29/03/2026
"ብዙ ነገር አሳልፌያለሁ፤ እግዚአብሔር የማልችለውን አልሰጠኝም። ሁሉን እንድችል አድርጎ በስኬት ያቆመኝን እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ። ግቢ ጉባኤ ጸሎትን የተለማመድኩባት፣ መንፈሳዊ ሕይወትን የጀመርኩባት የስኬቴ ምክንያት ናት"
ነቢዩ ዳዊት: የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ
መጋቢት 20 ቀን 2018 ዓ.ም
ማኅበረ ቅዱሳን ባሕር ዳር ማእከል በጥበበ ግዮን ግቢ ጉባኤ ያስተማራቸውን ተማሪዎች በዛሬው ዕለት በአባቶች ቡራኬ አስመርቋል።
ከተመራቂ ተማሪዎች መካከል እኩል 3.98 ነጥብ በማምጣት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሕክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ያዘጋጀውን የወርቅ ሜዳሊያ የተሸለሙት ነቢዩ ዳዊት እና ፍቅር ገብሩ የጥበበ ግዮን ግቢ ጉባኤ ፍሬዎች ናቸው።
ማኅበረ ቅዱሳን ባሕር ዳር ማእከል ባዘጋጀው የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር ሁለቱን የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚዎች ጨምሮ በግቢ ጉባኤው አገልግሎት በሥራ አስፈጻሚነት ያገለገሉና የከፍተኛ ማእረግ ተሸላሚዎች የሆኑትን ልዩ ስጦታ እና እውቅና ተበርክቶላቸዋል።
በመርሐ ግብር ላይ ተገኝቶ የተሰማውን ደስታ የገለጸው ተመራቂ ነቢዩ ዳዊት ብዙ ነገር አሳልፌያለሁ፤ እግዚአብሔር የማልችለውን አልሰጠኝም። ሁሉን እንድችል አድርጎ በስኬት ያቆመኝን እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ። ግቢ ጉባኤ ጸሎትን የተለማመድኩባት፣ መንፈሳዊ ሕይወትን የጀመርኩባት የስኬቴ ምክንያት ናት በማለት የተሰማውን ስሜት ገልጿል።
ሌላኛዋ የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ፍቅር ገብሩ የፊዚዮቴራፒ ትምህርት ክፍል ተመራቂ ስትሆን 3.98 ነጥብ በማምጣት ዩኒቨርሲቲው ያዘጋጀውን የወርቅ ሜዳሊያ በመጋራት ለመሸለም በቅታለች።
የግቢ ጉባኤው የሥራ አስፈጻሚ አባላት የነበሩ 3 የከፍተኛ ማእረግ ተመራቂዎችም በጉባኤው ላይ ተገኝተው ስጦታ ተበርክቶላቸዋል።
በመጨረሻም የወርቅ ሜዳልያ እና የከፍተኛ ማእረግ ተሸላሚ ተማሪዎቹ የህጻናት የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር ላይ ተገኝተው የሕይወት ልምዳቸውን አካፍለዋል።
👇👇👇👇👇👇
ማኅበረ ቅዱሳን ባሕር ማእከል ሚዲያ፦
ቴሌግራም፦👇
https://t.me/mkbdcenter
ፌስቡክ፦👇
https://m.facebook.com/mkbahirdarcenter