጋት ድረስ በመከራ ውስጥ ሆና የሔዋንን እዳ ትከፍል ነበር።
▹ኢየሱስን ክርስቶስን ጸንሳ እስክትወልድ ድረስ ወልዳም መከራ አልተለያትም።
▹ጨካኙ ከሐዲው ዳቢሎስ አዳምና ሔዋንን ወደገነት ይመልስብኛል ብሎ ሔሮድስን አስነስቶ በስደት መከራን እንድትቀበል አደረጋት፣አይሁድን አስነስቶ ክርስቶስ ልጇን አሠቀለ ምን ያልወጠነው ነገር ነበር ዳቢሎስ? ነገር ግን መለኮትን ይቃወመው ዘንድ አልቻለምና ተሸነፈ።
▹የአዳም ዘር በሙሉ ተነስቶ ከሲኦል ወደገነት ገባ የሔዋን እዳም በዚህ የመከራ ጉዞ ውስጥ ተከፈለ።
በድንግል ርሐብና ጥም እንባና ሐዘን ሔዋንን ከእዳ ተገላገለች እናታችን ሔዋን ከእባብ ጋር የተረገመችው እርግማን ጸጋ ወይም ስጦታ ሆኖ ተሠጣት፣የተዘጋው በር ተከፈተልን።
▹ከፋይ እዳ ፍዳን
ድንግል እናታችን
ለአዳምና ለሔዋን።

በዛ ዘመን በኦሮሞ መንግሥት፤ በአብይ አህመድ መሪነት ብዙ ክርስቲያኖች ተረሽነዋል።ብዙ አማራዎች ታርደዋል እየተባለ ታሪክ ይተርከዋል ፤ይኽን ጽልመት ዘመን ።ዛሬ ናዚ ብሎ መጥራት ጀርመን ውስ...
29/08/2026

በዛ ዘመን በኦሮሞ መንግሥት፤ በአብይ አህመድ መሪነት ብዙ ክርስቲያኖች ተረሽነዋል።ብዙ አማራዎች ታርደዋል እየተባለ ታሪክ ይተርከዋል ፤ይኽን ጽልመት ዘመን ።ዛሬ ናዚ ብሎ መጥራት ጀርመን ውስጥ እንደሚያሳስር ሁሉ የአብይ አህመድ የኦሮሞ መንግሥትም በትውልዱ ዘንድ እንደናዚ ይጠላል ይጠራልም።

ብልጽግናም በዓለም ወንጀለኛ መዝግብ ይመዘገባል እንደ ናዚ።

#ጽልመት

ከፋሲል ከነማ ደጋፊዎች የትብብር ጥሪ።----ወንድማችን ሀብታሙ ጎሹ (ፌኩ) ይባላል። አብዛኞቻችሁ እዚ social media መንደር ያላችሁ ሰዎች ታውቁታላችሁ። በተለያየ ማህበራዊ ና የበጎ አ...
28/08/2026

ከፋሲል ከነማ ደጋፊዎች የትብብር ጥሪ።
----
ወንድማችን ሀብታሙ ጎሹ (ፌኩ) ይባላል። አብዛኞቻችሁ እዚ social media መንደር ያላችሁ ሰዎች ታውቁታላችሁ። በተለያየ ማህበራዊ ና የበጎ አድራጎት ስራ የምናውቀው ወንድማችን ነው ከምንም በላይ ደግሞ በፋሲል ከነማ የልብ ደጋፊነቱና አስጨፋሪነቱ እንዲሁም በተለያዩ የአርት ስራዎች ይታወቃል።
ሂወት ባሰበበት መንገድ አልሄድ ሲለው ምንም እንኳን አደገኛ ቢሆንም ስደትን ምርጫው አድርጏ በግብፅና በሊቢያ በርሀ ድንበር በህገወጥ ደላሎች እጅ ይገኛል።
እስካሁን ያለውን ቤተሰቡ ያለውን ሽጦና ተበዳድሮ የከፈለ ሲሆን የቀረው 1,000,000 ብር ግን ከአቅማቸው በላይ ስለሆነ ወደ እግርኳሱ ቤተሰብ ደጅ ለመጥናት ተገደናል። ሀብቴን በተለያየ መንገድ የምታውቁት የእግርኳስ ቤተሰብ፣ የተለያየ ክለብ ደጋፊዎች፣ ስፖርተኞች፣ የፋሲል ከነማ ደጋፊዎች፣ ከምንም በላይ ደግሞ በውጪ የምትኖሩ ፋሲላዊያን እና ወዳጆቹ እርዳታችሁ ያስፈልገዋል። በመሆኑም ያለው ጊዜ እጅግ በጣም አጭር ከመሆኑ የተነሳ በፍጥነት ተረባርበን ካለበት ጭንቅ እንድናወጣውና በፈጣሪ እርዳታ ያሰበበት እንዲደርስ እንድናደርገው ስንል በፈጣሪ ስም እንጠይቃለን!🙏

ከስር በሚገኘው የእናቱ አካውንት ሁላችንም የተቻለንን እንድናደርግ እና ስክሪን ሹት በinbox እንድትልኩልን በፈጣሪ ስም እንጠይቃለን🙏

1000512569335
Abebu wale

ሼር በማድረግ ለሌሎች እንዲዳረስ አድርጉ!

ቆሞስ አባ ታደሰ በወለጋ እንዶዴ ሥላሴ ገዳም አስተዳዳሪእና የአካባቢው አጥቢያ ቤተክርስቲያን ሀላፊ ነበሩ። ከተመደቡበት ገዳም በጸጥታ አካላት ተወስደው በሚያሰቅቅ ሁኔታ ግድያ ተፈጽሞባቸዋል።...
28/08/2026

ቆሞስ አባ ታደሰ በወለጋ እንዶዴ ሥላሴ ገዳም አስተዳዳሪእና የአካባቢው አጥቢያ ቤተክርስቲያን ሀላፊ ነበሩ። ከተመደቡበት ገዳም በጸጥታ አካላት ተወስደው በሚያሰቅቅ ሁኔታ ግድያ ተፈጽሞባቸዋል። ከግድያው በአሻገር በዚህ መልኩ ተንቀሳቃሽ ምስል ቀርጸው በማሰራጨት በህዝባችን፣ በምዕመኑና በቤተሰቦቻቼው ላይ የማይሽር ጠባሳ ለመጣል ሞክረዋል። ጊዜ ይፍታው አንረሳውም።

የቤተክርስቲያን አላፍ ነን የሚሉ ጋጦጦች ግን ምንም አይሉም ያሳዝናል...​አምላክ ነፍስዎን በጻድቃንና በሰማዕታት ደጅ ያሳርፍልን።

መምህር የአርሲውን ጭፍጨፋ በመቃወማቸው ምክንያት በግፍ መታሰራቸው ይታወቃል። ይሁን እንጂ ፍርድ ቤት በዋስ እንዲለቀቁ  ቢወስንም እስከ አሁን ፍትህ ተነፍገው በእስርና በእንግልት ላይ ይገኛሉ...
27/08/2026

መምህር የአርሲውን ጭፍጨፋ በመቃወማቸው ምክንያት በግፍ መታሰራቸው ይታወቃል። ይሁን እንጂ ፍርድ ቤት በዋስ እንዲለቀቁ ቢወስንም እስከ አሁን ፍትህ ተነፍገው በእስርና በእንግልት ላይ ይገኛሉ። እኛም ለሳምንት ጮኸን ሁሉን ረስተን ተቀመጥን። የማይተወው የማይጥለው የማይረሳው የእውነት አምላክ የሆነው #ክርስቶስ ይመልከታቸው እላለሁ።

“ሰው መጨነቅ ያለበት ስለ እኔ ሳይሆን ሀገር ቤት ስላለው ሕዝብ ነው።” —ክቡር  ዶ/ር ገዱ አንዳርጋቸውየቀድሞው የአማራ ክልል ፕሬዝዳንትና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ገዱ አንዳርጋቸው፣ በ...
26/08/2026

“ሰው መጨነቅ ያለበት ስለ እኔ ሳይሆን ሀገር ቤት ስላለው ሕዝብ ነው።” —ክቡር ዶ/ር ገዱ አንዳርጋቸው

የቀድሞው የአማራ ክልል ፕሬዝዳንትና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ገዱ አንዳርጋቸው፣ በአሜሪካ ሥራ ላይ እያሉ የተቀረጸውን ቪዲዮ አስመልክቶ ምላሽ ሰጥተዋል።

ክቡር ዶ/ር ገዱ በሰጡት ማብራሪያ፣ በስደት አገር በነፃነት የራሳቸውን ሥራ ሠርተው ሕይወታቸውን እየመሩ እንደሚገኙ ገልጸዋል። ትኩረት መደረግ ያለበት በግል ሁኔታቸው ላይ ሳይሆን፣ በሀገር ቤት በችግርና በስቃይ ውስጥ በሚገኘው ሕዝብ ላይ መሆን እንዳለበትም አሳስበዋል።

ይድረስ አቶ ገዱን ለማሸማቀቅ ለተውተረተራችሁ ህሊና ቢስ ሆድ አደሮች ሁሉ።ህሊናን ቀብሮ ሆድን ራስ አድርጎ ሚኒስትር፣ አምባሳደር፣ ኮሚሽነር፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ወይም ሌላ ሹመት በመያዝ፤ የቤ...
26/08/2026

ይድረስ አቶ ገዱን ለማሸማቀቅ ለተውተረተራችሁ ህሊና ቢስ ሆድ አደሮች ሁሉ።

ህሊናን ቀብሮ ሆድን ራስ አድርጎ ሚኒስትር፣ አምባሳደር፣ ኮሚሽነር፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ወይም ሌላ ሹመት በመያዝ፤ የቤተ መንግሥት ሎሌ፣ የአምባገነኖች ጭራ፣ የጨካኞች በትር፣ የጽንፈኛ ብሔረተኞች ፈረስ ሆኖ ከመኖር፤ በክብር፣ ከፍ ባለ የሞራል ልዕልና፣ በራስ ነፃነት፣ በሕዝብ ወገንተኝነት፣ በእውነት እና ግፍን በመጥላት መኖር ይሻላል።

በተለይም በግፈኞች ተዋክቦና ተሳዶ በስደት አገር መኪና ጠባቂ ወይም ከዚያም ዝቅ ያለ ሥራ ከሚሠራ ሰው ጋር ሲነጻጸር፣ ከሁለቱ ማን በሰላም ይተኛል? ማንስ በክብር ሰው ሆኖ ኖሮ፣ ሰው ሆኖ ይሞታል?

ፍርዱን ለእያንዳንዱ ሰው እተወዋለሁ። ለእኔ ግን ሁለተኛውን እመርጣለሁ።

"አንቺ የገነት ምንጭ የህይወት ውሃ ጉድጓድ ከሊባኖስም የሚፈስ ወንዝ ነሽ...መሓለይ ዘሰለሞን 4:15... ድንግል ማርያም የሽቶ መኖሪያና  የሕይወት ውሃ ምንጭ ናት፣ የማህፀኗ ፍሬ ሰውን ሁ...
26/08/2026

"አንቺ የገነት ምንጭ የህይወት ውሃ ጉድጓድ ከሊባኖስም የሚፈስ ወንዝ ነሽ...መሓለይ ዘሰለሞን 4:15... ድንግል ማርያም የሽቶ መኖሪያና የሕይወት ውሃ ምንጭ ናት፣ የማህፀኗ ፍሬ ሰውን ሁሉ አድኗልና ከእኛም እርግማንን አጠፋልን በመካከላችንም ሆኖ በመስቀሉ አስታረቀን በልዩ ትንሳኤውም ሰውን ዳግመኛ ወደ ገነት መለሰው ቅድስት ሆይ ለምኝልን።

"እናቴ እመቤቴ ቅድስት ድንግል ማርያም ክብር ሁሉ ላንቺ ይሁን።

   በማድረግ ለደጋግ ሰዎች እንዲደርስ እናድርግ🙏      ጃፋር መሀመድ የተባለው ወንድማችን ነዋሪነቱ በወሊሶ ከተማ 02 ኢጀርሳ ቀበሌ ነዋሪ ሲሆን የሁለት ልጆች አባት ነው።  ትልቁ መስጂድ...
26/08/2026


በማድረግ ለደጋግ ሰዎች እንዲደርስ እናድርግ🙏

ጃፋር መሀመድ የተባለው ወንድማችን ነዋሪነቱ በወሊሶ ከተማ 02 ኢጀርሳ ቀበሌ ነዋሪ ሲሆን የሁለት ልጆች አባት ነው።

ትልቁ መስጂድ ጀርባ ላይ በብረታብረት ብየዳ ስራ የሚታዳደር ታታሪ ሰራተኛ ነበረ በአሁኑ ስዓት ግን በህመም ምክንያት ስራውን አቁሞ ከወሊሶ ቅዱስ ሉቃስ ሆስፒታል ወደ በአዲስ አበባ ለከፍተኛ ህክምና ተልኮ በአለርት በአሚን ሆስፒታሎች ምርመራ አድርጎ የጨጓራና የጉበት ካንሰር እንዳለበት ተነግሮት አፋጣኝ የቀዶ ጥገና እንደሚያስፈልገው እስከዛው ግን በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የኬሞቴራፒ ሕክምና እንዲያደርግ በተሰጠው የሀኪም ትዕዛዝ መሰረት እያደረገ ይገኛል።

ሆኖም ለቀዶ ህክምናው ገንዘብ የሚያስፈልግ ሲሆን ወንድማችን ለቀዶ ህክምና የተጠየቀው ገንዘብ ቀርቶ በየጊዜዉ ለሚያደርገው የኬሞቴራፒ ወጪ እጅ እያጠረው ስለሚገኘ ሁላችንም በቻልነው አቅም ሁሉ ወንድማችንን እንርዳው ።

ለዚህም ይሆን ዘንድ በራሱና በሰፈር ልጅ እንዲሁም በመስኪድ አካባቢ ጓደኞች የተቆቆመ ኮሚቴ በከተማችን ወሊሶ ውስጥ እርዳታ ለማሰባሰብ ዝግጅት ላይ ይገኛሉ።

ለዚህ እርዳታ እንዲሆን የባንክ አካውንት የተከፈተ ሲሆን በከተማ ውስጥ ያላቹ በአጠቃላይ አነሰ በዛ ሳትሉ ያቅማቹን እጃችሁን ትዘረጉላቸው ዘንድ በአክብሮት እየጠየቅን🙏 ከከተማ ውጪ በተለያዩ ከተሞች እና ከሀገር ውጪ ያላችሁ የከተማችን ተወላጆች እና ደጋግ ኢትዮጲያውያን በሙሉ 50 ሎሚ ለአንድ ሰው ሸክሙ ለ50 ሰው ጌጡ ነው እንደሚባለው አነሰ በዛ ሳንል ሁላችንም በሚከተሉት አካውንቶች በመጠቀም የአቅማችንን ድጋፍ በማድረግ ከፈጣሪ በታች ህይወቱን እንታደግ።

CBE 1000786020267

Coop 1002100406671

Awash 0132017957599001

ለበለጠ መረጃ

0904174515

0912209189

ምድራዊ ገነቱ — ክብራን ገብርኤል!ጣና ሐይቅ ገዳም።ክብራን ገብርኤል አንድነት ገዳም በጣና ሐይቅ ደቡባዊ ክፍል በምትገኝ አንዲት ደሴት ላይ የሚገኝ ገዳም ነው። ከባሕር ዳር ከተማ በቅርብ ር...
26/08/2026

ምድራዊ ገነቱ — ክብራን ገብርኤል!

ጣና ሐይቅ ገዳም።

ክብራን ገብርኤል አንድነት ገዳም በጣና ሐይቅ ደቡባዊ ክፍል በምትገኝ አንዲት ደሴት ላይ የሚገኝ ገዳም ነው። ከባሕር ዳር ከተማ በቅርብ ርቀት ከሚገኙ ገዳማት መካከል አንዱ ሲሆን፣ 8 ኪሎ ሜትር ያህል ርቀት ላይ ይገኛል።

ገዳሙ የተመሠረተው በዐፄ ዓምደ ጽዮን ዘመነ መንግሥት፣ በ1313 ዓ.ም. ሲሆን፣ ገዳሙን የመሠረቱትም አቡነ ዘዮሐንስ ይባላሉ።

አቡነ ዘዮሐንስ ከሰባቱ ከዋክብት ደቀ መዛሙርት አንዱ ናቸው። በሁለት መንትያ ደሴቶች ላይ የወንዶችን ክብራን ገብርኤል እና የሴቶችን እንጦስ ኢየሱስ ገዳማትን የመሠረቱት እነርሱ ናቸው።

ከጀልባ ከወረዱ በኋላ፣ በወፎች ዝማሬ ታጅበው ለጥቂት ደቂቃዎች አቀበታማውን የድንጋይ ደረጃ ይወጣሉ። ከአባ እንጦንስ ኢየሱስ ገዳም ትይዩ፣ ከሐይቁ አናት ላይ የሚገኘውን የወንዶች ገዳም ክብራን ገብርኤልን ያገኙታል።

በገዳሙ ውስጥ አነስተኛ ቤተ መዘክር ይገኛል። በዚያም የተለያዩ ነገሥታት ዘውዶችና 17 ኪሎ ግራም የሚመዝነው፣ 260 የፍየል ሌጦ ቆዳዎችን የፈጀው መጽሐፈ ሐዊ የተባለው የሕግና የሥርዓት መጽሐፍ ይገኛል። በተጨማሪም የተለያዩ የቤተ ክርስቲያን መገልገያዎች፣ ቅዱሳት የብራና መጻሕፍትና በእንጨት ገበታ ላይ የተሳሉ ሥዕሎች በብዛት ይገኛሉ።

የቅዱሳን መናገሻ ከተማ

ክቡራን ገብርኤል ገዳም!

ቀድሰው የሚያቆርቡን ካህናት እስካሁን በጨለማ እስር ቤት ይገኛሉ። ፍርድ ቤት ከዎንጄል ነፃ እንደሆኑ ቢያሳውቅም አመፀኞች “አንለቅም” ብለው እነሆ ሦስት ወር ሆኗቸዋል።የከፋው ደግሞ ወደ ፍር...
25/08/2026

ቀድሰው የሚያቆርቡን ካህናት እስካሁን በጨለማ እስር ቤት ይገኛሉ። ፍርድ ቤት ከዎንጄል ነፃ እንደሆኑ ቢያሳውቅም አመፀኞች “አንለቅም” ብለው እነሆ ሦስት ወር ሆኗቸዋል።

የከፋው ደግሞ ወደ ፍርድ ቤት አይቀርቡም፤ ጠበቃ አያገኙም፤ ቤተሰቦቻቸውም እንዲያገኟቸው አይፈቀድላቸውም።

ይህ ሁሉ ለምን? በዚህ ልክ ግፍ ለምን ይፈጸምባቸዋል? የሕግና የፍትሕ መርህ ለሁሉም እኩል መሆን የለበትምን?

Address

Addis Abeba
Bahir Dar

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Christian Abrham posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Christian Abrham:

Shortcuts

Share