06/09/2026
ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት 778 የሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎችን በብፁዕ አቡነ አብርሃም አባታዊ ቡራኬ አስመረቀ
📍 ጳጕሜን 1 ቀን 2018 ዓ.ም. | ባሕር ዳር
የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት፣ በሀገረ ስብከቱ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አስተባባሪነት በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ሲማሩ የነበሩ 778 ተማሪዎችን በብፁዕ አቡነ አብርሃም አባታዊ ቡራኬ አስመርቋል።
የምረቃ መርሐ ግብሩ በደብረ ጽዮን ሰላም አድርጊው ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን የስብከተ ወንጌል አዳራሽ ተካሂዷል።
በመርሐ ግብሩ ላይ የባሕር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ አብርሃም በመገኘት ለተመራቂዎቹ አባታዊ ቡራኬና መልዕክት ሰጥተዋል።
በምረቃ መርሐ ግብሩ ላይ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ሰብሳቢ አቶ አየለ አዱኛ ባቀረቡት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት፣ አንድነቱ በ102 አድባራትና ገዳማት የሚገኙ 83,625 አባላትን በማሳተፍ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ገልጸዋል።
በተጨማሪም፣ በ59 አጥቢያዎች ለ27,542 ተማሪዎች ወጥ የሆነ ሥርዓተ ትምህርት ተግባራዊ መደረጉ ተገልጿል።
🎓 ምረቃ የመጨረሻ ሳይሆን፣ ለአዲስ የእውቀት፣ የእምነትና የአገልግሎት ምዕራፍ መነሻ ነው!
🙏 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት
ፎቶ ባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሚዲያ
#ባሕርዳርሀገረስብከት #ሰንበትትምህርትቤቶችአንድነት #778ተመራቂዎች #ምረቃ #አቡነአብርሃም #ሥርዓተትምህርት #ኦርቶዶክስ