30/08/2026
መደበኛ የእሑድ አምልኮ ነሐሴ 24፣ 2018 ዓ.ም
ከሥላሴ በኋላ 10ኛ እሑድ
እውነተኛና ሐሰተኛ ጽድቅ
👉ኤር. 31፥7-9
👉ሮሜ 5፥12-21
👉ማቴ. 23፥1-12
ፕሮግራም መሪ፦ ወ/ም ገዛኸኝ
መዝሙር አገልግሎት፦ የጉባዔ አምልኮ መሪዎች
ቃል አቅራቢ፦ ቄስ ሃብተወልድ አሸናፊ
የቀጠለ (ከባለፈው ሳምንት የቀጠለ)
ርዕስ፦ የእግዚአብሔር ቃልና ቅዱሳት ሚስጥራት (የጸጋ መቀበያ መሣሪያዎች)
ሉቃ. 6፥46-49
የሚጠመቁት ልጆች የትኞቹ ናቸው?
አማኝ የሆነ፣ ሊንከባከባቸውና ቃሉን ማስተማር የሚችል ወላጅ ያላቸው። የክርስትና እናት ወይም አባት አላማው ወላጆች በሞት ቢለዩ እነርሱን ተክተው ለመንከባከብ እንዲመች ነው።
ማጥመቅ የሚችለው ማን ነው?
ለአገልግሎቱ የተመደበ አገልጋይ ወይንም ደግሞ አስቸኳይ ጥምቀት ከሆነ(ተጠማቂው የሞት አፋፍ ላይ ከሆነ) ማንኛውም ምእመን
ቅዱስ ጥምቀት የት መካሄድ አለበት?
የቦታ ወሰን የለውም። ቤትም፣ ከቤት ውጪም ሊካሄድ ይችላል።
እምነት ወይስ ጥምቀት ይቅደም?
እምነትና ጥምቀት የተነጣጠሉ ሳይሆን አብረው መሄድ የሚችሉ ነገሮች ናቸው። ግን ቤተክርስቲያናችን ልጆችን አጥምቃ ታስተምራለች። አዋቂዎችን ደግሞ አስተምህራ ታጠምቃለች።
ጥምቀት በማን ስም ይደረግ?
በአብ፣ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም። በሐዋርያት ሥራ ላይ ሐዋርያት በኢየሱስ ስም ብቻ ያጠመቁት አይሁዶች በእግዚአብሔር አብና በመንፈስ ቅዱስ ስለሚያምኑ የማያምኑት በኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ስለሆነ በዚያ ምክንያት ነው።
3. የጌታ እራት(ቅዱስ ቁርባን)
የጌታ እራት ሌላኛው የጸጋ መቀበያ መንገድ ሲሆን ጌታችን በማቴ. 26፥26-29 ያቋቋመው ሥርዓት ነው።
ቤተክርስቲያናችን ጌታ ይህ "...እንካችሁ፥ ብሉ ይህ ሥጋዬ ነው አለ። . . . ሁላችሁ ከእርሱ ጠጡ፤ ስለ ብዙዎች ለኃጢአት ይቅርታ የሚፈስ የአዲስ ኪዳን ደሜ ይህ ነው።" ስላለ የምንወስደው ኅብስትና ወይን እውነተኛ የጌታ ሥጋና ደም ነው ብለን አምነን ነው የምንቀበለው።