21/05/2026
#በዓለ ዕርገት በባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ደብረ ሰላም በዓለ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን በድምቀት ተከበረ።
++++++++++++++++++++
(ግንቦት 13 ቀን 2018 ዓ.ም፤ ባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሚዲያ)
++++++++++++++++++++++
ከጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዐበይት በዓላት መካከል አንዱ የሆነው በዓለ ዕርገት፣ በዛሬው ዕለት በባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ደብረ ሰላም በዓለ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን በድምቀት ተከብሮ ውሏል።
በክብረ በዓሉ ላይ "በብዙ ደስታ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ" (ሉቃ. 24፥52) በሚል ርእስ፣ የሀገረ ስብከቱ የሊቃውንት ክፍል ኃላፊና የአራቱ ጉባኤያት መምህር ክቡር ሊቀ ሊቃውንት ስምዐ ኮነ መልአክ የበዓሉን ታሪክና ምሥጢር የሚያስረዳ ሰፊ ትምህርተ ወንጌል ሰጥተዋል። በተጨማሪም በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና በሰንበት ትምህርት ቤት መዘምራን ያሬዳዊ ወረብና መዝሙር ቀርቧል።
በመጨረሻም በሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ በክቡር መልአከ ሰላም ኤፍሬም ሙሉዓለም አማካኝነት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ተሰጥቶ የበዓሉ ፍጻሜ ሆኗል።
@ባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሕዝብ ግንኙነት ክፍል