Christian Abrham

Christian Abrham Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Christian Abrham, Religious Center, Bahir Dar.

▹ከዚህ እርካሽ ዓለም ቅዱስ ካልሆነ ግንኙነት እምነት ከሌለብት ንግግር እግዚአብሄር ከማይክበርብት እሩጫ ፍቅር ከሌለበት ስጦታ ተመስጦ ከሌለው ዝማሬ ምፅዋት ከሌለበት ሃብት እንድንርቅ እግዚአብሄር ይርዳን ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች!! 𝐄𝐓𝐇𝐈𝐎𝐏𝐈𝐀-🟩🟨🟥 እዳ ከፋይ የሔዋን እዳ ከፋይ=
_
በሔዋን ምክንያት የገነት ደጅ ተዘጋ ዳግመኛም ስለድንግል ማርያም ተከፈተልን፣ከዕፀ ሕይወት እንበላ ዘንድ አደለን።
_
▹ሔዋን እጸ በለስ ከበላች በኋላ ርግማንን ለመሸከም ተገደደች ከገነት እንድትወጣም ተፈረደባት፣በዚህም ምክንያት የምድረ ፋይዳ እዳ ባለቤት ሆነች፣
▹የውርስ ሐጥያት ያልነካት እመቤታችን ቅድስ ድንግል

ማርያም የሔዋንን እዳ አስወገደች፣የሔዋንን እዳ ትከፍል ዘንድ እናቱን መረጠ፣አባ ሕርያቆስ በቅዳሴው እውነተኛ የሕይዎት መብልና መጠጥ ናት ስለወለድሽልን ድንግል ማርያም ሆይ እንወድሻለን፣ብሎ እንደተናገረው ይህ ምግብና መጠጥ፣የሔዋንን እዳ ከንቱ አደረገው።
▹እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ገና በመሕጸን እያለች ነበር የሔዋንን እዳ መክፈል የጀመረችው።
▹ሐና እመቤታችንን ቅድስት ድንግል ማርያምን ጸንሳ እያለች ነበር ወደሊባኖስ የተሠደደችው።
▹እመቤታችን በቤተ መቅደስም ጠላትቿ ነበሩ ልጇ እስከሚያሳርጋት ድረስ በመከራ ውስጥ ሆና የሔዋንን እዳ ትከፍል ነበር።
▹ኢየሱስን ክርስቶስን ጸንሳ እስክትወልድ ድረስ ወልዳም መከራ አልተለያትም።
▹ጨካኙ ከሐዲው ዳቢሎስ አዳምና ሔዋንን ወደገነት ይመልስብኛል ብሎ ሔሮድስን አስነስቶ በስደት መከራን እንድትቀበል አደረጋት፣አይሁድን አስነስቶ ክርስቶስ ልጇን አሠቀለ ምን ያልወጠነው ነገር ነበር ዳቢሎስ? ነገር ግን መለኮትን ይቃወመው ዘንድ አልቻለምና ተሸነፈ።
▹የአዳም ዘር በሙሉ ተነስቶ ከሲኦል ወደገነት ገባ የሔዋን እዳም በዚህ የመከራ ጉዞ ውስጥ ተከፈለ።
በድንግል ርሐብና ጥም እንባና ሐዘን ሔዋንን ከእዳ ተገላገለች እናታችን ሔዋን ከእባብ ጋር የተረገመችው እርግማን ጸጋ ወይም ስጦታ ሆኖ ተሠጣት፣የተዘጋው በር ተከፈተልን።
▹ከፋይ እዳ ፍዳን
ድንግል እናታችን
ለአዳምና ለሔዋን።

"በአንድነት ስንቆም የማንፈታው ማሰሪያ፣ የማናልፈው ተራራ የለም። በደስታም ሆነ በፈተና ቀናት እርስ በእርስ በመደጋገፍ፣ መከባበርንና መቻቻልን መሠረት ያደረገ ጠንካራ ማህበረሰብ መገንባት የ...
06/06/2026

"በአንድነት ስንቆም የማንፈታው ማሰሪያ፣ የማናልፈው ተራራ የለም። በደስታም ሆነ በፈተና ቀናት እርስ በእርስ በመደጋገፍ፣ መከባበርንና መቻቻልን መሠረት ያደረገ ጠንካራ ማህበረሰብ መገንባት የሁላችንም የጋራ ኃላፊነት ነው። አንድነታችን ኃይላችን፣ መተባበራችን ደግሞ የወደፊት ስኬታችን መሠረት ነው።"

"በየወሩ 29ኛው ቀን የጌታችንን እና መድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ልደት በክብር እናስታውሳለን። የቤተልሔሙ ብርሃን ዛሬም በልባችን ይብራ፤ የክርስቶስ ሰላም፣ ፍቅር እና በረከት በሁላች...
06/06/2026

"በየወሩ 29ኛው ቀን የጌታችንን እና መድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ልደት በክብር እናስታውሳለን። የቤተልሔሙ ብርሃን ዛሬም በልባችን ይብራ፤ የክርስቶስ ሰላም፣ ፍቅር እና በረከት በሁላችን ላይ ይብዛ። አሜን! ✝️🙏🏻"

05/06/2026

ቤተክርስቲያን በስደት ላይ ነች፤ ቤተ አምልኮዎቿ ይቃጠላሉ፣ አማኞቿ ይገደላሉ፣ ብዙዎችም ከቀዬአቸው ይፈናቀላሉ። ይህ ሁሉ ሲሆን ግን እምነቷ አልተሰበረም፤ በመከራ መካከልም ቆማ ትመሰክራለች። ታሪኳ የተጻፈው በመከራ እና በጽናት ነውና ዛሬም በፈተና ውስጥ ሆና ተስፋዋን አልተወችም።

ጌታ ሆይ ከጽዋው ሞልቶ የተረፈውን መከራችንን ተመልከት አጽናኝ የሆነውን መንፈስ ቅዱስንም ላክልን!!
03/06/2026

ጌታ ሆይ ከጽዋው ሞልቶ የተረፈውን መከራችንን ተመልከት አጽናኝ የሆነውን መንፈስ ቅዱስንም ላክልን!!

ሥራችሁ ምን እንደሆነ በውል የማታውቁ የኢኦተቤ ጳጳሳት ሆይ፣አይነ ልቦናችሁንና የልብ ጄሯችሁን ይክፈትል አሜን!በአርሲና አካባቢው በእምነታቸው ምክንያት መከራ፣ ግፍና ሞት እየደረሰባቸው ላሉ ...
02/06/2026

ሥራችሁ ምን እንደሆነ በውል የማታውቁ የኢኦተቤ ጳጳሳት ሆይ፣አይነ ልቦናችሁንና የልብ ጄሯችሁን ይክፈትል አሜን!

በአርሲና አካባቢው በእምነታቸው ምክንያት መከራ፣ ግፍና ሞት እየደረሰባቸው ላሉ ኦርቶዶክሳውያን እግዚአብሔር የሰማዕትነታቸውን ዋጋ ይቀበላቸው!

ከምድራውያን ጠባቂዎች ጥበቃ ተነፍገው ቢቀሩም፣ ወደ ዘላለማዊው እረኛቸው ወደ ክርስቶስ ሄደዋል። እነርሱ በሰማይ የማይጠፋ ክብርን አግኝተዋል፤ እኛ ግን በምድር ላይ ቀርተን ስለ ዝምታ፣ ስለ ፍርሃት እና ስለ ቸልተኝነት ራሳችንን ልንጠይቅ ይገባናል!

በጎቹ ሲበተኑ እረኞቹ የት ነበሩ? በጎቹ በአደጋ ውስጥ ሲወድቁ ድምፃቸው ለምን ጠፋ? የእረኝነትና ኃላፊነት የክብር ወንበር ላይ መቀመጥ ብቻ ሳይሆን በጎቹ ሲሳደዱ ከፊት ቆሞ መከላከልም ነበር መከራችንን በደላችንን ትሰሙ ዘንድ እግዚአብሔር የልብ ጄሯችሁን ይክፈትል በእውነት!

ዛሬ የምናለቅሰው በሞቱት ወንድሞቻችን ብቻ አይደለም፤ በችግር ጊዜ የሚሰማ ጄሮና ድምፅ በማጣታችን፣ በመከራ ጊዜ የሚቆም አባት በማጣታችን ጭምር ይሁን!

እነዚህ ሰማዕታት በደማቸው የመሰከሩትን እምነት እኛ በትዕግሥት፣ በጸሎት እና በጽናት እንጠብቅ የእነርሱን ጽዋ ለመጠጣት ጊዜያችን እስኪደርስ ድረስ በእውነት እንቁም፣ በእምነት እንጽና፣ በተስፋም እንጓዝ!
👉 Abrham Yenealem

31/05/2026

ከእስልምና ወደ ክርስትና አድምጡት ታተርፉበታላችሁ
ቀሪዎቻችሁም ኦርቶዶክስ ሳትሆኑ እንዳትሞቱ።

አለ መቸኮል ደጋግሞ ማየት ። ችኩልነት አገር ያጠፋል መታገስ መልካም ነው ለምሳሌ እየው ላችሁ  መታገስ ብዙ አይነት ነው ለምሳሌ አንድን ችግር  ተሸክመነው ኑረን ኑረን መፍትሄ በምናገኝበት ...
31/05/2026

አለ መቸኮል ደጋግሞ ማየት ። ችኩልነት አገር ያጠፋል መታገስ መልካም ነው ለምሳሌ እየው ላችሁ መታገስ ብዙ አይነት ነው ለምሳሌ አንድን ችግር ተሸክመነው ኑረን ኑረን መፍትሄ በምናገኝበት ቀን የማይረባ ውሳኔ ልንወስን እንችላለን እስከመጨረሻው መጽናት ነው ።
ትዕግስትን ያዘወተረ ሰው ይድናል ማቴዎስ ፳፬፥፲፬
ሁል ጊዜ ያደረጋት

#አባ ገብረ ኪዳን

ሣራ ሁለት ጊዜ ሳቀች ‼️አንደኛው እግዚአብሔር ልጅ ትወልጃለሽ ሲላትካረጀው በኋላ እንዴት ይሆናል? በማለት በልብዋ የውሸት ሳቅ ሳቀችሁለተኛው ይስሐቅን በዘጠና ዓመቷ ከወለደች በኋላእግዚአብሔ...
28/05/2026

ሣራ ሁለት ጊዜ ሳቀች ‼️
አንደኛው እግዚአብሔር ልጅ ትወልጃለሽ ሲላት
ካረጀው በኋላ እንዴት ይሆናል?
በማለት በልብዋ የውሸት ሳቅ ሳቀች

ሁለተኛው ይስሐቅን በዘጠና ዓመቷ ከወለደች በኋላ
እግዚአብሔር ሳቅ አድርጎልኛል ስትል የደስታ ሳቅ ሳቀች

በዘመናችሁ የውሸት ሳይሆን
የእውነትና የደስታ ሳቅ ይሁንላችሁ።

 #መልአከ ገነት ወደ ገነት...! #በታላቅ ኀዘንና በቅዱስ ተስፋ መካከል ሆነን፣ ከግማሽ ክፍለ ዘመን ( 50 ዓመታት) በላይ ዕድሜአቸውን ሙሉ ሳይደክሙና ሳይሰለቹ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንንና...
23/05/2026

#መልአከ ገነት ወደ ገነት...!

#በታላቅ ኀዘንና በቅዱስ ተስፋ መካከል ሆነን፣ ከግማሽ ክፍለ ዘመን ( 50 ዓመታት) በላይ ዕድሜአቸውን ሙሉ ሳይደክሙና ሳይሰለቹ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንንና የእግዚአብሔርን ሕዝብ በቅንነትና በፍቅር ሲያገለግሉ የኖሩትን፣

#የክብር አክሊል ሊቀበሉ ወደ ፈጣሪያቸው የሄዱትን የቦሬ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ዋርካ የሆኑትን ውድ አባታችን መልአከ ገነት ቆሞስ አባ ተስፋ ማርያምን በፍፁም ክብር እናስባቸዋለን

#አባታችን ለእኛ የእምነት ምሰሶ፣ የትሕትና አርአያ እና የፅናት ተምሳሌት ነበሩ በቤተ ክርስቲያን ቅጥር ውስጥ ያሳለፏቸው እነዚያ ረጅም ዓመታት የስም ወይም የስልጣን ሳይሆኑ፣ የፍጹም መሥዋዕትነትና የቅንነት ታሪክ ነበሩ

#ብርድና ሙቀቱ ሳይበግራቸው፣ ፈተናና መከራው ሳይመልሳቸው፣ እንደ ሐዋርያት መልካሙን ገድል ተጋድያለሁ፥ ሩጫውን ጨርሻለሁ፥ ሃይማኖትን ጠብቄአለሁ” (2 ጢሞ 4፥7) የሚሉትን ታላቅ ቃል በተግባር አሳይተውናልና እርሳቸው በፈጣሪያቸው ፊት በእውነት ብፁዕ ናቸው

#ለእናት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን፣ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸውና በፀሎታቸው ለተጠለሉ ምዕመናን ሁሉ እግዚአብሔር አምላክ መጽናናትን ይስጥልን

#የአባታችን በረከትና ረድኤት ከሁላችን ጋር ይሁን ነፍሳቸውን በአብርሃም፣ በይስሐቅና በያዕቆብ እቅፍ ያኑርልን

ኪዳነምህረት" የሚለው ስም ሲጠራ፣ በልባችን ውስጥ ልዩ ሰላም ይነግሳል፤ በነፍሳችንም ውስጥ የተስፋ ብርሃን ይበራል። አዎን፣ ኪዳነምህረት ማለት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት። ይህ ...
23/05/2026

ኪዳነምህረት" የሚለው ስም ሲጠራ፣ በልባችን ውስጥ ልዩ ሰላም ይነግሳል፤ በነፍሳችንም ውስጥ የተስፋ ብርሃን ይበራል። አዎን፣ ኪዳነምህረት ማለት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት። ይህ ስም እንዲሁ ተራ መጠሪያ ሳይሆን፣ በእግዚአብሔርና በሰው ልጅ መካከል የተዘረጋ የፍቅር ድልድይ፣ የማይታጠፍ የይቅርታ ቃል ኪዳን መግለጫ ነው።
"ኪዳን" ማለት በሁለት ወገኖች መካከል የሚደረግ የማይፈርስ ውል ወይም ጥብቅ ስምምነት ማለት ሲሆን፣ "ምህረት" ደግሞ ርኅራኄና ይቅርታ ማለት ነው። ስለዚህ "ኪዳነምህረት" ማለት "የምህረት ቃል ኪዳን" ማለት ነው። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እናቱን ድንግል ማርያምን "ስምሽን የጠራውን፣ ዝክርሽን ያዘከረውን፣ በቃል ኪዳንሽም የተማጸነውን ሁሉ እምርልሻለሁ" ብሎ የሰጣት ታላቅ የጸጋ ስጦታ ነው።

Address

Bahir Dar

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Christian Abrham posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Christian Abrham:

Shortcuts

Share