ዘባቤን ሚዲያ

👉🇷🇺💒🥰🇷🇺 ወርቃማውና ማራኪው የሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ባለ ዐሥራ ሁለት ጉልላት ቤተክርስቲያን🇷🇺🥰💒🇷🇺
09/08/2026

👉🇷🇺💒🥰🇷🇺 ወርቃማውና ማራኪው የሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ባለ ዐሥራ ሁለት ጉልላት ቤተክርስቲያን🇷🇺🥰💒🇷🇺

09/08/2026

"የተሰወረ መና ያለብሽ ንጹሕ የወርቅ መሶብ አንቺ ነሽ ፤ መናም ከሰማይ የወረደውና ለዓለም ሁሉ ሕይወትን የሚያድለው ኅብስት ነው ቅድስት ሆይ ለምኝልን"
የእሁድ ውዳሴ ማርያም

09/08/2026

እጃችን ከሚመጸውተው ገንዘብ በላይ አንደበታችን የሚመጸውተው ምጽዋት እጅግ የበዛና የሰዎችን ሕይወት የሚቀይር ነው እርሱም ሰዎችን የሚያበረታና የሚያጽናና የፍቅርና የርህራሄ ቃል መናገር ነው።

ፍልሰታ ምን ማለት ነው?ፍልሰታ ማለት ‹ፈለሰ – ተሰደደ› ከሚለው ግሥ የወጣ ነው፡፡ ‹ፍልሰት› ማለት ደግሞ የተለያየ ትርጕም ቢሰጠውም ‹ፍልሰታ ለማርያም› ተብሎ ሲገለጽ እመቤታችን ቅድስት ...
08/08/2026

ፍልሰታ ምን ማለት ነው?

ፍልሰታ ማለት ‹ፈለሰ – ተሰደደ› ከሚለው ግሥ የወጣ ነው፡፡ ‹ፍልሰት› ማለት ደግሞ የተለያየ ትርጕም ቢሰጠውም ‹ፍልሰታ ለማርያም› ተብሎ ሲገለጽ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከሚያልፈው ወደ ማያልፈው ዓለም ከመቃብር የወጣችበት (የተነሣችበት) ቀን ማለት ነው፡፡ ወይም ደግሞ ከሥጋዊው ዓለም ወደ መንፈሳዊው ዓለም የተሸጋገረችበት ማለት ነው፡፡››

'ፍልሰታ ለማርያም' የሚለው የግእዝ ቃል ሲኾን ‹ፍልሰታ› ማለት ደግሞ ‹ፈለሰ› ከሚል ግሥ የተገኘ ነው፡፡ ‹ፍልሰት› ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ መሔድን (መፍለስን) ያመለክታል፡፡

እመቤታችን ካረፈች በኋላ የሥጋዋን መፍለስ አስመልክቶ ሐዋርያት የእመቤታችን ሥጋ የት እንደ ተቀበረ አላወቁም ነበርና እግዚአብሔር የእመቤታችንን ሥጋ እንዲገልጥላቸው የጾሙት ጾም ነው፡፡

ሐዋርያት ኹለት ሱባዔ ጾመው የእመቤታችንን ሥጋዋን ሰጥቷቸው ትንሣኤዋንና ዕርገቷን በማየት በረከት ያገኙበት ጾም ነው፡፡ ስለኾነም ምእመናን ፍልሰታ ለማርያምን ከልጅ እስከ አዋቂው በጾም በጸሎትና በመቍረብ በጋራ በፍቅር፣ በሰላም ያሳልፉታል፡፡››

ቅዱስ ዮሐንስ እመቤታችንን እንዲጠብቃት ከተደረገ በኋላ ሐዋርያት ‹‹የእመቤታችን ነገር እንዴት ነው?›› ብለው በጠየቁት ጊዜ ‹‹እመቤታችንማ በገነት በዕፀ ሕይወት ሥር ናት›› ብሎ ነገራቸው፡፡

በዚህ ጊዜ ሐዋርያት እመቤታችን ከመቃብር መነሣቷንና ማረጓን ማየት አለብን፤ እንዴት ዮሐንስ አይቶ እኛ ሳናይ እንቀራለን ብለው በመንፈሳዊ ቅናት በመነሣሣት ነሐሴ አንድ ቀን በዕለተ ሰኞ ሁለት ሰባት ሱባዔ ያዙ፡፡

በዐሥራ አራተኛው ቀን ጌታችን የእመቤታችንን ሥጋ አንሥቶ ሰጣቸውና በጌቴሴማኒ ቀበሯት፡፡ እመቤታችን በ፷፬ ዓመቷ ጥር ፳፩ ቀን ዐርፋ ነሐሴ ፲፬ ቀን ተቀብራለች፡፡

ይኹንና ሐዋርያት ቢቀብሯትም ትንሣኤዋንና ዕርገቷን አላዩም ነበር፡፡ ትንሣኤዋንና ዕርገቷን ያየው ሲቀብሯት ያላየው ሐዋርያው ቶማስ ነው፡፡

ቶማስ እንዲያስተምር ሕንድ አገር ዕጣ ደርሶት አስተምሮ በደመና ሲመለስ ነሐሴ ፲፮ ቀን እመቤታችን ስታርግ ሕዋ ላይ ተገናኙ።

ምእመናን ጾመ ፍልሰታ የእመቤታችን ዕረፍት፣ ትንሣኤና ዕርገቷ የሚዘከርበት ከሰባቱ አጽዋማት አንዱ የኾነ ጾም ነው፡፡ በየዓመቱ ሕፃን አዋቂው ሳይቀር የእመቤታችን ፍቅር አድሮባቸው ጾሙን ይጾማሉ፣ ያስቀድሳሉ፤ ይቈርባሉ፡፡

የፍልሰታን ጾም ከሌሎቹ አጽዋማት ልዩ የሚያደርገው ምንድን ነው?

የፍልሰታን ጾም ከሌሎቹ አጽዋማት ልዩ የሚያደርገው ምንድን ነው?

ኢትዮጵያ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የዐሥራት አገር በመኾኗ እና ሕዝበ ክርስቲያኑ ለእመቤታችን ልዩ ፍቅር ስላላቸው መሬት ላይ እየተኙ፣ ጥሬ እየበሉ በሰላም በፍቅር ይጾሙታል፡፡

ምእመናን ፍልሰታን ከሌሎች አጽዋማት በተለየ መልኩ መሬት ላይ እየተኙ ይጾሙታል፡፡ ይህ ደግሞ የእመቤታችን ፍቅር ስለሳባቸው ነው፤፡፡

ይቆየን

ድንግል ሆይ ዘንዶውና የግብር ልጆቹ ይጠሉሻል ፥ በልጅሽ ደም የዳንን እኛ ኦርቶዶክሳውያን ግን ከራሳችን በላይ እንወድሻለን ።
06/08/2026

ድንግል ሆይ ዘንዶውና የግብር ልጆቹ ይጠሉሻል ፥ በልጅሽ ደም የዳንን እኛ ኦርቶዶክሳውያን ግን ከራሳችን በላይ እንወድሻለን ።

🔴 «ፍልሰታ» የሚለው ቃል «ፈለሰ» ከሚለው የግዕዝ ግሥ የተገኘ ሲሆን ትርጉሙም ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ መዛወር መሄድ ወይም ማደግ ማለት ነው። በዚህም መሠረት ፆመ ፍልሰታ የእመቤታችን ቅ...
06/08/2026

🔴 «ፍልሰታ» የሚለው ቃል «ፈለሰ» ከሚለው የግዕዝ ግሥ የተገኘ ሲሆን ትርጉሙም ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ መዛወር መሄድ ወይም ማደግ ማለት ነው። በዚህም መሠረት ፆመ ፍልሰታ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ቅዱስ ሥጋ ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ መዛወሩን ፣ ከሞት ተለይታ መነሣቷንና ወደ ሰማይ ማረጓን የሚያስብ ፆም ነው።

✍️"እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዚህ ዓለም ፷፬ (64) ዓመት ካኖረች በኋላ ጥር ፳፩ ቀን አረፈች። በወቅቱ ቅዱሳን ሐዋርያት ሥጋዋን አክብረው ወደ ጌቴሴማኒ መቃብር ሊወስዱት ሲሉ አይሁድ በቅናት ተነሥተው «ሥጋዋን አቃጥለን እናጥፋ» በማለት ሊቀሙአቸው ሞከሩ። በዚህ ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ የእመቤታችንን ሥጋ ከወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ ጋር ነጥቆ ወደ ገነት ወስዶ በዕፀ ሕይወት ሥር አኖረው።

ሐዋርያት የእመቤታችንን ሥጋ በማጣታቸው እጅግ አዘኑ ፤ እንደ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሁሉ የእመቤታችንም ትንሣኤ እርገት ለማየት ፤ ሥጋዋን አግኝተው ለመቅበር ተመኙ።

✍️ ሐዋርያት የእመቤታችንን ቅዱስ ሥጋ እንዲገልጥላቸውና እንዲሰጣቸው በመመኘት ከነሐሴ ፩ ቀን ጀምረው ሱባኤ ገቡ ፤ እግዚአብሔርንም በፆምና በጸሎት ለመኑ። እግዚአብሔር አምላክም የሐዋርያትን ጸሎትና ልመና ሰምቶ በነሐሴ ፲፬ ቀን የእመቤታችንን ሥጋ ሰጣቸው። ሐዋርያትም በታላቅ ክብርና ምስጋና በጌቴሴማኒ አጸድ ቀበሩት።
በሦስተኛው ቀን (ነሐሴ ፲፮ ቀን) ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እመቤታችንን ከሙታን ለይቶ አስነሥቶ ወደ ሰማይ አሳረጋት።

✍️ እመቤታችን በነሐሴ ፲፮ ቀን ስታርግ ከሐዋርያት መካከል አደራዋን ለመቀበል ያልነበረው ቅዱስ ቶማስ በደመና ተጫኖ ከሕንድ ሀገር ሲመጣ እመቤታችን ስታርግ አገኛት። እርሱም «ቀድሞ የልጅሽን ትንሣኤ ሳላይ ቀረሁ ፤ ዛሬ ደግሞ ያንቺን ትንሣኤ ሳላይ ቀረሁ» ብሎ አዘነ። እመቤታችንም አጽናናችው ከተገነዘችበት ሰበን ሰጥታው ወደ ሰማይ አረገች።

ቶማስ ወደ ሐዋርያት ዘንድ በአገኘ ጊዜ እመቤታችንን መቅበራቸውን ነገሩት ፤ እርሱም «እኔ ሳላይ አላምንም» ያላቸው ወደ መቃብሩ ሂደው ሲከፍቱት ሥጋዋን አጡት። በዚህ ጊዜ ቶማስ የእመቤታችንን እርገትና የሰጠችውን ሰበን አበሰራቸው። ሐዋርያትም ቶማስ ያየውን ትንሣኤና እርገት እኛም እንይ በማለት በሚቀጥለው ዓመት (ከነሐሴ ፩ እስከ ፲፮) ዳግመኛ ሱባኤ ያዙ። በ፲፮ኛው ቀን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እመቤታችንን መንበር ቅዱስ ጴጥሮስን ንፍቅ ቄስ ፣ ቅዱስ እስጢፋኖስን ዋና ዲያቆን አድርጎ ቅዳሴ ቀድሶ ቁርባን አቁርቧቸዋል ትንሣኤዋንና እርገቷንም በአይናቸው አይተዋል።

✍️ በዚህ ከጥንት ጀምሮ ምእመናን በነሐሴ ወር ከነሐሴ ፩ እስከ ፲፮ ባሉት ፲፮ ቀናት ወደ ቤተ ክርስቲያን በመመላለስ በቁርባን፣ በፆምና በጸሎት፣ በሱባኤ ያሳልፋሉ።

በነሐሴ ወር ሕፃናትና ወጣቶች በደስታ ቤተ ክርስቲያን የሚያገለግሉበት ፣ የማኅበርና የአንድነት ፍቅር የሚገለጥበት ታላቅ ወቅት ነው።

✍️"እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለፍጥረታት ሁሉ የምትለምንና የምታማልድ እናት በመሆኗ፣ በዚህ ፆም ምእመናን በምልጃዋ ተስፋ በማድረግ የበረከቷ ተካፋይ ይሆናሉ።

♦️➨በድጋሚ እንኳን አደረሳችሁ ። አምላካችን እግዚአብሔር የፆሙን ጊዜ የሰላም የፍቅርና የበረከት ያድርግልን። የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነትና በረከት አይለየን አሜን!

💔 የትውልድ ድልድያችን፣ የታሪክና የባህል ጠባቂያችን ሄደ…​"የአረጋውያን ህልፈት ያልተጻፈ ትልቅ መጽሐፍ እንደመቃጠል ይቆጠራል" ይባላል ። ዛሬ ለእኔና ለማህበረሰባችን ያ የጥበብና የታሪክ ...
03/08/2026

💔 የትውልድ ድልድያችን፣ የታሪክና የባህል ጠባቂያችን ሄደ…
​"የአረጋውያን ህልፈት ያልተጻፈ ትልቅ መጽሐፍ እንደመቃጠል ይቆጠራል" ይባላል ። ዛሬ ለእኔና ለማህበረሰባችን ያ የጥበብና የታሪክ ጎተራ የነበሩት ውዱ አያታችን ወደ አምላካቸው ሄደዋል ።
​ከእሳቸው ጋር አብሮ የሄደው ታሪክ ፣ ባህልና ዕውቀት በቀላሉ የሚተካ አይደለም ።

የሰላም ወላጅ አባ ዲማዊ በማህበረሰቡ ውስጥ ቅሬታዎችና ውዝግቦች ሲነሱ በበሰለ ምክራቸውና በሽምግልናቸው የሚፈቱ ፣ የሰላም አባት ነበሩ ። እሳቸውን ማጣት ለሁላችንም ትልቅ ክፍተት ነው ።

አያታችን አባ ዲማዋ በየነ ሆይ ​​የሰጡንን የምርቃትና የበረከት ከለላ ፣ መልካም እሴት ፣ ፍቅርና ምክር እስከወዲያኛው በልባችን አምቀን እኖራለን ።
ፈጣሪ ​ነፍስዎን በገነት ያኑርልን ! ሁሌም በልባችን ውስጥ ይኖራሉ ።
Teshale Humando

01/08/2026

ተክለ ሃይማኖት(2x)
ትባርከን ዘንድ ና (4)

ጉሙዘኛ መዝሙር (በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ካማሽ ዞን)

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!የተከበራችሁ!በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የምትኖሩ የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እምነት ተከታዮችና ምዕመናን በሙሉ፤...
27/07/2026

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

የተከበራችሁ!በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የምትኖሩ የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እምነት ተከታዮችና ምዕመናን በሙሉ፤

እነሆ በንጉስ ተክለ ሀይማኖት በ1886 ዓ/ም እንደተመሠረች የታሪክ ድርሳናት ያስረዱላትና በመተከል ዞን ወምበራ ወረዳ በደብረ-ዘይት ከተማ የምትገኘው የታሪካዊቷና ጥንታዊቷ ደብረ ዘይት ደብረ ምጥማቅ ቅድስት ማሪያም ገዳም እጅግ እድሜ ጠገብ ከመሆኗ ጋር ተያይዞ የመፍረስ አደጋ እንዳይደርስባት በአዲስ መልክ በቅርቡ ታሪካዊ ይዘቷን ሳትለቅ እጅግ ባማረና በተዋበ መንገድ ለማሠራትና ለማነፅ እንቅስቃሴ እንደተጀመረ ይታወቃል።

በመሆኑም የቤተክርስቲያኗን የህንፃ ግንባታ ለማስጀመር በህንፃ አሰሪ ኮሚቴ በኩል የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን በማጠናቀቅ የቤተክርስቲያን ህንፃ ግንባታ ለማከናወን የመጀመሪያው ምዕራፍ የሆነውን የግንባታ ቦታ የማፅዳት ስራ በዛሬው ዕለት በይፋ ተጀምሯል።

በዚህም መሰረት በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የምትኖሩ የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እምነት ተከታዮችና ምዕመናን የህንፃ ግንባታ ስራው የተጀመረ መሆኑን አውቃችሁ በገንዘብ፣በዕውቀት፣በአይነትና ቁሳቁስ፣ በጉልበት እንዲሁም በቅዱስ ምክራችሁና ጸሎታችሁ ለቅድስት ቤተክርስቲያኗ ድጋፍ ታደርጉ ዘንድ በልዑል እግዚአብሔር ስም ቤተክርስቲያኗ ጥሪዋን አቅርባለች።

ኑ!ታሪካዊቷና ጥንታዊቷን ደብረ ዘይት ደብረ ምጥማቅ ቅድስት ማሪያም ገዳምን በጋራ በመገንባት ዘላለማዊ ህይወትን እናትርፍ!!!

ድጋፍ ለምታደርጉ ውድ ምዕመናን በቤተክርስቲያኗ ህጋዊ የባንክ ሂሳብ ቁጥር በኩል የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ = 1000539306344

አዋሽ ባንክ=013521148762301
ላይ ድጋፍ ማድረግ የምትችሉ መሆኑን በአክብሮት እንገልፃለን።

#የደብረ ዘይት ደብረ ምጥማቅ ቅድስት ማሪያም ገዳም ህንፃ አሰሪ ኮሚቴ!

የተወደዳችሁ ወንድም እህቶቼ እንኳን ለሐምሌ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል በሰላምና በጤና አደረሳችሁ !​ሠልስቱ ደቂቅን ከነበልባሉ እሳት ያዳነው ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል የሕይወታችንን እሳት ...
26/07/2026

የተወደዳችሁ ወንድም እህቶቼ እንኳን ለሐምሌ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል በሰላምና በጤና አደረሳችሁ !

​ሠልስቱ ደቂቅን ከነበልባሉ እሳት ያዳነው ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል የሕይወታችንን እሳት ያብርድልን ፣ ለቤታችንና ለሀገራችን የደስታና የሰላም የምሥራች ያብስረን !

Address

Asosa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ዘባቤን ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to ዘባቤን ሚዲያ:

Shortcuts

Share