EECMY Referal Congregation Hawassa

EECMY Referal Congregation Hawassa ለወንጌል የምትኖር ቤተ-ክርስቲያን!!

"ሃይማኖታዊ ዕሴቶቻችን ለዘላቂ ሰላማችን” በሚል መሪ ሐሳብ የጸሎት መርሐ ግብር ተካሄደ።ዛሬ ግንቦት 16 2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ባዘጋጀው “ሃይማኖታዊ ዕሴቶቻችን ለ...
24/05/2026

"ሃይማኖታዊ ዕሴቶቻችን ለዘላቂ ሰላማችን” በሚል መሪ ሐሳብ የጸሎት መርሐ ግብር ተካሄደ።

ዛሬ ግንቦት 16 2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ባዘጋጀው “ሃይማኖታዊ ዕሴቶቻችን ለዘላቂ ሰላማችን” በሚል መሪ ሐሳብ በአራዳ ፓርክ ያዘጋጀው ሀገር አቀፍ የአደባባይ የሰላምና አብሮነት የጸሎት / ዱዓ መርሐ ግብር በደማቅ ሁኔታ ተካሂዷል።

በመርሐ ግብሩ የተለያዩ የሃይማኖት አባቶች፣ የመንግሥት ኃላፊዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ አባገዳዎች፣ ሃደ ሲንቄዎች እና በርካታ ወጣቶች ተገኝተው ለኢትዮጵያ ሰላም፣ አንድነት እና መልካም የወደፊት ጉዞ ጸሎት / ዱዓ አድርገዋል።

የጉባኤው ጠቅላይ ፀሀፊ ሊቀ ትጉኀን ቀሲስ ታጋይ ታደለ “ህብረ ብሔራዊ አንድነታችን የዘላቂ ሰላምና ዕድገት መሰረታችን ነው” በማለት አንድነትና ጸሎት ለሀገር ዘላቂ ሰላም ያላቸውን ከፍተኛ አስተዋፅኦ አስገንዝበዋል።

“ኢትዮጵያ ከግል ፍላጎታችን በላይ ናት” በማለትም ሁሉም ዜጎች ለሰላም፣ ለአንድነትና ለሀገራዊ መግባባት በጋራ እንዲቆሙ ጥሪ ቀርቧል።

https://t.me/gmmtvnews22

የ"ጉበኛ ለትውልድ" የጸሎት መርሀግብር ለሀገር ሰላምና ለምርጫ ስኬት ተጠናቀቀ::"ጉበኛ ለትውልድ ዓለም አቀፍ አገልግሎት" በኢትዮጵያ ሰላም፣ ለመንፈሳዊ መነቃቃት እና ለምርጫው ስኬታማነት ሲ...
24/05/2026

የ"ጉበኛ ለትውልድ" የጸሎት መርሀግብር ለሀገር ሰላምና ለምርጫ ስኬት ተጠናቀቀ::

"ጉበኛ ለትውልድ ዓለም አቀፍ አገልግሎት" በኢትዮጵያ ሰላም፣ ለመንፈሳዊ መነቃቃት እና ለምርጫው ስኬታማነት ሲያካሂድ የቆየውን የ5 ቀናት ልዩ የጾምናጸሎት ኮንፈረንስ በድምቀት አጠናቀቀ።
በኮንፈረንሱም
በግንቦት ወር ለሚካሄደው ሀገራዊ ምርጫ ስኬት እና የሀገሪቱን ሰላም በጸሎት አደራ ብለዋል።

በአብያተ ክርስቲያናት ውስጥ የመጨረሻው ዘመን ሪቫይቫል እንዲቀጣጠልና አማኞች ክርስቶስን እንዲመስሉ ጥሪ ቀርቧል ::
በሀገራችን የሚታዩትን የሙስና፣ የጥላቻና የደም መፋሰስ ችግሮች እንዲያቆሙ ምልጃ ተደርጓል።
ለወጣቱ ትውልድ፡ 70 በመቶው የኢትዮጵያ ወጣት በሥነ-ምግባር የታነጸ፣ በሳይንስና በፈጠራ የዳበረ አእምሮ ያለው ትውልድ እንዲሆን ተጸልየዋል።
ለኢትዮጵያውያን፡ በደቡብ አፍሪካ ለሚገኙ ወገኖቻችን ጥበቃና ሰላም እንዲሁም ለእስራኤል ሰላም ልዩ ምልጃ ቀርቧል።
የአገልግሎቱ ባለራዕይ አገልጋይ ነገደ ወልደ ሰንበት፣ አማኞች በጸሎትና በአንድነት ለሀገር ሰላምና ለንጹህ ሕይወት እንዲተጉ ጥሪ አስተላልፈዋል።

ኢቫንጀሊካል ዜና ሩት ዋቅጅራ
ዘገባው ዳንኤል አንተነህ ነው

ከ1 ሺሕ በላይ ዜጎች የሚሳተፉበት የጸሎት መርሃግብር ሊካሄድ ነውየኢትዮጵያ ሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ መጪውን ምርጫ አስመልክቶ ከ1 ሺሕ በላይ ዜጎች የሚሳተፍበት የጸሎት እና የዱአ መርሃግብር ...
22/05/2026

ከ1 ሺሕ በላይ ዜጎች የሚሳተፉበት የጸሎት መርሃግብር ሊካሄድ ነው
የኢትዮጵያ ሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ መጪውን ምርጫ አስመልክቶ ከ1 ሺሕ በላይ ዜጎች የሚሳተፍበት የጸሎት እና የዱአ መርሃግብር እንዳዘጋጀ አስተወቀ።
ይህ መርሃግብር በቀጣይ እሁድ ግንቦት 16 ከቀኑ 9 ሰዓት በአራዳ ፓርክ ከ7 የሃይማኖት ተቋማት የተወጣጡ የሃይማኖት አባቶች ባሉበት እንደሚከናወን ተገልጿል።
በተመሳሳይ ሰዓት በሁሉም ክልሎች የጸሎት ሥነ ሥርዓት እንደሚከናወንም የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሐፊ ቀሲስ ታጋይ ገልጸዋል።
የአደባባይ ጸሎቱ በዋናነት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ በማሰብ የሚካሄድ መሆኑም ገልፀዋል።
የአሁኑ የጸሎት መርሃግብር፤ ጉባኤው በተደጋጋሚ የሚያደርገው የጋራ የጸሎት መሆኑንም ገልፀዋል። በተለይም የኮቪድ 19 ወረርሺኝን በማስታወስ እንዲህ ዓይነት የጋራ ጉዳዮች ሲመጡም ጉባኤው በቀጣይ የፀሎት መርሐግብር እያደረገ እንደሚቀጥል ተነግሯል።

ለኢቫንጄሊካል ዜና አስጨናቂ ሀብታሙ

‎          ክፍል 2 # ‎የሥላሴ ምንነት‎የእግዚአብሔር አንድነት‎የተዋሀደ አንድነት (ዘጸ6:4፣ ኤፌ4:3-6፣ 1ጢሞ2:5)‎ከሁሉም በላይ መሆኑን የሚያመለክት አንድነት (ዘጸ20:3፣ ዘ...
21/05/2026

‎ ክፍል 2
# ‎የሥላሴ ምንነት
‎የእግዚአብሔር አንድነት
‎የተዋሀደ አንድነት (ዘጸ6:4፣ ኤፌ4:3-6፣ 1ጢሞ2:5)
‎ከሁሉም በላይ መሆኑን የሚያመለክት አንድነት (ዘጸ20:3፣ ዘዳ6:4፣ 1ቆሮ8:4-6፣ ያዕ2:19)
‎የእግዚአብሔር ሶስትነት (አሐዱ ሥሉስነት) ሥላሴ
‎ሥላሴ የሚለው ቃል ሦስትነትን በአንድ ለመግለጽ የምንጠቀምበት የግዕዝ ቃል ነው:: ይህም የእግዚአብሔርን ሦስትነት ሳይሆን አንድነት ለመግለጽ ነው::

‎አዲስ ኪዳን በእግዚአብሔር ዘንድ ሦስት አካል እንዳሉና ስማቸውም አብ፣ ወልድና መንፈስ ቅዱስ መሆኑን ይገልጻል:: እያንዳንዱ ፍጹም አካል አለው:: ይህ ማለት ግን እግዚአብሔር በሦስት አይነት መልክ ሳይሆን በባህርይና በመለኮት አንድ የሆኑ ሦስት ፍጹማን አካላት አሉ ማለት ነው:: አካል ማለት በዚህ ትርጉም ፍጹም ሙለአዊና እኔ ባይ ማለት ነው:: ለሥላሴ ትምህርት መሰረቱም፡-

‎የጌታ ኢየሱስ ጥምቀት (ማቴ3:13-17)
‎ለጥምቀት የተሰጠን ሥርአት (ማቴ28:19)
‎የሰው መፈጠርና መውደቅ (ዘፍ1:26,3-:-22)
‎ለበረከት ያላቸው ውህደት(2ቆሮ13-:-13) ናቸው፡፡
‎የሥላሴ ሥራ
‎በመፍጠር

‎አብ - ዘፍ1፡3
‎ወልድ - ዮሐ1:1
‎መንፈስ ቅዱስ - ዘፍ1:2፣ ኢዮ26:12-13
‎በጌታ መወለድ

‎አብ - ዮሐ3:16
‎ወልድ - ሉቃ2:11
‎መንፈስ ቅዱስ - ሉቃ1:35
‎በድነት

‎አብ - ሉቃ15:22
‎ወልድ - ሉቃ15:4
‎መንፈስ ቅዱስ - ኤፌ1:13
‎በሕብረት

‎አብ - ኤፌ2:18
‎ወልድ - 2ቆሮ5:19
‎መንፈስ ቅዱስ - ኤፌ2:18
‎በክብር

‎አብ - 1ቆሮ15:24
‎ወልድ - ፊል3:21
‎መንፈስ ቅዱስ - ራዕ22:17
‎የእግዚአብሔር አብ፣ የእግዚአብሔር ወልድ እና የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ግንኙነት
‎አብ፣ ወልድና መንፈስ ቅዱስ የባሕርይ ስሞች ናቸው::

‎አብ የምክር፣ የሀሳብና የፈቃድ ምንጭ የሆነው አካል ነው:: (ኤፌ1:1፣ ሐዋ22:12-14)
‎ወልድ ከአብ የተገኘ አንድያ ልጁና ፈቃዱን፣ ምክሩንና ሀሳቡን ፈጻሚ ሆኖ የሚገለጥ መለኮታዊ አካል ነው:: (ዮሐ1-:-18,ቆላ1:15-22፣ መዝ40:7-10)
‎መንፈስ ቅዱስ ከአብና ከወልድ የሚወጣ የአብና የወልድን ፈቃድ ሞራልና ሐሳብ የሚያስፈጽም መለኮታዊ አካል ነው:: (ዮሐ15:26፣ ኤፌ1:13፣ ዘፍ1:2)
‎አብ፣ ወልድ እና መንፈስ ቅዱስ አንድ አይነት መለኮታዊ ባሕርይ፣ እኩል አምላክነትና እኩል ዘላለማዊነት አላቸው:: በምክር አንድ ናቸው፤ በሕልውናቸው አይቀዳደሙም፤ በባሕርይም አይበላለጡም:: አንዱን ስንጠራ ሁሉን እየጠራን ነው፤ አንዱን ስናመልክም ሁሉን እያመለክን ነው:: አንዱ በሚሰራበት ሁሉም በአንድነት ይሰራሉ፤ አንዱ የሚያውቀውንም ሁሉም ያውቃሉ:: የማይለያይ፣ የማይከፋፈልና የማይጨፈለቅ (የማይዋጥ) አንድነት አላቸው:: አንዱ ከሌላው ሳይቀድም ለዘላለም በአድነትና በሦስትነት ይኖራሉ::

‎የእግዚአብሔር አብ፣ የእግዚአብሔር ወልድ እና የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ልዩነት
‎በአካልና በስራ ይለያያሉ:: አብን አብ የሚያሰኘው የአባትነት ባሕርይ ነው፤ ወልድን ወልድ የሚያሰኘው የልጅነት ባሕርይ ነው፤ መንፈስ ቅዱስን መንፈስ የሚያሰኘው የተልዕኮ ባሕርይ ነው:: አብ ወልድ አይደለም፤ አብ መንፈስ ቅዱስ አይደለም፤ መንፈስ ቅዱስ አብም ወልድም አይደለም::

‎ስለ ሰው ልጆች ድነት (መዳን) ኢየሱስ ክርስቶስን ወደ ዓለም የላከው አብ ነው::
‎ለሰው ልጆች ኃጢአት በመሰቀል የሞተው በግንባር ቀደምነት ወልድ ነው::
‎በበዓለ ሃምሳ ቀን ለአማኞች ኃይልና መጽናናት እንዲሆን የመጣው መንፈስ ቅዱስ ነው::
‎አብ የራሱ አካል አለው፤ ወልድ የራሱ አካል አለው፤ መንፈስ ቅዱስም የራሱ አካል አለው፡፡ ስለዚህ በአካል ሦስት ናቸው::

‎ጥንቃቄ
‎በዚህ ዓለም በአይናችን በምናያቸው ነገሮች የእግዚአብሔርን ባሕርይ ለመግለጽ ብቁ ስለማይሆኑ ምስጢረ ሥላሴን በምሳሌ ለማስረዳት ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል::

‎👉 አዳዲስ ትምህርታዊ, አስተማሪና ቁምነገር ያለውን መንፈሳዊ መረጃዎችን ለማግኘት ይህንን ( Page Like Follow share ) እያደረጋችሁ ተከታተሉን


‎የማህበር ምዕመናን ዲጂታል የወንጌል አገልግሎት ዘርፍ

‎ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ከታች ያለው Page Follow በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ
https://tr.ee/VcHXkRfRGI
‎Facebook
https://www.facebook.com/share/1BX2xBEgrx/
‎YouTube
https://www.youtube.com/
‎Telegram
https://t.me/EECMYR70








21/05/2026

Enjoy the videos and music you love, upload original content, and share it all with friends, family, and the world on YouTube.

በBelarus ታሪክ ውስጥ ከፍተኛ ነው የተባለውና ከ15,000 በላይ ሰዎችን ያሳተፈ የወንጌል ምሽት ተካሄደበChizhovka-Arena በተካሄደው ታላቅ የወንጌል ስብሰባ 15,500 የሚሆኑ ሰ...
19/05/2026

በBelarus ታሪክ ውስጥ ከፍተኛ ነው የተባለውና ከ15,000 በላይ ሰዎችን ያሳተፈ የወንጌል ምሽት ተካሄደ
በChizhovka-Arena በተካሄደው ታላቅ የወንጌል ስብሰባ 15,500 የሚሆኑ ሰዎች ተሰብስበው “የኃጢአት ደመወዝ ሞት ነው፣ የእግዚአብሔር የጸጋ ስጦታ ግን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ የዘላለም ሕይወት ነው” (ሮሜ 6፡23) የሚለውን የምሥራች መስማታቸውም ተገልጿል።
በዝግጅቱም አንድ ሰው ባለፈው ማክሰኞ ሕይወቱን ለማጥፋት አስቦ እንደነበር ነገር ግን እግዚአብሔር እንዳስመለጠው ምስክርነት መስጠቱም ተነግሯል። በዚህም በወንጌል ምሽቱ ስነ ሰርዓት መምጣቱን ተከትሎም የሰማው ወንጌል እየሱስ ክርስቶን አምኖ እንዲቀበል እንዳደረገውም ተገልጿል ።
በተጨማሪም በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎችም ከኃጢአታቸው ተመልሰው ሕይወታቸውን ለጌታ አሳልፈው ሰጥተዋል። ይህ በBelarus ታሪክ ውስጥ ከፍተኛ እና ታሪካዊ የወንጌል ስብሰባ መሆኑ ተገልጿል።
በዚህ ሥራ ውስጥ ለብዙ ዓመታት በጸሎት የተባበሩ አብያተ ክርስቲያናትና ፓስተሮች ምስጋናም የቀረበ ሲሆን ባለፈው ሳምንት በሀገሪቱ ያሉ ክርስቲያኖች 24 ሰዓት ያልተቋረጠ ጸሎት ሲያደርጉ እንደቆዩ ተጠቅሷል።
እንዲሁም ከ43 የተለያዩ ከተሞች የተውጣጡ 1,300 አባላት ያሉት መዘምራን፣ ኦርኬስትራዎች፣ ሙዚቀኞችና ሶሎቲስቶች በፕሮግራሙ ላይ በልዩ ሁኔታ ተሳትፈዋል። መረጃዉን GMM TV አገኘነዉ።
ለኢቫንጄሊካል ዜና አስጨናቂ ሀብታሙ፡፡

በመጋቢት 16 ቀን 2018 ዓ.ም ከኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ዋና ቢሮ የወጣ ታሪካዊ ውሳኔመካነ ኢየሱስ ራሳቸውን "ሐዋርያት" እና "ነቢያት" ብለው የሚጠሩትን ጨምሮ የ...
19/05/2026

በመጋቢት 16 ቀን 2018 ዓ.ም ከኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ዋና ቢሮ የወጣ ታሪካዊ ውሳኔ

መካነ ኢየሱስ ራሳቸውን "ሐዋርያት" እና "ነቢያት" ብለው የሚጠሩትን ጨምሮ የሌሎች ቤተ እምነት አገልጋዮች በመድረኬ ላይ እንዲጋበዙም ሆነ አገልጋዮቼ በእነርሱ መድረክ ላይ እንዲቆሙ አልፈቅድም ብላለች። ይህንን በሚያደርጉ እና ውሳኔዋን በሚተላለፉ ቄሶችና ወንጌላውያን ላይ ቅስናቸውን እስከ መግሰስ እና ከወንጌላዊነት መደብ እስከ ማንሳት የሚደርስ የማያዳግም እርምጃ እንደምትወሰድ ጠንከር ያለ መልእክት አስተላልፋለች።

"ብልጥ ልጅ የተሰጠውን ይዞ ለቀረው ያለቅሳል" እንዲሉ፣ ስለዚህ ታላቅና ታሪካዊ ውሳኔ መሪዎቻችንን እያመሰገንን፣ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ከካውንስል እና ከሉተራን ዎርልድ ፌዴሬሽን ሕብረት ውስጥ ሙሉ በሙሉ ለቃ መውጣቷን እስክናረጋግጥ ድረስ ቃለ እግዚአብሔርን መሠረት ያደረገ ሙግታችን የሚቀጥል መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን።

‎‎‎የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ሪፈራል ማህበር ምዕመናን‎  ================================‎      ግንቦት 09/09/2018 ዓ.ም ሀዋሳ ‎‎መል...
18/05/2026



‎የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ሪፈራል ማህበር ምዕመናን
‎ ================================
‎ ግንቦት 09/09/2018 ዓ.ም ሀዋሳ

‎መልዕክት አቅራቢ: ፍሬው ሀ/ማሪያም

‎የመነሻ ጥቀስ: መዝሙር ዳዊት 25_3

‎ርዕሰ: ተስፋችንን አጥብቀን እንያዝ ።
‎ -----------------------------
‎ተስፋችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።

‎ 1. ተስፋ የሰጠን እርሱ የታመነ ነውና ተስፋችን የሆነውን ኢየሱስን በመከራ ጊዜም ይሁን በደስታ ጊዜ እርሱን ማሰብ ያስፈልጋል።

‎2. በእግዚአብሔር ላይ ተስፋ ያደረገ ሰው ምንም ዓይነት ችግር በሚደርስበት ጊዜ በችግርና በመከራ ውስጥ ሆነው ተስፋው ኢየሱስ እንደሆነ ያስባል አይናወጥም።

‎1. እግዚአብሔርን ተስፋ ያደረገ ሰው ተስፋውን በችግር፣በመከራ እንድሁም በስኬት አይለካም። በሞት ጥላ ውስጥ ሆነው የማይሞት ተስፋ ይጠበቃል።
‎2. ተስፋን አጥብቆ የያዘ ሰው ለቤተክርስቲያን ፣ ለቤተሰበ፣ ለራሱ እና ለሀገር እንደ አብርሃም በረከት ይሆናል። ዘፍ 12፥1

‎ስለዚህ ከሁኔታው፣ ከችግር፣ከመከራ፣ከስኬት እና ካለን ነገር በላይ እግዚአብሔርን ተስፋ ማድረግ አያሳፍርም። ተስፋችን በእምነት እና በፍቅር በትዕግሥትም እንያዝ።

‎“አንተን ተስፋ የሚያደርጉ አያፍሩም፤ በከንቱ የሚገበዙ ያፍራሉ።”
‎ መዝሙር 25፥3

‎ ኢየሱስ ጌታ ነው!!
‎ 👇
‎ የማህበር ምዕመናን ዲጂታል የወንጌል አገልግሎት ዘርፍ

‎ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ከታች ያለው Page Follow በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ
https://tr.ee/VcHXkRfRGI
‎Facebook
https://www.facebook.com/share/1BX2xBEgrx/
‎YouTube
https://www.youtube.com/
‎Telegram
https://t.me/EECMYR70

‎ውድ ተከታዮቻችን ከዚህ ቀደም ስለመጽሐፍ ቅዱስ እስከ ክፍል አራት ድረስ አቅርበንላችሁ ነበር አሁን ከዚህ በመቀጠል ስለ እግዚአብሔር ክፍል አንድ ይዘንላችሁ መተናል የእናንተ ሀሳብና አስታይ...
16/05/2026

‎ውድ ተከታዮቻችን ከዚህ ቀደም ስለመጽሐፍ ቅዱስ እስከ ክፍል አራት ድረስ አቅርበንላችሁ ነበር አሁን ከዚህ በመቀጠል ስለ እግዚአብሔር ክፍል አንድ ይዘንላችሁ መተናል የእናንተ ሀሳብና አስታይታችሁ አይለየን እያለን ወደ ትምህርቱ

‎ ክፍል አንድ

‎ መግቢያ
‎እግዚአብሔር የሚለው ቃል የሁለት ግዕዝ ቃላት "እግዚአ" እና "ብሔር" ጥምር ቃል ሲሆን ትርጓሜውም፡-

‎እግዚአ ማለት ጌታ ማለት ሲሆን
‎ብሔር ደግሞ ማለት አለም ወይም ህዝብ ማለት ነው፡፡
‎በአንድ ላይም እግዚአብሔር የሚለው ቃል የአለም ጌታ ማለት ነው::

‎የእግዚአብሔር ባሕሪያት

‎የእግዚአብሔር መለኮታዊ ባሕሪያት
‎መንፈስ ነው ፡- (ዮሐ4:24)
‎ዘላለማዊ ነው :- (1ጢሞ1:17፣ ሚል3:6)
‎ሁሉን ቻይ ነው :- (ዘፍ17:1፣ ማቴ19:26፣ ራዕ15:3፣ 19:6)
‎በሁሉም ሥፍራ አለ :- (ዘፍ28:15፣ መዝ139:7-10፣ ኤፌ1:23)
‎ሁሉን አዋቂ ነው :- (መዝ104:24፣ ሮሜ11:33፣ ኤፌ3:10፣ ዘፍ18፡18፣ ዘፍ19፣ ሉቃ16:15፣ ዕብ4:13)
‎የበላይ ባለሥልጣን ነው :- (ዳን4:35፣ ሮሜ9:21)
‎ቅዱስ ነው :- (ዘሌ19:2፣ 1ጴጥ1:15-16)

‎የእግዚአብሔር የሥነምግባር ባሕሪያት

‎ቅዱስ ነው :- (ዘፀ15:11፣ ሉቃ1:49፣ ራዕ4:8)
‎ጻድቅ ነው :- (ዘፍ18:25፣ 1ዮሐ1:9)
‎ታማኝ ነው :- (ዘዳ7:9፣ 1ቆሮ1:9)
‎መሐሪ ነው :- (ሰቆኤር3:22፣ ቲቶ3:5)
‎ፍቅር ነው :- (ዘዳ7:8፣ ዮሐ3:16፣ 1ዮሐ4:9)
‎ታጋሽ ነው :- (ዘፀ3፣ 34-:-6)
‎እውነተኛ ነው ፡- (ዘዳ32፡4፣ ዘዳ20፡22፣ ዘጸ20፡22)
‎ቸር ነው ፡- (ዘዳ22፡27፣ መዝ86፡15)



‎👉 አዳዲስ ትምህርታዊ, አስተማሪና ቁምነገር ያለውን መንፈሳዊ መረጃዎችን ለማግኘት ይህንን ( Page Like Follow share ) እያደረጋችሁ ተከታተሉን



‎ 👇
‎የማህበር ምዕመናን ዲጂታል የወንጌል አገልግሎት ዘርፍ

‎Follow Us
https://tr.ee/VcHXkRfRGI
‎Facebook
https://www.facebook.com/share/1BX2xBEgrx/
‎YouTube
https://www.youtube.com/
‎Telegram
https://t.me/EECMYR70




በአካል ጉዳተኞች አገልግሎት ላይ ያተኮረ አውደ ጥናት በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ዋና ጽሕፈት ቤት እየተካሄደ ይገኛል።"ከስቃይ ባሻገር" በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ባ...
14/05/2026

በአካል ጉዳተኞች አገልግሎት ላይ ያተኮረ አውደ ጥናት በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ዋና ጽሕፈት ቤት እየተካሄደ ይገኛል።

"ከስቃይ ባሻገር" በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ባለው አውደ ጥናት ከተለያዩ የቤተ ክርስቲያቱ ሲኖዶሶች እና የአገልግሎት ክፍሎች የመጡ አገልጋዩች እና መሪዎች እየተሳተፉበት የሚገኝ ሲሆን አላማውም በቤተክርስቲያን እና በማህበረሰብ ውስጥ ያሉ አካል ጉዳተኞችን ፍላጎቶችኝ በመረዳት በአካታችነት የማገልገል አስፈላጊነት ግንዛቤ የሚያስጨብጥ ነው።

በመክፈቻ መርሃ ግብሩም የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ፕሬዝዳንት ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ ባደረጉት ንግግር "ይህ ስልጠና በይዘቱ የመጀመሪያው መሆኑን በመጥቀስ የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ድምበር የለሽ መሆኑን ተናግረዋል።

አክለውም በቤተ ክርስቲያን እና በማህበረሰብ ውስጥ ውስንነት ያላቸውን ሰዎች አቅማቸውን በመጠቀም በህይወታቸው ውጤታማ እንዲሆኑ መርዳት አስፈላጊ መሆኑን አሳስበዋል።

የአውደ ጥናቱም ተካፋዮች መጽሐፍ ቅዱሳዊ የአካል ጉዳተኝነትን ትርጓሜ መገንዘባቸውን እና ሊሰጣቸው ስለሚገባ አገልግሎት መረዳታቸውን በመግለጽ ብዙ ጎጂ ባህላዊ መረዳቶችን እንዲቀይሩ ስልጠናው እንደረዳቸው ተናግረዋል።

አገልግሎቱን በብሔራዊ ደረጃ እያስተባበረ ከሚገኘው የወንጌል እና ቲኦሎጂ መምሪያ የዲያቆና አገልግሎት የሥራ ክፍል ለመረዳት እንደተቻለው ይህንን መሰል ሥልጠና በቀጣይ በተለያዩ ክላስተሮች ከአጋር ድርጅት ከሆነው ከጆኒና ጓደኞቹ ተቋም ጋር በመተባበር እንደሚሰጥ ተገልጿል።

The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus

የስብሐት ለአምላክ  የመዝሙር መጽሐፍት በአዲስ መልክ ታትሞ መቅረቡን  የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የምሥራች ድምፅ የመገናኛ ዘዴዎች አገልግሎት  አስታወቀች፡፡ የስብሐ...
12/05/2026

የስብሐት ለአምላክ የመዝሙር መጽሐፍት በአዲስ መልክ ታትሞ መቅረቡን የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የምሥራች ድምፅ የመገናኛ ዘዴዎች አገልግሎት አስታወቀች፡፡
የስብሐት ለአምላክ 1ኛ መጽሐፍ ዝማሬ አዳዲስ መዝሙራት ታክለውበት ተሻሽሎና ታርሞ እንዲሁም በአንድ ርዕስ ውስጥ የሚገኙትን መዝሙሮች አንድ ላይ በማምጣት መዘጋጀቱን የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የምሥራች ድምፅ የመገናኛ ዘዴዎች አገልግሎት ዳይሬክተር ቄስ ገመቺስ ዲዲ ገልጸዋል፡፡
የስብሐት ለአምላክ 1ኛ የመዝሙር መጽሐፍ አርባ አምስት ዓይነት መዝሙሮች በተለያዩ ርዕሶች የያዘ ሲሆን ሁሉም ርዕሶች ለተጠቃሚው በሚመች መልኩ መቀመጣቸው ቄስ ገመቺስ ዲዲ ጨምረው ገልጸዋል፡፡
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የምሥራች ድምፅ የመገናኛ ዘዴዎች አገልግሎት የጽነ ጹሑፍ ክፍል አስተባባሪ የሆኑት አቶ ደመላሽ ዶላ በበኩላቸው የመዝሙር መጽሐፉን ለማዘጋጀት ረጅም ጊዜ የወሰደ መሆኑን አስታውቀው ቁጥር 2 የስብሐት ለአምላክ የመዝሙር መጽሐፍ ለማዘጋጀትም አስፈላጊው ዝግጅት መጠናቀቁንም አስታውቀዋል፡፡
የስብሐት ለአምላክ 1ኛ የመዝሙር መጽሐፉን የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የምሥራች ድምፅ የመገናኛ ዘዴ አገልግሎት በመካኒሳ፣ በአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም ፣ በመገናኛ፣ በቦሌ፣ በቢሾፍቱ እና በአዳማ የንዋየ ቅዱሳት ማከፋፈያዎች ማግኘት እንደሚቻልም አቶ ደመላሽ ዶላ ጨምረው ገልጸዋል፡፡
የስብሐት ለአምላክ 1ኛ የመዝሙር መጽሐፍ ከዘጠኝ ዓመታት በኃላ አዳዲስ መዝሙራት ታክለውበት ተሻሽሎና ታርሞ መዘጋጀቱን ለማወቅ ተችሏል፡፡

👇
‎የማህበር ምዕመናን ዲጂታል የወንጌል አገልግሎት ዘርፍ

‎Follow Us
https://tr.ee/VcHXkRfRGI
‎Facebook
https://www.facebook.com/share/1BX2xBEgrx/
‎YouTube
https://www.youtube.com/
‎Telegram
https://t.me/EECMYR70

Address

Referal Mekanyesus
Awassa
REFERALMEKANYESUS

Telephone

+251916769670

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when EECMY Referal Congregation Hawassa posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to EECMY Referal Congregation Hawassa:

Share