የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት

  • Home
  • Ethiopia
  • Bahir Dar
  • የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት

የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በባሕርዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የሚዲያ ገጽ ነው፡፡

 #በዓለ ዕርገት በባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ደብረ ሰላም በዓለ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን በድምቀት ተከበረ።            ++++++++++++++++++++​(ግንቦት 13 ቀን 2018 ዓ...
21/05/2026

#በዓለ ዕርገት በባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ደብረ ሰላም በዓለ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን በድምቀት ተከበረ።
++++++++++++++++++++
​(ግንቦት 13 ቀን 2018 ዓ.ም፤ ባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሚዲያ)
++++++++++++++++++++++
ከጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዐበይት በዓላት መካከል አንዱ የሆነው በዓለ ዕርገት፣ በዛሬው ዕለት በባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ደብረ ሰላም በዓለ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን በድምቀት ተከብሮ ውሏል።
​በክብረ በዓሉ ላይ "በብዙ ደስታ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ" (ሉቃ. 24፥52) በሚል ርእስ፣ የሀገረ ስብከቱ የሊቃውንት ክፍል ኃላፊና የአራቱ ጉባኤያት መምህር ክቡር ሊቀ ሊቃውንት ስምዐ ኮነ መልአክ የበዓሉን ታሪክና ምሥጢር የሚያስረዳ ሰፊ ትምህርተ ወንጌል ሰጥተዋል። በተጨማሪም በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና በሰንበት ትምህርት ቤት መዘምራን ያሬዳዊ ወረብና መዝሙር ቀርቧል።
​በመጨረሻም በሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ በክቡር መልአከ ሰላም ኤፍሬም ሙሉዓለም አማካኝነት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ተሰጥቶ የበዓሉ ፍጻሜ ሆኗል።
​@ባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሕዝብ ግንኙነት ክፍል

 #የአቡነ ተክለ ሃይማኖትና የቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ዓመታዊ ክብረ በዓል በድምቀት ተከበረ       ​(ግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም |       ​ግንቦት 12 ቀን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ...
20/05/2026

#የአቡነ ተክለ ሃይማኖትና የቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ዓመታዊ ክብረ በዓል በድምቀት ተከበረ

​(ግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም |


​ግንቦት 12 ቀን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓት ተከብረው ከሚውሉት በዓላት መካከል፦
​የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ፍልሰተ አፅም፣
​ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ዐሥር ሺህ ነፍሳትን ከሲኦል ያወጣችበት፣
​የታላቁ ሊቅ የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ዕረፍት፣
​ቅዱስ ሚካኤል እንባቆምን ልኮ ነቢዩ ዳንኤልን በተዘጋ ጉድጓድ ውስጥ የመገበበት ታሪክና ሌሎችም ታስበው ይውላሉ።
​ከላይ ከተጠቀሱት መካከል የአቡነ ተክለ ሃይማኖትና የቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ዓመታዊ ክብረ በዓል በባሕር ዳር ሀገረ ስብከት፣ ቤተ ደናግል አቡነ ገሪማ የእናቶች ገዳም በድምቀት ተከብሮ ውሏል።
​በክብረ በዓሉ ላይ የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ክቡር መላከ ሰላም ኤፍሬም ሙሉዓለም፣ የሀገረ ስብከቱ የየክፍሉ ኃላፊዎች፣ የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣ በርካታ ሊቃውንትና ምእመናን ተገኝተው በዓሉን በማክበር ከቅዱሳኑ በረከት ተካፍለዋል።
የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት የሕዝብ ግንኙነት ክፍል

"ጋብቻ ንጹሕ ነው፤ የወንድና የሴት አንድ መሆንንም እግዚአብሔር አክብሮታል።"— መጽሐፈ ዲድስቅልያሚያዝያ 25/2018 ዓ.ም፣ በደብረ አባይ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያንየጋብቻ ሥነ ሥርዓታቸ...
03/05/2026

"ጋብቻ ንጹሕ ነው፤ የወንድና የሴት አንድ መሆንንም እግዚአብሔር አክብሮታል።"
— መጽሐፈ ዲድስቅልያ

ሚያዝያ 25/2018 ዓ.ም፣ በደብረ አባይ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን
የጋብቻ ሥነ ሥርዓታቸውን ለፈጸሙ
ውድ ወንድማችን ማሩ ላቀው (የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አመራር)
እና እህታችን ትግስት፣

እንኳን ደስ አላችሁ! 🎉

የአብርሃምንና የሣራን፣ የይስሐቅንና የርብቃን ጋብቻ የባረከ አምላክ ትዳራችሁን ይባርክ፤
እመብርሃን በአማላጅነቷ አትለያችሁ፤
ቅዱስ ገብርኤል ከፊታችሁ ይምራችሁ ከኋላችሁም ይከተላችሁ።

መልካም የትዳር ሕይወት ይሁን! ❤️

የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት

26/04/2026
መንፈሳዊ ጉባኤ በዛራ ቅዱስ ሚካኤል
23/04/2026

መንፈሳዊ ጉባኤ በዛራ ቅዱስ ሚካኤል

 #ብፁዕ አቡነ አብርሃም በፈለገ ሕይወት አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ተገኝተው ሕሙማንን ጎበኙ።+++++++++++++++++++++++++​(ሚያዝያ 4 ቀን 2018 ዓ.ም፤ አንድነት ሚዲያ)+...
12/04/2026

#ብፁዕ አቡነ አብርሃም በፈለገ ሕይወት አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ተገኝተው ሕሙማንን ጎበኙ።
+++++++++++++++++++++++++
​(ሚያዝያ 4 ቀን 2018 ዓ.ም፤ አንድነት ሚዲያ)
++++++++++++++++++++++++++
​የባሕር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ አብርሃም በፈለገ ሕይወት አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ተገኝተው ሕሙማንን ጎበኙ።
​በዛሬው ዕለት ፈለገ ሕይወት አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በሆስፒታሉ ለሚገኙ ታካሚዎችና አስታማሚዎች የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የትንሣኤ በዓል ምክንያት በማድረግ የማዕድ ማጋራት መርሐ ግብር አከናውኗል።
​ብፁዕነታቸውም ፈለገ ሕይወት አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የክርስቶስን የትንሣኤ በዓል ምክንያት በማድረግ ይህንን የግብዣ መርሐ ግብር በማዘጋጀቱ የሆስፒታሉን አስተዳደር ሠራተኞች አመስግነዋል።
በዚህ ዕለት በጤናቸው በገጠማቸው እክል ምክንያት በዚህ ታላቅ በዓል ከቤተሰብ ርቀው በፈለገ ሕይወት አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለሚገኙ ታካሚዎችንና አስታማሚዎችም አባታዊ ትምህርተ ወንጌልና ቡራኬ ሰጥተው ተመልሰዋል።
​ታካሚዎችና አስታማሚዎችም በዚህ የተቀደሰ ቀን በብፁዕነታቸው በመጎብኘታቸውና ቡራኬያቸውን በማግኘታቸው እጅግ ደስ እንደተሰኙ ገልጸዋል።
ዘገበው የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ነው

 #ብፁዕ አቡነ አብርሃም የትንሣኤ በዓልን አስመልክቶ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ✝️✝️✝️✝️​( #ሚያዝያ 3 ቀን 2018 ዓ.ም፤  #አንድነት ሚዲያ)✝️​የባሕር ዳርና የሰሜን ...
11/04/2026

#ብፁዕ አቡነ አብርሃም የትንሣኤ በዓልን አስመልክቶ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ
✝️✝️✝️✝️
​( #ሚያዝያ 3 ቀን 2018 ዓ.ም፤ #አንድነት ሚዲያ)

✝️​የባሕር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ አብርሃም፣ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የትንሣኤ በዓል በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ።
✝️ብፁዕነታቸው “እንደተናገረ ተነሥቶአልና በዚህ የለም፤ የተኛበትን ስፍራ ኑና እዩ” (ማቴ 28፡6) የሚለውን የቅዱስ ወንጌል ቃል መነሻ አድርገው ባስተላለፉት መልእክት፤ በዓሉ ሞት በክርስቶስ ሞት ድል የተደረገበትና በጌታ ትንሣኤም የሰው ልጆች ሁሉ ትንሣኤ የታወጀበት ታላቅ ዕለት መሆኑን በዝርዝር አስረድተዋል።
✝️​ብፁዕነታቸው አያይዘውም ምዕመናን በዓሉን ሲያከብሩ በቤተ ክርስቲያን ሥርዓትና ሕግ መሠረት ሊሆን እንደሚገባ አሳስበዋል። በተለይም ደካሞችንና ችግረኞችን በማሰብ፣ ያላቸው ለሌላቸው በማካፈልና የተቸገሩትን በመርዳት በዓሉን በደስታ፣ በፍቅርና በመረዳዳት እንዲያከብሩ አጽንዖት ሰጥተው ተናግረዋል።
ዘገበው @የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሕዝብ ግንኙነት ክፍል

 #‎የጸሎተ_ሐሙስ_ሕጽበተ እግር ብፁዕ አቡነ አብርሃም‎  የባሕር ዳር እና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ   ‎ በባሕር ዳር  ፈለገ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ገዳም( ካቴድራል )በመገ...
09/04/2026

#‎የጸሎተ_ሐሙስ_ሕጽበተ እግር ብፁዕ አቡነ አብርሃም
‎ የባሕር ዳር እና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
‎ በባሕር ዳር ፈለገ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ገዳም( ካቴድራል )በመገኘት የሕጽበተ እግር አከናውነዋል

‎ባሕር ዳር፡ ሚያዝያ 01/2018 ዓ.ም (አንድነት ሚዲያ

‎።

‎🌐 በባሕረዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት

‎SUBSCRIBE 👇 https://www.youtube.com/c/AndnetMedia 💠 የማኅበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን በመቀላቀል መረጃዎችን ይከታተሉ ለሌሎች ኦርቶዶክሳዊያንም ያዳርሱ...

 #ብፁዕ አቡነ አብርሃም በጉባኤ ቤታቸው በማስተማር ላይ ሳሉ ጥቃት የደረሰባቸውን መምህር በጉባኤ ቤታቸው ተገኝተው ጐበኙ​(መጋቢት ፳፬ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም አንድነት ሚዲያ) ✝️​በባሕር ዳር ...
02/04/2026

#ብፁዕ አቡነ አብርሃም በጉባኤ ቤታቸው በማስተማር ላይ ሳሉ ጥቃት የደረሰባቸውን መምህር በጉባኤ ቤታቸው ተገኝተው ጐበኙ

​(መጋቢት ፳፬ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም አንድነት ሚዲያ)

✝️​በባሕር ዳር ሀገረ ስብከት፣ በዓየር ጤና ደብረ መድኃኒት መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን የድጓ መምህር የሆኑት መ/ር መንክር ጌጡ፤ መጋቢት ፳፩ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም. ምሽት ለደቀ መዛሙርታቸው የማኅበር ቀለም እያሰሙ ባለበት ሰዓት የድብደባ ጥቃት ተፈጽሞባቸዋል።

✝️ይህንን ክብረ ቤተ ክርስቲያንን የሚያሳንስ ተግባር በቅጽረ ቤተ ክርስቲያንና በቤተ ጉባኤ ውስጥ መፈጸሙን የሰሙት የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ አብርሃም፤ በቦታው በመገኘት የተጐዱትን መምህርና ደቀ መዛሙርቶቻቸውን ጐበኝተዋል።

✝️​መምህር መንክር የድብደባውን መንስኤና ፈጻሚ አካል ለብፁዕነታቸው ሲያስረዱ፤ ከደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ሣህል ጥበቡ በዛ ጋር ከአሁን በፊት አለመግባባቶች እንደነበሩ ጠቅሰው፣ ወንጀሉን የፈጸሙትም የደብሩ አስተዳዳሪ ልጆች መሆናቸውን ገልጸዋል። ብፁዕነታቸውም የመምህሩን ቃል ካደመጡ በኋላ በተፈጸመው ድርጊት እጅግ አዝነው የሚከተለውን መልእክት አስተላልፈዋል፦
​"ጉባኤ ቤት ሌላኛዋ ቤተ መቅደስ ናት፤ እንዴት እንደዚህ ያለ ክርስቲያናዊ ያልሆነ ግብር በቤተ ጉባኤ ይፈጸማል? ይህ ከመምህሩም ባለፈ ክብረ ቤተ ክርስቲያንን የሚያዋርድ፣ የጉባኤ ቤት መምህራንን ሞራል የሚነካ፣ ነውርም ኃጢአትም የሆነ እኩይ ተግባር ነው።"

✝️​ብፁዕነታቸው አክለውም "ጉዳዩን ሕግ እንደያዘው ሰምተናል፤ ስለሆነም ሕግ በራሱ ሥርዐት ተገቢ የሆነ እርምት ይሰጥበታል ብለን እናምናለን። እኛ ግን እንደ ሀገረ ስብከት በቤተ ክርስቲያን ሕግና ቀኖና መሠረት ጉዳዩን በሚገባ አጣርተን፣ የቤተ ክርስቲያንን ክብር በሚመጥንና አስተማሪ በሆነ መልኩ አስተዳደራዊ መፍትሔ በአስቸኳይ እንሰጣለን" ብለዋል።
✝️ለመምህሩም በደረሰባቸው ጉዳት ከልብ ያዘኑ መሆኑን ገልጸው የመጽናኛ አባታዊ ምክር ሰጥተዋል።

✝️​አያይዘውም ብፁዕነታቸው ለደቀ መዛሙርቱ በሰጡት አባታዊ መመሪያ፤ እንዲህ ዓይነት ፈተናዎች በሚከሰቱበት ጊዜ ተስፋ ሳይቆርጡ፣ የነገ የቤተ ክርስቲያን ተተኪዎች እነርሱ መሆናቸውን አውቀው በትምህርታቸው እንዲበረቱ አሳስበዋል።
✝️ በመጨረሻም መምህሩና ደቀ መዛሙርቱ ከብፁዕነታቸው እግረ መስቀል ሥር ዝቅ ብለው ጸሎተ ማርያም በማስደገምና ቡራኬ በመቀበል በረከት አግኝተዋል።
​@የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሕዝብ ግንኙነት ክፍል

ማኅበረ ቅዱሳን ባሕር ዳር ማእከል በጥበብ ግዮን ግቢ ጉባኤ ያስተማራቸውን 180 የግቢ ጉባኤ ተማሪዎች በአባቶች ቡራኬና በአደራ መስቀል አስመርቋል። መጋቢት 20/2018 ዓ.ምበማኅበረ ቅዱሳን...
30/03/2026

ማኅበረ ቅዱሳን ባሕር ዳር ማእከል በጥበብ ግዮን ግቢ ጉባኤ ያስተማራቸውን 180 የግቢ ጉባኤ ተማሪዎች በአባቶች ቡራኬና በአደራ መስቀል አስመርቋል።

መጋቢት 20/2018 ዓ.ም

በማኅበረ ቅዱሳን የባሕር ዳር ማእከል ምክትል ሰብሰቢ አቶ ብርሃኑ አሳሳ በምረቃ በዓሉ ላይ ተገኝተው የማኅበረ ቅዱሳንን መልእክት ያስተላለፉ ሲሆን ማኅበረ ቅዱሳን እናንተን ሲያስተምር ከተመረቃችሁ በኋላ በግቢ ጉባኤ ያገኛችሁትን እውቀት መንፈሳዊና የአገልግሎት ልምድ አሳድጋችሁ በምትደርሱበት ምድር ሁሉ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን በእውቀታችሁ፣ በገንዘባችሁና በጉልበታችሁ እንድታገለግሏት በማሰብ ነው ብለዋል።

በግቢ ጉባኤው የባች ማስተባበሪያ አገልግሎት ክፍል ተጠሪ እና በፋርማሲ ትምህርት ክፍል 3.94 በማምጣት የከፍተኛ ማእረግ ተመራቂው ማስረሻው ዋለ ስለስኬቱ ሲናገር ግቢ ጉባኤ እናት፣ አባት፣ እህት፣ ወንድም ሆና ለዚህ ስኬት አብቅታኛለችና ግቢ ጉባኤ ለእኔ መተኪያ የላትም በማለት ተናግሯል።

ሃይማኖት ዝግአለ ይባላል። የግቢ ጉባኤው የሙያና በጎ አድራጎት ክፍል ተጠሪ እና በሜዲካል ላቭራቶሪ ትምህርት ክፍል 3.94 በመምጣት የከፍተኛ ማእረግ ተሸላሚ ነው። ግቢ ጉባኤ ለእኔ ያለችኝን ጥቂት ጊዜ ተጠቅሜ በትኩረት በማንበብ ውጤታማ እንድሆን አድርጋኛለች ሲል የስኬቱን ምስጢር ይናገራል።

መአዛ ሙሉዓለም የግቢ ጉባኤው ፀሐፊ በመሆን ስታገለግል ነበር። የህጻናት ነርስ ትምህርት ክፍል ተመራቂ ተማሪ ስትሆን 3.7 በማምጣት በከፍተኛ ውጤት ተመርቃለች። የአብነት ትምህርት በግቢ ጉባኤው ውስጥ በመማር መዝሙረ ዳዊትን ዘልቃለች። መአዛ ግቢ ጉባኤ ለእኔ እናቴ ናት በችግር ጊዜ የመፍትሔ ሰው መሆን እንድችል አስተምራኛለች በማለት ትገልጻለች።

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በሕክምና እና ጤና ሳይንስ ዘርፍ ያሰለጠናቸውን 255 ተመራቂዎች መጋቢት 19 ቀን 2018 ዓ.ም ማስመረቁ የሚታወስ ሲሆን ከእነዚህ ተመራቂዎች መካከል 180 የሚሆኑት ተመራቂዎች በግቢ ጉባኤ የሚሳተፉ የነበሩ ናቸው።

© ማኅበረ ቅዱሳን ባሕር ዳር ማዕከል

Address

Bahir Dar

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት:

Share