08/06/2026
ብፁዕ ካርዲናል ክላውዲዮ ጉጀሮቲ በኮምቦልቻና ደሴ ሐዋርያዊ ጉብኝት አደረጉ፤
ካርዲል ክላውዲዮ ጉጀሮቲ እና የእርሳቸው ልዑካን በባህርዳር-ደሴ ሃገረ ስብከት እያደረጉት ያለውን ሐዋርያዊ ጉብኝት በመቀጠል በሦስተኛው ቀን ቆይታቸው በኮምቦልቻና ደሴ ቁምስናዎች ጉብኝት አድርገዋል።
በኮምቦልቻ የደረሱት ብፁዕነታቸው በምዕመናን፣ በካህናት እና በደናግል ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። በቆይታቸውም የመድኃኔዓለም ቁምስና፣ትምህርት ቤቱን እና የአፍሪካ ሚሲዮናዊያን (White Fathers) የወጣቶች ማዕከልን ጎብኝተዋል።
ከዚያም ጉዞአቸውን በመቀጠል ወደ ደሴ በማቅናት በዚያም በምዕመናን፣በአባቶችና በደናግላን ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።በቆይታቸውም ጥንታዊቷን የደሴ ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን እና የአርሶላይን እህቶችን ገዳም ጎብኝተዋል።
ጉብኝቱ በሀገረ ስብከቱ የሚገኙ ምዕመናንን፣ ካህናትን እና ማኅበራትን ለማበረታታት እንዲሁም የአካባቢውን የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት በቅርብ ለመመልከት የተደረገ መሆኑ ተገልጿል።
ሰኔ 01 ቀን 2018 ዓ.ም.
© (የባህርዳር–ደሴ ሀገረ ስብከት ኮሚኒኬሽን ቢሮ)