Eparchy of Bahirdar Dessie

Eparchy of Bahirdar Dessie This page represents a religious institution of Eparchy of BahirDar Dessie with in the Ethiopian C.Ch
(1)

‎የባህርዳር-ደሴ ካቶሊክ ጽ/ቤት ሰራተኞች የ2019 ዓ.ም የአዲስ አመት የስራ መክፈቻ እና ያለፈው አመት የስራ ግምገማ የጋራ መድረክ ተካሄደ፤‎‎        ባህርዳር መስከረም 05/2019 ...
16/09/2026

‎የባህርዳር-ደሴ ካቶሊክ ጽ/ቤት ሰራተኞች የ2019 ዓ.ም የአዲስ አመት የስራ መክፈቻ እና ያለፈው አመት የስራ ግምገማ የጋራ መድረክ ተካሄደ፤

‎ ባህርዳር መስከረም 05/2019 ዓ.ም

‎በባህርዳር-ደሴ ሰበካ የካቶሊክ ጽ/ቤት ሰራተኞች የ2019 ዓ.ም የጋራ መድረክ ከሰበካው ጽ/ቤት ሰራተኞች ጋር ተካሄደ።

‎የመድረኩን መርሃ ግብር የባህርዳር-ደሴ ሀገረ ስብከት ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ልሳነክርስቶስ ማቴዎስ በጸሎት በመክፈት መርሃ ግብሩ እንዲጀምር አድርገዋል።

‎የጋራ መድረኩ ዋና ዓላማ በ2018 ዓ.ም የተከናወኑ ሥራዎችን፣ የተገኙ ውጤቶችን፣ ያጋጠሙ ችግሮችንና የተገኙ ሰኬቶችን በመገምገም ለ2019 ዓ.ም የተሻለ የሥራ አፈጻጸም አቅጣጫ ማስቀመጥ ነበር።

‎በተጨማሪም ሰራተኞች የሥራ ልምዳቸውን እንዲለዋወጡ፣ የተሻለ የትብብር የሥራ ባህል እንዲገነቡ እና ከአዳዲስ የጽ/ቤቱ ሰራተኞች ጋር እንዲተዋወቁ ዕድል ፈጥሯል።

‎በመድረኩ ላይ የሰበካው ጽ/ቤት ዳይሬክተር ክቡር አባ ስንታየሁ ገላው በ2018 ዓ.ም በጽ/ቤቱ የተከናወኑ ዋና ዋና ሥራዎችን አቅርበዋል። በተጨማሪም የ2019 ዓ.ም የሥራ አቅጣጫዎችን በማስረዳት የጽ/ቤቱን ራዕይና ተልዕኮ ለሰራተኞች ገለጻ አድርገዋል።

‎በሌላ በኩል በካቶሊክ ማኅበራዊ ትምህርት (Catholic Social Teaching – CST) ዙሪያ ገለጻ ተደርጓል። በሥራ ቦታ የካቶሊክ ማኅበራዊ ትምህርት ያለው ተግባራዊ ትርጉም፣ ሰራተኞች በሙያቸው ለማኅበረሰቡ ሊያበረክቱ የሚችሉት አስተዋጽኦ፣ እንዲሁም በሥራ ቦታ ፍትሃዊነትን፣ ክብርንና አገልግሎትን ማስፈን ስለሚቻልበት መንገድ ተብራርቷል።

‎የጽ/ቤቱ የፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ ደጀን ይግዛው በበኩላቸው በሰበካው ስለሚከናወኑ የልማትና የፕሮጀክት ሥራዎች ሰፊ ገለጻ አድርገዋል።

‎በገለጻቸውም በሰበካው በተለያዩ አካባቢዎች ስለሚከናወኑ የልማት ሥራዎች፣ የምግብ ዋስትና ፕሮጀክቶች፣ የውሃ፣ የሶላር ኃይልና የመጸዳጃ ቤት ፕሮጀክቶች እንዲሁም ሌሎች የልማት ሥራዎች በመጥቀስ በ2018 ዓ.ም የተገኙ ውጤቶችን አብራርተዋል።

‎በተለይም በአማራ ክልልና በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በሚገኙ የተለያዩ ወረዳዎች በልማት ዘርፍ የተከናወኑ ሥራዎችን በማስታወስ ለተጠቃሚዎች ስለተደረጉ ድጋፎችና ስለተፈጠሩ የልማት ዕድሎች አብራርተዋል።

‎እንዲሁም የአቅም ግንባታ (Capacity Building) ሥራዎች በሀገረ ስብከቱ በሚከናወኑ የልማት ፕሮጀክቶች ውስጥ ስላላቸው ሚና በማብራራት የሰራተኞችን አቅምና የሥራ አፈጻጸም በማጠናከር የተሻለ ውጤት ማምጣት እንደሚቻል ገልጸዋል።

‎አቶ ደጀን በተጨማሪም በ2018 ዓ.ም በሥራ ሂደት ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን በመጥቀስ በተለይም ከሰራተኞች የሥራ ጫናና ከተለያዩ የሥራ አካባቢ ተግዳሮቶች ጋር በተያያዘ ለ2019 ዓ.ም የተሻለ የሥራ አቅጣጫ መያዝ እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል።

‎በመድረኩ የሥራ ሥነ-ምግባር (Work Ethics) የቡድን ሥራ (Teamwork) እና ጤናማ የሥራ ባህል አስፈላጊነትም በወንድም አቦነህ ተነስቷል። ሰራተኞች በጋራ በመስራት እርስ በርሳቸው በመደጋገፍና በተጠያቂነት መንፈስ በመስራት የሰበካውን ተልዕኮ ለማሳካት ያላቸውን ሚና ማጠናከር እንደሚገባ ተገልጿል።

‎በመጨረሻም በ2018 ዓ.ም ለተከናወኑ ሥራዎች ሰራተኞች ያበረከቱት አስተዋጽኦ በማድነቅ በ2019 ዓ.ም በተሻለ ትብብር፣ በተጠያቂነትና በትጋት እንዲሰሩ የሚያበረታቱ መልዕክቶችና ምስጋናዎች ቀርበዋል።

‎የጋራ መድረኩም በብፁዕነታቸው በቀረበ ጸሎትና ቡራኬ ተጠናቋል።

‎መስከረም 05/2019 ዓ.ም.
‎© የባህር ዳር–ደሴ ሃገረ ስብከት ኮሚኒኬሽን ቢሮ

‎ለበለጠ መረጃ የባህር ዳር–ደሴ ሀገረ ስብከት የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይጎብኙ።
‎X (Twitter): https://x.com/Bahirdardessie
‎Instagram: https://www.instagram.com/ebdcs2025
‎TikTok: https://www.tiktok.com/
‎YouTube: https://youtube.com/

14/09/2026

እንኳን ከዘመነ ማርቆስ ወደ ዘመነ ሉቃስ በሰላም አደረሳችሁ ::

‎ካቶሊክ ካሪታስ ኢትዮጵያ ባህርዳር–ደሴ ለተፈናቃይ ወገኖች የምግብ ድጋፍ አደረገ፤‎‎በአማራ ክልል ዋግኽምራ ዞን በተፈጥሮ አደጋና በግጭት ምክንያት ከመኖሪያ ቀያቸው ተፈናቅለው ለሚገኙ ተጋላ...
14/09/2026

‎ካቶሊክ ካሪታስ ኢትዮጵያ ባህርዳር–ደሴ ለተፈናቃይ ወገኖች የምግብ ድጋፍ አደረገ፤

‎በአማራ ክልል ዋግኽምራ ዞን በተፈጥሮ አደጋና በግጭት ምክንያት ከመኖሪያ ቀያቸው ተፈናቅለው ለሚገኙ ተጋላጭ ወገኖች አስቸኳይ የምግብ ድጋፍ ተደረገ።

‎የካቶሊክ ካሪታስ ኢትዮጵያ ባህርዳር–ደሴ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ከማኑስ ዩኒዳስ (Manos Unidas) በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ በዋግኽምራ ዞን ከተለያዩ ወረዳዎች ተፈናቅለው ለመጡ 3,000 ተፈናቃይና ተጋላጭ ወገኖች የምግብ ድጋፍ አከፋፈለ።

‎በድጋፉም ለእያንዳንዱ ተፈናቃይ 15 ኪሎ ግራም የስንዴ ዱቄት እና 1 ሊትር የምግብ ዘይት በነፍስ ወከፍ ተሰራጭቷል። በአጠቃላይም 450 ኩንታል የስንዴ ዱቄት እና 3,000 ሊትር የምግብ ዘይት ለተጋላጭ እና ተፈናቃይ ወገኖች ተሰጥቷል።

‎ይህ አስቸኳይ የምግብ ድጋፍ ሙሉ በሙሉ በማኑስ ዩኒዳስ የተደገፈ ሲሆን አጠቃላይ የድጋፉ ዋጋ ከ11,000,000 (አስራ አንድ ሚሊዮን) የኢትዮጵያ ብር በላይ መሆኑ ተገልጿል።

‎የጽ/ቤቱ ፕሮጀክት ማኔጀር አቶ ደጀን ይግዛው ድጋፉ በሚሰጥበት ቦታ በመገኘት ተፈናቃይ ወገኖችን በመጎብኘትና ድጋፉ በአግባቡ እንዲሰራጭ በማድረግ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ አድርገዋል።

‎የተደረገው ድጋፍ በተለይ በአስቸጋሪ ሁኔታ ለሚገኙ ተፈናቃይና ተጋላጭ ወገኖች የምግብ ዋስትናቸውን ለማጠናከር እና የዕለት ተዕለት ኑሯቸውን ለማቃለል ያለመ ነው።

‎ካቶሊክ ካሪታስ ኢትዮጵያ – ባህርዳር–ደሴ

መስከረም 04/2019 ዓ.ም.
‎© የባህር ዳር–ደሴ ሃገረ ስብከት ኮሚኒኬሽን ቢሮ

‎ለበለጠ መረጃ የባህር ዳር–ደሴ ሀገረ ስብከት የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይጎብኙ።
‎X (Twitter): https://x.com/Bahirdardessie
‎Instagram: https://www.instagram.com/ebdcs2025
‎TikTok: https://www.tiktok.com/
‎YouTube: https://youtube.com/

በባህርዳር–ደሴ ሀገረ ስብከት የ2019 ዓ.ም አዲስ ዓመት በዓል ተከበረ፤‎‎ብፁዕ አቡነ ልሳነክርስቶስ ማቴዎስ የባህርዳር–ደሴ ሀገረ ስብከት ጳጳስ የአዲስ ዓመት መስዋዕተ ቅዳሴን መርተዋል።‎...
11/09/2026

በባህርዳር–ደሴ ሀገረ ስብከት የ2019 ዓ.ም አዲስ ዓመት በዓል ተከበረ፤

‎ብፁዕ አቡነ ልሳነክርስቶስ ማቴዎስ የባህርዳር–ደሴ ሀገረ ስብከት ጳጳስ የአዲስ ዓመት መስዋዕተ ቅዳሴን መርተዋል።

‎ብፁዕነታቸው በቃለ እግዚአብሔራቸው ለሀገረ ስብከቱ ምዕመናን፣ ካህናት፣ ሃይማኖታዊ ማኅበራት፣ ወጣቶች፣ ሕፃናትና አገልጋዮች ሁሉ የአዲስ ዓመት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።በመልዕክታቸውም ከዘመነ ማርቆስ ወደ ዘመነ ሉቃስ ስንሻገር ምስጋናን፣ ተስፋንና ጸሎትን ይዘን መጓዝ እንደሚገባን አስገንዝበዋል።በተለይም አዲሱ ዘመን የጸሎት፣ የመንፈሳዊነት፣ የሰላም፣ የአንድነትና የተስፋ ዘመን እንዲሆን ለሀገራችን፣ ለሕዝባችን፣ ለቤተ ክርስቲያናችንና ለዓለማችን ሰላም በጸሎት እንድንለምን አሳስበዋል።

‎እንዲሁም በእምነት መሥራት ተስፋ ለቆረጡ ተስፋ መሆን፣ በችግር ላሉ ወንድሞችና እህቶች መጽናኛ መሆን እንድንችል አንድነታችንን ማጠናከርና የሰላም መሳሪያ መሆን እንደሚገባን አስታውሰዋል።

‎በዚህም አዲስ ዓመት በንስሐ እንድንታደስ የሰይጣንን ክፉ ስራ እንድናጠራ በቃለ እግዚአብሔር እንድንመራና በፍቅር እንድንኖር ጥሪ አቅርበዋል የዘመነ ሉቃስ ሰዎች እንድንሆንና እርሱን በዚህ ዘመን እንድናገለግለው ስለመረጠን ክብር ምስጋና ለእርሱ ይሁን ሲሉ ቃለ ምዕዳቸውን አሳርገዋለ።

‎በዕለቱ በብፁዕነታቸው እጅ ምስጢረ ሜሮን የተሰጠና በደብረ ገነት ኪዳነ ምህረት ቁምስና የሚገኙ ታዳጊ ህፃናት በራሳቸው ተነሳሽነት የተመሰረተው ማህበር በብፁዕነታቸው ብራኬ በይፋ ጀምረዋል። በዓሉም በዝማሬና በታላቅ መንፈሳዊነት ደምቆ ተከብሯል።

‎እንኳን ለ2019 ዓ.ም አዲስ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ!

‎እግዚአብሔር ሰላሙን፣ ጸጋውን፣ ምሕረቱንና በረከቱን በሁላችንም ላይ ያብዛልን። የእመቤታችን በረከትና ምልጃዋ አይለየን።


‎መስከረም 01/2019 ዓ.ም.
‎© የባህር ዳር–ደሴ ሃገረ ስብከት ኮሚኒኬሽን ቢሮ

‎ለበለጠ መረጃ የባህር ዳር–ደሴ ሀገረ ስብከት የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን ይጎብኙ።
‎X (Twitter): https://x.com/Bahirdardessie
‎Instagram: https://www.instagram.com/ebdcs2025
‎TikTok: https://www.tiktok.com/
‎YouTube: https://youtube.com/

የብፁዕ አቡነ ልሳነክርስቶስ ማቴዎስ የባህርዳር -ደሴ ሃገረ ስብከት ጳጳስ ያስተላለፉት የአዲስ አመት (2019 ዓ.ም ) የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት።
10/09/2026

የብፁዕ አቡነ ልሳነክርስቶስ ማቴዎስ የባህርዳር -ደሴ ሃገረ ስብከት ጳጳስ ያስተላለፉት የአዲስ አመት (2019 ዓ.ም ) የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት።

የአዲስ ዓመት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክትበባህርዳር–ደሴ ሃገረ ስብከት ጳጳስ+ ብፁዕ አቡነ ልሳነክርስ...

እንኳን ከዘመነ ማርቆስ ወደ ዘመነ ሉቃስ  በሰላም አሸጋገራችሁ። መልካም አዲስ አመት 2019 ዓ.ም
10/09/2026

እንኳን ከዘመነ ማርቆስ ወደ ዘመነ ሉቃስ በሰላም አሸጋገራችሁ።
መልካም አዲስ አመት 2019 ዓ.ም

የአዲስ ዓመት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት በክቡር አባ ታምራት አጦ

07/09/2026

የወጣቶች የምስጋና መርሃ ግብር የፓዌ ልደታ ማርያም ቁምስና

07/09/2026

የወጣቶች የምስጋና መርሃ ግብር የፓዌ ልደታ ማርያም ቁምስና

06/09/2026
05/09/2026

Address

Bahir Dar

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
Tuesday 09:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 09:00 - 17:00
Friday 09:00 - 17:00

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Eparchy of Bahirdar Dessie posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Eparchy of Bahirdar Dessie:

Shortcuts

Share