Eparchy of Bahirdar Dessie

Eparchy of Bahirdar Dessie This page represents a religious institution of Eparchy of BahirDar Dessie with in the Ethiopian C.Ch
(1)

ብፁዕ ካርዲናል ክላውዲዮ ጉጀሮቲ በኮምቦልቻና ደሴ ሐዋርያዊ ጉብኝት አደረጉ፤‎‎ካርዲል ክላውዲዮ ጉጀሮቲ እና የእርሳቸው ልዑካን በባህርዳር-ደሴ ሃገረ ስብከት እያደረጉት ያለውን ሐዋርያዊ ጉብ...
08/06/2026

ብፁዕ ካርዲናል ክላውዲዮ ጉጀሮቲ በኮምቦልቻና ደሴ ሐዋርያዊ ጉብኝት አደረጉ፤

‎ካርዲል ክላውዲዮ ጉጀሮቲ እና የእርሳቸው ልዑካን በባህርዳር-ደሴ ሃገረ ስብከት እያደረጉት ያለውን ሐዋርያዊ ጉብኝት በመቀጠል በሦስተኛው ቀን ቆይታቸው በኮምቦልቻና ደሴ ቁምስናዎች ጉብኝት አድርገዋል።

‎በኮምቦልቻ የደረሱት ብፁዕነታቸው በምዕመናን፣ በካህናት እና በደናግል ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። በቆይታቸውም የመድኃኔዓለም ቁምስና፣ትምህርት ቤቱን እና የአፍሪካ ሚሲዮናዊያን (White Fathers) የወጣቶች ማዕከልን ጎብኝተዋል።

ከዚያም ጉዞአቸውን በመቀጠል ወደ ደሴ በማቅናት በዚያም በምዕመናን፣በአባቶችና በደናግላን ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።በቆይታቸውም ጥንታዊቷን የደሴ ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን እና የአርሶላይን እህቶችን ገዳም ጎብኝተዋል።

‎ጉብኝቱ በሀገረ ስብከቱ የሚገኙ ምዕመናንን፣ ካህናትን እና ማኅበራትን ለማበረታታት እንዲሁም የአካባቢውን የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት በቅርብ ለመመልከት የተደረገ መሆኑ ተገልጿል።

‎ሰኔ 01 ቀን 2018 ዓ.ም.
‎© (የባህርዳር–ደሴ ሀገረ ስብከት ኮሚኒኬሽን ቢሮ)

08/06/2026
ብፁዕ ካርዲናል ክላውዲዮ ጉጀሮቲ በባህርዳር–ደሴ ሀገረ ስብከት ቆይታቸው የእለተ ሰንበት ቅዳሴ አሳረጉ፤‎‎በባህርዳር–ደሴ ሀገረ ስብከት ቆይታቸው ሁለተኛ ቀን ያሳለፉት የምሥራቃውያን ካቶሊካዊ...
07/06/2026

ብፁዕ ካርዲናል ክላውዲዮ ጉጀሮቲ በባህርዳር–ደሴ ሀገረ ስብከት ቆይታቸው የእለተ ሰንበት ቅዳሴ አሳረጉ፤

‎በባህርዳር–ደሴ ሀገረ ስብከት ቆይታቸው ሁለተኛ ቀን ያሳለፉት የምሥራቃውያን ካቶሊካዊ ቤተ ክርስቲያናት ዲካስቴሪ ኃላፊ የሆኑት ካርዲናል ክላውዲዮ ጉጀሮቲ በሀገረ ስብከቱ ጳጳስ አቡነ ልሳነ ክርስቶስ ማቴዎስ የተመራውን የእለተ ሰንበት መስዋዕተ ቅዳሴ አሳርገዋል።

‎በዚሁ ወቅት ከሀገረ ስብከቱ ምዕመናን ተወካዮች በተሰጠ መልዕክት የብፁዕነታቸው በመካከላቸው መገኘት መንፈሳዊ ተስፋቸውን እንዳለመለመና እንዳጠናከረ ገልጸዋል።

‎ብፁዕ አቡነ ልሳነ ክርስቶስ በሰጡት ሰፊ ገለጻ ሀገረ ስብከቱ በቅርብ ዓመታት በጦርነትና በመፈናቀል ምክንያት ያሳለፋቸውን ፈታኝ ሁኔታዎች አብራርተዋል።
‎በተጨማሪም በጉሙዝ አካባቢ እየተከናወነ ያለውን ሃዋርያዊ እንቅስቃሴና የወንጌል ስብከት ጠቅሰው ሀገረ ስብከቱ ሰፊ አካባቢን በማካተቱና በነባራዊ ሁኔታዎች ምክንያት ሁሉንም አካባቢዎች በሃዋርያዊ ጉብኝት ለመድረስ ፈታኝ መሆኑን ገልጸዋል።

‎በመርሃ ግብሩ ማጠቃለያ ላይ ብፁዕ ካርዲናል ለተደረገላቸው ሞቅ ያለ አቀባበል ምስጋናቸውን አቅርበው በምዕመናኑ ዘንድ የተመለከቱት ጠንካራ እምነትና መንፈሳዊ ሕይወት እጅግ እንዳስደነቃቸው ገልጸዋል። በቀጣይም ከፖፕ ሊዮ 14ኛ ጋር በሚያደርጉት ስብሰባ በዚህ ጉብኝት ያዩትን መንፈሳዊ ምስክርነት እንደሚያካፍሉ ገልጸው የፖፕ ሊዮ 14ኛን ሐዋርያዊ ቡራኬ ለምዕመናን፣ ለካህናት እና ለደናግል አድርሰዋል። በስተመጨረሻም በያዝነው አመት የግንባታ ሂደቱ የተጀመረዉን የእግዚአብሄር አብ ካቴድራል አሁናዊ የግንባታ ሂደት ጎብኝተዋል።

‎ግንቦት 30/2018ዓ.ም
‎©(የባህርዳር - ደሴ ሀገረ ስብከት ኮሚኒኬሽን ቢሮ)

ብፁዕ ካርዲናል ክላውዲዩ ጉጀሮቲ የምስራቅ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን የበላይ ኃላፊ ለሐዋሪያዊ ጉብኝት ባህር ዳር ገቡ፤‎‎ብፁዕነታቸው ከልዑካኖቻቸው ጋር በመሆን የባህርዳር-ደሴ ሀገረ ስብከት...
06/06/2026

ብፁዕ ካርዲናል ክላውዲዩ ጉጀሮቲ የምስራቅ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን የበላይ ኃላፊ ለሐዋሪያዊ ጉብኝት ባህር ዳር ገቡ፤

‎ብፁዕነታቸው ከልዑካኖቻቸው ጋር በመሆን የባህርዳር-ደሴ ሀገረ ስብከትን ለመጎብኘት እንዲሁም ሃገረ ስብከቱን ለመባረክ በመሃላችን ሲገኙ የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል በባህር ዳር አውሮፕላን ማረፊያ በመገኘት የሀገረ ስብከቱ ካህናት፣ ደናግላን፣ ምዕመናን እንዲሁም የተለያዩ ሐይማኖት አባቶች በመገኘት ደማቅ አቀባበል የተደረገላቸው ሲሆን፤

‎በደብረ ገነት ኪዳነ ምሕረት ቁምስና ወጣት ያሬዳዊ ዘማሪያን ትውፊቱን በጠበቀ ዝማሬ አቀባበል ተደርጎላቸዋል በመርሃ ግብሩ ላይ ብፁዕነታቸው በተደረገላቸው አቀባበል አመስግነው "እናተ ያቀረባችሁት ዝማሬና ፀሎት ትልቅ በረከት አለው እናንተ የልዑል እግዚአብሔር የእጁ ፍሬዋች ናችሁ ድካማችሁ ሁሉ እርሱ ይቀበላል።"ካሉ በኋላ ህዝብ ክርስቲያን በፀሎት ባርከዋል።

‎ብፁዕ ካርዲናል ከሰዓት በኋላ ውሏቸው የባህርዳር ደሴ ካቶሊክ ጽ/ቤትን የጎበኙ ሲሆን በጽ/ቤቱ ሰራተኞች ደማቅ የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል ተደርጓላቸዋል።

‎ግንቦት 29/2018ዓ.ም
‎©(የባህርዳር - ደሴ ሀገረ ስብከት ኮሚኒኬሽን ቢሮ)

03/06/2026
02/06/2026

የብጹዕ አቡነ ልሳነክርስቶስ ትምህርት 2 ከቀድሞው የሃገረ ስብከቱ የዩቱብ ገፅ የተወሰደ

‎በባህርዳር-ደሴ ሀገረ ስብከት የደብረ ማርቆስ  ''Missionary's Of Charity" (የማዘር ትሬዛ) ማኅበር የተመሰረተበትን 25ኛ አመት እዮቤልዩ በደማቅ ተከበረ፤‎‎በዕለቱ የቅዱስ ...
30/05/2026

‎በባህርዳር-ደሴ ሀገረ ስብከት የደብረ ማርቆስ ''Missionary's Of Charity" (የማዘር ትሬዛ) ማኅበር የተመሰረተበትን 25ኛ አመት እዮቤልዩ በደማቅ ተከበረ፤

‎በዕለቱ የቅዱስ ዮሴፍ አመታዊ ክብረ በዓል የተከበረ ሲሆን፤ ከአመታዊ ክብረ በዓሉ ጋር ይህ የ''Missionary's Of Charity" (የማዘር ትሬዛ) ማህበር 25ኛ እዩቤልዩ መከበሩ ለዕለቱ ትልቅ ድምቀት ሆኖ አልፏል።

‎የዕለቱን የምስጋና መስዋዕተ ቅዳሴ የመሩት እና ቃለ እግዚአብሔር ለህዝበ ክርስቲያኑ ያካፈሉት የቅዱስ ዮሴፍ ቁምስና ቆሞስ ክቡር አባ አማኑኤል ገ/ወልድ በስብከታቸው በሰውኛ ስናስበው አንድ ሰው እጮኛው ከሌላ አርግዛለች ቢባል ምን ያህል አሳፋሪ እንደሚሆን የታወቀ ነው። ነገርግን ዮሴፍ ፃድቅ ሰው ስለነበረ ማርያምን ለክፋት ሊሰጣት አልፈለገም፤ እያንዳንዳችን ከራሳችን ድካም አልፈን የሌሎችን ድካም ለመሸከም ምን ያህል ዝግጁ ነን?እማሆይ ቅድስት ትሬዛ የሚያገለግሏቸው ሰዎች በሌሎች ዘንድ የተናቁና የተጣሉ ነበሩ። ብዙዎች እማሆይ ትሬዛን በዚህ አገልግሎታቸው ይስቁባቸው ነበር። ነገር ግን እማሆይ ትሬዛ በድሆች ውስጥ የተሰቀለውን ኢየሱስን አገኘሁ በማለት ድሆችን ተንከባክበዋል።
‎የቅዱስ ዮሴፍን ጽድቅና ትዕግሥት በማስታወስ ክርስቲያኖች የሌሎችን ድካም ለመሸከም እንዲዘጋጁ አሳስበዋል። እንዲሁም እማሆይ ቅድስት ትሬዛ በተገለሉና በተናቁ ድሆች ውስጥ ክርስቶስን እያዩ በፍቅር እንዳገለገሉ አብራርተዋል።
‎በመጨረሻም ከቀናት ቀናት ፣ ከሳምንታት ሳምንታት ፣ ከወራት ወራት ፣ ከአመታት አመታት አሳልፎ ለ25ኛ አመት ኢዮቤልዩ ያደረሰን እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን ሲሉ ቃለ ምዕዳቸውን አጠቃለዋል።

‎አመታዊ የቅዱስ ዮሴፍ ንግስ እንዲሁም የ 25ኛ ዓመት እዩቤልዩ ክብረ በዓል ከምስጋና መስዋዕተ ቅዳሴው ባሻገር በዝማሬ፣በቅዱስ ቁርባን ኡደት ተከብሮ አልፏል።

‎ግንቦት 22/2018ዓ.ም
‎©(የባህርዳር - ደሴ ሀገረ ስብከት ኮሚኒኬሽን ቢሮ)

26/05/2026
እንኳን ለሚሽነሪስ ኦፍ ቻሪቲ ደብረ ማርቆስ 25ኛ አመት ኢዮቤልዩ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ። በደብረ ማርቆስ ከተማ የሚገኙ የቅድስት እማሆይ ትሬዛ እህቶች በእለተ ቅዳሜ 22/09/2018 ዓ...
25/05/2026

እንኳን ለሚሽነሪስ ኦፍ ቻሪቲ ደብረ ማርቆስ 25ኛ አመት ኢዮቤልዩ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ። በደብረ ማርቆስ ከተማ የሚገኙ የቅድስት እማሆይ ትሬዛ እህቶች በእለተ ቅዳሜ 22/09/2018 ዓ.ም በሚከበረው የ25ኛ አመት ኢዮቤልዩ በዓል እንድትሳተፉ በታላቅ ፍቅርና አክብሮት ጥሪ አቅርበዋል። በእለቱ የሚደረጉ ዝግጅቶች፡

 መስዋዕተ ቅዳሴ
 ምስጋና ማቅረብ
 የ25 አመት ጉዞ ታሪክ
 መዝሙር እና ድራማ
 የምሳ ግብዣ
አድራሻ፡ ደ/ማርቆስ Missionary Of Charity (ማዘር ትሬዛ) ግቢ ውስጥ፡፡

‎ግንቦት 17/2018ዓ.ም
‎©(የባህርዳር-ደሴ ሀገረ ስብከት ኮሚኒኬሽን ቢሮ)

Address

Bahir Dar

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
Tuesday 09:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 09:00 - 17:00
Friday 09:00 - 17:00

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Eparchy of Bahirdar Dessie posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Eparchy of Bahirdar Dessie:

Share