Lutherans gallery Asella

Lutherans gallery Asella “ጻድቅ በእምነት ይኖራል ተብሎ እንደ ተጻፈ የእግዚአብሔር ጽድቅ ከእምነት ወደ እምነት በእርሱ ይገለጣልና።" ሮሜ 1:17

ጌታ ክብሩን ይውሰድ ድንቅ ጊዜ ነበረን ሁለተኛ አመት የልጆች ኮንፍራንስ 🥰🥰🥰
09/05/2026

ጌታ ክብሩን ይውሰድ ድንቅ ጊዜ ነበረን ሁለተኛ አመት የልጆች ኮንፍራንስ 🥰🥰🥰

የቤተክርስቲያናችን ፕሬዚዳንት ቄስ አወቀ ጨፋ በChristian leadership የማስተርስ ዲግሪ በመመረቅዎ እርስዎ እና ቤተሰብዎ እንዲሁም ቤተክርስቲያን በመላው እንኳን ደስ ያለን!Congr...
08/05/2026

የቤተክርስቲያናችን ፕሬዚዳንት ቄስ አወቀ ጨፋ በChristian leadership የማስተርስ ዲግሪ በመመረቅዎ እርስዎ እና ቤተሰብዎ እንዲሁም ቤተክርስቲያን በመላው እንኳን ደስ ያለን!

Congratulations to our church president, Rev. Aweke Chefa, and, his family and, the entire church, on his graduation with Master's degree in Christian leadership!

ትንቢተ ሚልክያስ 3:6 ••••••••••⁶ እኔ እግዚአብሔር አልለወጥም፤ እናንተ የያዕቆብ ልጆች ሆይ፥ ስለዚህ የጠፋችሁ አይደላችሁም።👆👆👆👆👆ነገ ማክሰኞ ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ ለዩ የእናቶች ...
04/05/2026

ትንቢተ ሚልክያስ 3:6
••••••••••
⁶ እኔ እግዚአብሔር አልለወጥም፤ እናንተ የያዕቆብ ልጆች ሆይ፥ ስለዚህ የጠፋችሁ አይደላችሁም።
👆👆👆👆👆
ነገ ማክሰኞ ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ ለዩ የእናቶች እና የእህቶች ፕሮግራም በአሰላ ሉተራን ቤተክርስቲያን አይቀርም

03/05/2026

ማቴዎስ 19:14፦ "ኢየሱስ ግን፦ ሕፃናትን ተዉአቸው፥ ወደ እኔም ይመጡ ዘንድ አትከልክሏቸው፤ መንግሥተ ሰማያት እንደነዚህ ላሉ ናትና አላቸው።" 2ተኛ አመት ልዩ የልጆች እና የወላጆች አመታዊ ኮንፍራንስ በአሰላ ወንጌላዊት ሉተራን ቤተክርስቲያን 👉ቅዳሜ ግንቦት 1 ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ ልጆች ተዘጋጅተው ይጠብቃቹሀል 🥰🥰 በዕለቱ ልጆች በዝማሬ በፀሎት በድራማ በኬሮግራፊ በልዩ አዝናኝ ዜናዎች ይቀርባሉ ሁላችሁም ተጋብዛቹሀል ወላጆች ከልጆቻቹ ጋ እንዳትቀሩ 🥰🥰

መጽሀፍ እንደሚል:"“ነፍስ እውቀት የሌለባት ትሆን ዘንድ መልካም አይደለም....”  — ምሳሌ 19፥2 በቤተክርስቲያናችን አስተምህሮ ላይ የተዘጋጀው ትምህርት ከነገ እሁድ ሚያዝያ 25 ቀን 20...
02/05/2026

መጽሀፍ እንደሚል:"“ነፍስ እውቀት የሌለባት ትሆን ዘንድ መልካም አይደለም....”
— ምሳሌ 19፥2
በቤተክርስቲያናችን አስተምህሮ ላይ የተዘጋጀው ትምህርት ከነገ እሁድ ሚያዝያ 25 ቀን 2018ዓ.ም ከሰዓት በኃላ ጀምሮ በተከታታይ በ15 ቀናት በሚደረገው የወጣቶቾ ፕሮግራም ላይ ስለሚሰጥ: ሁላችን በቤተክርስቲያን ተገኝተን ትምህርቱን እንድንከታተል ይሁን!
ጌታ ኢየሱስ ይባርካችሁ።

 🎚️📌“እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን።” ትንቢተ ኢሳያስ 53፡5📌ይህ ቃል ነብዩ ኢሳያ...
05/04/2026

🎚️

📌“እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን።” ትንቢተ ኢሳያስ 53፡5

📌ይህ ቃል ነብዩ ኢሳያስ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ከእናቱ ከድንግል ማርያም ከመወለዱ ከ540–550 ዓመተ አለም በፊት በእግዚአብሔር መንፈስ ተመርቶ ስለ ስቃዩና ሞቱ ዋንኛ ምክኒያት የተናገረው አስደናቂ መለኮታዊ መልዕክት ነው፡፡

📌ሁሉ በርሱ ለእርሱ የተፈጠረው፣ፍጹም አምላክ የሆነው የእግዚአብሔር ልጅ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው ሆኖ ወደ ምድር የመጠበት ዓላማ በኃጢአት ምክኒያት ከፈጣሪው የተለየውን የሰው ልጅ በራሱ ከአብ ጋር ለማስታረቅ ነው፡፡

📌ጌታ ኢየሱስ በሞቱ እና ትንሳዔው የሰው ልጅ ሊያሟላ የማይችለው እና እግዚአብሔር የሚፈልገውን የጽድቅ ስራ በመስራት፤ሰውን ከእግዚአብሔር ከአምላኩ ጋር አስታረቀ፡፡

📌በዚህ የመስዋትነት ስራ ውስጥ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ የሰው ልጅ በኃጢአት ምክኒያት ሊደርስበት የሚችለውን የእግዚአብሔር ቁጣ ወደ እራሱ ወሰደው፡፡ በምትኩም በእምነት በኩል የእግዚአብሔር ጽድቅ የምንካፈልበትን ዕድል አስገኘልን፡፡

📌በመስቀል ላይ የሰው ልጅ በደልና ኃጢአት ሁሉ በጌታ ኢየሱስ ላይ ሆነ፤እርሱ ስለ እኛ ቆሰለ፣ደማ፣ተሰቃየ፣ሞተ፣የእግዚአብሔር ቁጣ በርሱ ላይ አረፈ፡፡

📌ኃጢአያት የሌለበት ቅዱሱ የእግዚአብሔር ልጅ፣ስለ እኛ ኃጢአት ሆነ፡፡(2ኛ ቆሮ.5›21) በሞቱ የኃጢአት ስርየትን ተቀበልን! (ሐዋ.10፡43፣ኤፌ 1፡7) በደሙ የበደላችን ዕዳችን ታጠበ!(ቆላ.2፡14) በትንሳዔው ጽድቅ ሆነልን! (ሮሜ 4፡24-25) በሞቱ እና የዘላለም ህይወትና አገኘን! (ዮሀ.3፡16)
🎚️በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን!

📌ይህ የህማማት ሳምንት ይህንን ታላቅ እውነት በማሰብ፣የእግዚአብሔር ቃል በማንበብና በማጥናት፣የጌታን እራት በጋራ በመካፈል፣ እንዲሁም በፆምና በጸሎት የምንቆይበት ሳምንት ይሁንልን!

🎚️ዝማሬያችንም እንዲህ የሚል ይሁን?

፩ የተናቀ ሰውም የጠላው ነበር
ያ የሞተልን የሞተልን።
ተጨነቀ ተሠቃየም በጻር
ግሩም ኃይል አለ በደሙ።
ግሩም ኃይል ኃይል አለ በደሙ
በየሱስ ክርስቶስ ደም።
ኃይል አለ ድንቅ ሥራ የሚሠራ
በከበረው በየሱስ ደም።
፪ የጌታህን ደም ታስባለህን?
ያ የሞተልን የሞተልን።
ነፍሴ ትረሺ ይሆን ቀራንዮን
ግሩም ኃይል አለ በደሙ።
ግሩም ኃይል . . .።
፫ የሱስ አዳኙን ታስባለህን
ያ የሞተልን የሞተልን
በንባው የራሰው ጌቴሴማኒን?
ግሩም ኃይል አለ በደሙ።
ግሩም ኃይል . . .።
፬ የጌታን ሕማም ትረሳለህን?
ያ የሞተልን የሞተልን
በቅዱስ ደሙ አነጻው ሁሉን
ግሩም ኃይል አለ በደሙ።
ግሩም ኃይል . . .።
ተ. ኤ. ቦ.

ለሁላችንም!!
16/01/2026

ለሁላችንም!!

የአሰላ ሉተራን አጥቢያ ቤተክርስቲያን ቀደምት ጉባዔ። ሰዎች ይወለዳሉ፣ ይኖራሉ፣ ይሞታሉ፤አምላካችን እግዚአብሔር ግን ሁሌም ያው ነው።" እኔ እግዚአብሔር አልለወጥም፤"—ሚልክያስ 3:6An ol...
15/01/2026

የአሰላ ሉተራን አጥቢያ ቤተክርስቲያን ቀደምት ጉባዔ። ሰዎች ይወለዳሉ፣ ይኖራሉ፣ ይሞታሉ፤አምላካችን እግዚአብሔር ግን ሁሌም ያው ነው።
" እኔ እግዚአብሔር አልለወጥም፤"
—ሚልክያስ 3:6

An old version of the Asella Lutheran Congregation. People are born, live, and die. But our God is the same always.
"For I, the LORD, do not change."
-Malachi 3:6

ኑና የእግዚአብሄርን ፀጋ አብረን እንካፈል ሁላቹም ተጋብዛቹሀል 🙏🙏
06/11/2025

ኑና የእግዚአብሄርን ፀጋ አብረን እንካፈል ሁላቹም ተጋብዛቹሀል 🙏🙏

Address

Asella

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Lutherans gallery Asella posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share