24/05/2026
"ሃይማኖታዊ ዕሴቶቻችን ለዘላቂ ሰላማችን” በሚል መሪ ሐሳብ የጸሎት መርሐ ግብር ተካሄደ።
ዛሬ ግንቦት 16 2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ባዘጋጀው “ሃይማኖታዊ ዕሴቶቻችን ለዘላቂ ሰላማችን” በሚል መሪ ሐሳብ በአራዳ ፓርክ ያዘጋጀው ሀገር አቀፍ የአደባባይ የሰላምና አብሮነት የጸሎት / ዱዓ መርሐ ግብር በደማቅ ሁኔታ ተካሂዷል።
በመርሐ ግብሩ የተለያዩ የሃይማኖት አባቶች፣ የመንግሥት ኃላፊዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ አባገዳዎች፣ ሃደ ሲንቄዎች እና በርካታ ወጣቶች ተገኝተው ለኢትዮጵያ ሰላም፣ አንድነት እና መልካም የወደፊት ጉዞ ጸሎት / ዱዓ አድርገዋል።
የጉባኤው ጠቅላይ ፀሀፊ ሊቀ ትጉኀን ቀሲስ ታጋይ ታደለ “ህብረ ብሔራዊ አንድነታችን የዘላቂ ሰላምና ዕድገት መሰረታችን ነው” በማለት አንድነትና ጸሎት ለሀገር ዘላቂ ሰላም ያላቸውን ከፍተኛ አስተዋፅኦ አስገንዝበዋል።
“ኢትዮጵያ ከግል ፍላጎታችን በላይ ናት” በማለትም ሁሉም ዜጎች ለሰላም፣ ለአንድነትና ለሀገራዊ መግባባት በጋራ እንዲቆሙ ጥሪ ቀርቧል።
https://t.me/gmmtvnews22