Denb full gospel believers church

Denb full gospel believers church "22 And whatsoever we ask, we receive of him, because we keep his commandments, and do those things

 #ጥር እሁድ  #10/2018 ዓ.ም        #ደንቢ ኢትዮጵያለ4ት ተከታታይ ቀናት አድስ ህንጻ ለማስጀመሪያና የመሠረት ድንጋይ ለመጣል ስካሄድ የነበረዉ መንፈሳዊ ኮንፎረንስ ተጠናቀቀ።በእነ...
19/01/2026

#ጥር እሁድ #10/2018 ዓ.ም
#ደንቢ ኢትዮጵያ
ለ4ት ተከታታይ ቀናት አድስ ህንጻ ለማስጀመሪያና የመሠረት ድንጋይ ለመጣል ስካሄድ የነበረዉ መንፈሳዊ ኮንፎረንስ ተጠናቀቀ።በእነዚህ ቀናት በቃል ያገለገሉት ከ ዝዋይ ሕ/ብ/ቤ/ክ መጋቢ #ዘርፉ ወልደዮሐንስ ስሆኑ በዝማሬ ደግሞ በብዙ ዝማሬዎቹ የምናውቀው ወንድማችን ዘማር #ክፍሌ ሹዴ ያገለገሉ ሲሆን የቀድሞ የአለታ በንሳና አከባቢዉ ከልል ፐረስደንት #መጋቢ ጳውሎስ ሆሼ÷የቀድሞ የቤተክርስቲያንቱ መጋቢ #ኃይሉ መጦ÷የቤተክርስቲያንቱ መስራች ወንድም #ተስፋዬ ጉጆ እና ከተለያዬ ቦታ የመጡ እንግዶች በተገኙበት በአለታ በንሳና አከባቢው ክልል ፐረስደንት #በመጋቢ በቀለ ሀደሶ የመሠረት ድንጋይ በይፋ ተቀምጧል።

11/01/2026
 #በምስራቃዊ ሲዳማ ዞን ዳዬ ከተማ አስተዳደር ደንቢ ቀበሌ  #በደንቢ ሙሉወንጌል ቤ/ክ  #ጥር 10/2018 ዓ.ም የአለታና በንሳ አከባቢው ክልል ፐረስደንት በሆኑት በተከበሩ በአቶ በቀሌ ሀ...
01/01/2026

#በምስራቃዊ ሲዳማ ዞን ዳዬ ከተማ አስተዳደር ደንቢ ቀበሌ #በደንቢ ሙሉወንጌል ቤ/ክ #ጥር 10/2018 ዓ.ም የአለታና በንሳ አከባቢው ክልል ፐረስደንት በሆኑት በተከበሩ በአቶ በቀሌ ሀዴሶ የመሠረት ድንጋይ በይፋ ይቀመጣል ስለዝህ ለዚህ ለእግዚአብሔር ቤት ሥራ ድጋፍ እንድታደርጉና የበረከቱ ተካፋዮች እንድትሆኑ ተጋብዛችኋል።
ዕዝራ 1
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³ ከሕዝቡ ሁሉ በእንናተ ዘንድ ማንም ቢሆን አምላኩ ከእርሱ ጋር ይሁን፥ እርሱም በይሁዳ ወዳለችው ወደ ኢየሩሳሌም ይውጣ፥ በኢየሩሳሌምም ለሚኖረው አምላክ፥ ለእስራኤል አምላክ ለእግዚአብሔር ቤት ይሥራ፤
⁴ በሚኖርበትም ስፍራ ሁሉ ለቀረው ሰው የአገሩ ሰዎች በብርና በወርቅ በዕቃም በእንስሳም ይርዱት፤ ይህም በኢየሩሳሌም ላለው ለእግዚአብሔር ቤት በፈቃዳቸው ከሚያቀርቡት ሌላ ይሁን።
⁵ የይሁዳና የብንያም የአባቶች ቤቶች አለቆችም፥ ካህናቱም፥ ሌዋውያኑም፥ በኢየሩሳሌም ያለውን የእግዚአብሔርን ቤት ለመሥራት ይወጡ ዘንድ እግዚአብሔር መንፈሳቸውን ያነሣሣው ሁሉ ተነሡ።
⁶ በዙሪያቸውም ያሉ ሁሉ በፈቃዳቸው ካቀረቡት ሁሉ ሌላ በብር ዕቃና በወርቅ በገንዘቦችና በእንስሶች በሌላም ስጦታ አገዙአቸው።

30/12/2025

ሐጌ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³ በቀድሞ ክብሩ ሳለ ይህን ቤት ያየ በእናንተ መካከል የቀረ ማን ነው? ዛሬስ እንዴት ሆኖ አያችሁት? በዓይናችሁ እንደ ምናምን አይደለምን?
⁴ አሁን ግን፥ ዘሩባቤል ሆይ፥ በርታ፥ ይላል እግዚአብሔር፤ ታላቁም ካህን የኢዮሴዴቅ ልጅ ኢያሱ ሆይ፥ በርታ፥ እናንተም የአገሩ ሕዝብ ሆይ፥ በርቱና ሥሩ፥ ይላል እግዚአብሔር፤ እኔ ከእናንተ ጋር ነኝና፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር።
⁵ መንፈሴም በመካከላችሁ ይኖራልና አትፍሩ።
⁶ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና፦ ገና አንድ ጊዜ በቅርብ ዘመን እኔ ሰማያትንና ምድርን ባሕርንና የብስንም አናውጣለሁ፤
⁷ አሕዛብን ሁሉ አናውጣለሁ፥ በአሕዛብ ሁሉ የተመረጠውም ዕቃ ይመጣል፤ ይህንም ቤት በክብር እሞላዋለሁ፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር።
⁸ ብሩ የእኔ ነው፥ ወርቁም የእኔ ነው፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር።
⁹ ከፊተኛው ይልቅ የዚህ የሁለተኛው ቤት ክብር ይበልጣል፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር፤ በዚህም ስፍራ ሰላምን እሰጣለሁ፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር።

6 ስለዚህ አንድ ሥጋ ናቸው እንጂ ወደ ፊት ሁለት አይደሉም። እግዚአብሔር ያጣመረውን እንግዲህ ሰው አይለየው።
17/12/2025

6 ስለዚህ አንድ ሥጋ ናቸው እንጂ ወደ ፊት ሁለት አይደሉም። እግዚአብሔር ያጣመረውን እንግዲህ ሰው አይለየው።

18/10/2025

ምሳሌ 4
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁸ የጻድቃን መንገድ ግን እንደ ንጋት ብርሃን ነው፥ ሙሉ ቀን እስኪሆንም ድረስ እየተጨመረ ይበራል።


²⁶ የእግርህን መንገድ አቅና፥ አካሄድህም ሁሉ ይጽና።

ነጻ ሶፍትዌር (መተግበርያ) በስልክዎ ይጫኑ

18/10/2025

ምሳሌ 3
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁵ በፍጹም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን፥ በራስህም ማስተዋል አትደገፍ፤
⁶ በመንገድህ ሁሉ እርሱን እወቅ፥ እርሱም ጎዳናህን ያቀናልሃል።
⁷ በራስህ አስተያየት ጠቢብ አትሁን፤ እግዚአብሔርን ፍራ፥ ከክፋትም ራቅ፤
⁸ ይህም ለሥጋህ ፈውስ ይሆንልሃል፥ ለአጥንትህም ጠገን።

ነጻ ሶፍትዌር (መተግበርያ) በስልክዎ ይጫኑ

በኢትዮጵያ ሙ/ወ/አ/ቤ/ክ አለታና በንሳ አከባቢው ክልል የደንቢ ሙ/ወ/አ/ቤ/ክ                     👉ቀን 25/01/2018             መደበኛ የእሁድ አምልኮየቃል መልዕክ...
05/10/2025

በኢትዮጵያ ሙ/ወ/አ/ቤ/ክ አለታና በንሳ አከባቢው ክልል የደንቢ ሙ/ወ/አ/ቤ/ክ
👉ቀን 25/01/2018
መደበኛ የእሁድ አምልኮ
የቃል መልዕክት: ከመጋቢ ኃይሉ መጦ
ጥቅስ ሐጌ 2:8 ሐጌ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁸ ብሩ የእኔ ነው፥ ወርቁም የእኔ ነው፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር።
⁹ ከፊተኛው ይልቅ የዚህ የሁለተኛው ቤት ክብር ይበልጣል፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር፤ በዚህም ስፍራ ሰላምን እሰጣለሁ፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር።
1ዜና 29:10 1 ዜና 29
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁰ ዳዊትም በጉባኤው ሁሉ ፊት እግዚአብሔርን ባረከ፤ ዳዊትም አለ፦ አቤቱ፥ የአባታችን የእስራኤል አምላክ ሆይ፥ ከዘላለም እስከ ዘላለም ተባረክ።
¹¹ አቤቱ፥ በሰማይና በምድር ያለው ሁሉ የአንተ ነውና ታላቅነትና ኃይል፥ ክብርም፥ ድልና ግርማ ለአንተ ነው፤ አቤቱ፥ መንግሥት የአንተ ነው፥ አንተም በሁሉ ላይ ከፍ ከፍ ያልህ ራስ ነህ።
¹² ባለጠግነትና ክብር ከአንተ ዘንድ ነው፥ አንተም ሁሉን ትገዛለህ ኃይልና ብርታት በእጅህ ነው ታላቅ ለማድረግ፥ ለሁሉም ኃይልን ለመስጠት በእጅህ ነው።
¹³ አሁንም እንግዲህ፥ አምላካችን ሆይ፥ እንገዛልሃለን፥ ለክቡር ስምህም ምስጋና እናቀርባለን።
¹⁴ ሁሉ ከአንተ ዘንድ ነውና፥ ከእጅህም የተቀበልነውን ሰጥተንሃልና ይህን ያህል ችለን ልናቀርብልህ እኔ ማን ነኝ? ሕዝቤስ ማን ነው?
ርዕስ:የገንዘብ አያያዝና አስተዳደር
👉እግዝአብሔር በአደራ የሰጠንን ገንዘብ በአግባቡ ማስተዳደር አለብን።
👉ገንዘብ የእኛ አይደለም ከጌታ የተሰጠን እንጅ።
👉ገንዘብ በአግባብ ካልተጠቀምንበት የጥፋት ምንጭ ነው።
👉ገንዘብ መገልጌያችን እንጂ ጌታችን አይደለም።
👉ከገብያችን በቅድምያ የጌታን መለየት አለብንደ

07/09/2025
31/08/2025

Address

Bensa
Awassa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Denb full gospel believers church posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Denb full gospel believers church:

Share