ማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ማዕከል ሚዲያ Waldaa Qulqullootaa Wiirtuu Ciroo

ማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ማዕከል ሚዲያ  Waldaa Qulqullootaa Wiirtuu Ciroo Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ማዕከል ሚዲያ Waldaa Qulqullootaa Wiirtuu Ciroo, Religious Center, Asebe Teferi.

23/05/2026
ማአዕከሉ ለባለ እድለኞች የወጣላቸውን  እጣ አስረከበ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።ማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ማዕከል ለጽህፈት ቤት ግንባታ ፕሮጀክት ሲሸጥ የነበረውን እጣ ቲኬት ...
16/05/2026

ማአዕከሉ ለባለ እድለኞች የወጣላቸውን እጣ አስረከበ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

ማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ማዕከል ለጽህፈት ቤት ግንባታ ፕሮጀክት ሲሸጥ የነበረውን እጣ ቲኬት እጣው ለወጣላቸው ሰዎች አስረከበ ።

በዛሬው እለት በተካሔደው ርክብብ መርሐ ግብር 1ኛ እጣ Sapphire 43 ኢንች ቴሌቪዥን የወጣላቸው ዲ/ን ሲሳይ ከበዴሳ መጥተው የወጣላቸውን 43 ኢንች ቴሌቪዥን የማእከሉ ሰብሳቢ ዲ/ን ዳንኤል ሞገስ እና የህንጻ አሰሪ ኮሚቴ ሰብሳቢ የሆኑት ወ/ሮ ንጹህ ፍስሐ ባሉበት ተረክበዋል።

ሌሎች ባለ እድሎች በሀገር ባለመኖራቸው በተመቻቸው ጊዜ በመምጣት የወጣላቸውን ንብረት እንደሚወስዱ በርክክቡ ወቅት ተገልጿል።

14/05/2026

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

ግንቦት ፮/፳፻፲፰ ዓ.ም

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ የሆነችው ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን ሲኖዶሳዊ በመሆኗ አበው ቅዱሳን በፍትሕ መንፈሳዊና በጉባኤ አድያም ዘአንጾኪያ “ወይኩን ሲኖዶስ ዘጳጳሳት ፪ተ ጊዜያተ በበዓመት - የጳጳሳት ጉባኤም በዓመት ሁለት ጊዜ ይሁን” ብለው በደነገጉት ቀኖና መሠረት፤ በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ የሚመራው፣ የሐዋርያት መንበር ወራሽ የሆነው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የርክበ ካህናት ምልአተ ጉባኤውን በኅብረተ መንፈስ ቅዱስ ከሚያዝያ 28 እስከ ግንቦት 6 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ አካሄዷል፡፡

ምልአተ ጉባኤው ስለ ሀገር ሰላም፣ ስለ ቤተ ክርስቲያን አንድነት፤ ስለ ሰው ልጅ ሁሉ ደኅንነትና ክብር፣ በአጠቃላይ ወቅታዊ ጉዳዮችን በተመለከተ ሰፊ ውይይቶችን በማድረግ ዘመኑን የዋጁ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡ ከውሳኔዎቹም መካከል፡-

የቤተ ክርስቲያናችንን አንድነት መጠበቅና ማስጠበቅ የቅዱስ ሲኖዶስ ተግባር በመሆኑ ጥንታዊትና ሐዋርያዊት የሆነችውን ቤተ ክርስቲያን በአንድነቷና በሉዓላዊነቷ እንደተረከብናት ለወደፊቱም ሉዓላዊ ክብሯ ተጠብቆ እንድትቀጥል በምልዓተ ጉባኤው የተሠየመው በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የሚመራው “የሀገራዊ ሰላምና የቤተ ክርስቲያን አንድነት” ኮሚቴ ሥራውን አጠናክሮ እንዲቀጥል ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ፍጹም ሰላማዊ ሆኖ በተረጋጋ መንገድ እንዲካሄድ፣ ለሀገር ሰላምና ለሕዝብ አንድነት በሚጠቅም ሁኔታ እንዲጠናቀቅ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የምትጸልይ ሲሆን ምርጫው በሁሉም ወገን ለኢትዮጵውያን ዘላቂ ሰላምንና መረጋጋትን የሚያስገኝ ሆኖ እንዲፈጸም ቅዱስ ሲኖዶስ በአጽንዖት ያሳስባል፡፡

ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የአርሲ ሀገረ ስብከትን በሊቀ ጵጵስና በቋሚነት እንዲመሩ፣ ሕዝቡን እንዲያጽናኑ እየደረሰ ያለውን ችግር ከቋሚ ሲኖዶስና በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ከሚመራው የሰላም ኮሚቴ ጋር በመሆን የሚመለከተውን የመንግሥት አካል በማነጋገር ዘላቂ መፍትሔ እንዲያፈላልጉ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ወስኗል፡፡

ከጥንት ጀምሮ “ቅዱስ ሲኖዶስ” በሚል ርእስ እየተዘጋጀ ይታተም የነበረው ታሪካዊ መጽሔት የቅዱስ ሲኖዶስ ቀኖናዊ ውሳኔዎችን በማካተት በቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት አስፈጻሚነት ሕትመቱ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

የቤተ ክርስቲያናችንን ደንቦች፣ መመሪያዎች መርምሮ ማጽደቅ የቅዱስ ሲኖዶስ ሉዓላዊ ሥልጣን በመሆኑ፡-

የስብከተ ወንጌል ሐዋርያዊ ተልእኮ ማስፈጸሚያ ደንብ በብፁዕ አቡነ ማርቆስ ሰብሳቢነት

የአንድነት ገዳማት ኅብረት መተዳደሪያ ደንብ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስና ብፁዕ አቡነ ማርቆስ ባሉበት በድጋሚ እንዲታይና ሌሎቹም ለውሳኔ የቀረቡ ደንቦች በሊቃውንትና በሕግ ባለሙያዎች ታርመው ለጥቅምት 2019 ዓ/ም ምልዓተ ጉባኤ እንዲቀርቡ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል

የቀድሞው የሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የነበሩት ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ “የቤተ ክርስቲያን ታሪክ በዓለም መድረክ”ና “የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ” በሚሉ አርእስት አዘጋጅተው ያሳተሟቸው መጻሕፍትን የማሳተምና የማሰራጨት የባለቤትነት መብት ከሚያዝያ 29 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ለዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳም እንዲሆን ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

ከተለያዩ አህጉረ ስብከት በቀረቡ ጥናቶችና የማጣራት ውጤቶች መሠረት፡-

የደቡብ ሱዳን ሀገረ ስብከት ከምሥራቅ አፍሪካ ሀገረ ስብከት ጋር ተደርቦ በብፁዕ አቡነ ማቴዎስ ሊቀ ጳጳስ እንዲመራ፤
ብፁዕ አቡነ ሩፋኤል ሊቀ ጳጳስ የጋምቤላንና የቤንሻንጉል ጉምዝ አህጉረ ስብከትን ብቻ እንዲመሩ፤
ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ የጅማ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጰስ የሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከትን እንደያዙ እንዲቀጥሉ፤
ብፁዕ አቡነ ኤፍሬም የቡኖ በደሌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የቄለም ወለጋ ሀገረ ስብከትን ደርበው በአባትነት እንዲመሩ፣
የኮንታ ዞን ሀገረ ስብከት እንዲሆን የቀረበው ጥያቄ የጸደቀ በመሆኑ ሀገረ ስብከቱ ራሱን ችሎ እንዲደራጅና በብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ ሊቀ ጳጳስ እንዲመራ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፤
የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የልማት ተግባራትን ምልዓተ ጉባኤው በከፍተኛ ደረጃ በማድነቅ፣ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመ/ፓ/ጠ/ቤ/ክ/ ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ሲቲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤ በአባታዊ አመራር የፈጸሙት አስደናቂ የሥራ አፈጻጸም በጉልህ የሚታይ ለውጥ፣ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን የሚጠቅም፣ ሉዓላዊ ክብሯን የሚያስጠበቅ፣ ለሁሉም አበው ምሳሌነት ያለው በመሆኑ ምልዓተ ጉባኤው እጅግ ከፍ ባለ ክብር አመስግኗል፡፡

በዚህም መሠረት በብፁዕ ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጁ አባታዊ መሪነት እየተከናወኑ ያሉት ተግባራት ማለትም፡-

የቤተ ክርስቲያንን ቀደምት ሠነዶች በዲጂታል ቴክኖሎጂ እንዲደራጁ የተደረገበት ስልት ተጠናክሮ እንዲቀጥል፤

ከ1970 ዓ/ም ጀምሮ በመጋዝን ተከማችተው የቆዩ በርካታ ልዩ ልዩ መጻሕፍትን የማሰራጨት ሂደት በተጀመረው መንገድ እንዲጠናቀቅ፤

ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን የኢንፎርሜሽንና ኮምኒኬሽን ተጠቃሚ እንድትሆን የተጀመረው ዘመኑን የዋጀ ቴክኖሎጂ በሁሉም የቤተ ክርስቲያናችን መዋቅር በየደረጃው ተጠናክሮ ተግባራዊ እንዲሆን፤

በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ሥር የተጀመሩ የሕንፃ ግንባታዎችና አጠቃላይ የልማት ሥራዎች በተያዘላቸው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት ተጠናቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ ሁሉም አህጉረ ስብከትና ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን አስተዋጽኦና ትብብር እንዲያደርጉ ቅዱስ ሲኖዶስ በአፅንዖት ያሳስባል፡፡

በሰሜን አሜሪካ የሰሜን ካሊፎርኒያ፣ ኔቫዳና አሪዞና ሀገረ ስብከት ኆኅተ ሰማይ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስና ቅድስት አርሴማ ገዳም የመንፈሳዊ ኮሌጅ፣ የአብነት ት/ቤት ሥርዓተ ትምህርት የቤተ ክርስቲያንን ዶግማ፣ ቀኖና፣ ታሪክና ትውፊት በጠበቀ መልኩ ተጠናክሮ መዋቅራዊ ተጠሪነቱም በአግባቡ ተጠብቆ ሥራ ላይ እንዲውል ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ያቀረበውን የ2019 ዓ/ም በጀት በማጽደቅ በተገቢው መንገድ ሥራ ላይ እንዲውል ምልአተ ጉባኤው ወስኗል፡፡

በመጨረሻም ቅዱስ ሲኖዶስ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት በተነጋገረባቸው ጉዳዮች በትኩረት የተወያየው የቤተ ክርስቲያናችንን ሁለንተናዊ ዕድገትና ተቋማዊ ሕልውና ስለማስጠበቅ ሲሆን በአሁኑ ጊዜ ሀገራችንን ጨምሮ በመላው ዓለም እየታየ ያለው ግጭትና የሰላም መታጣት በእጅጉ አሳስቦታል፡፡

በመሆኑም ስለ ዓለምና ስለ ሀገራችን ሰላም፣ ስለ ሰው ልጆች ደኅንነት፣ በየቦታው በሃማኖታቸው ምክንያት መከራ የሚደርስባቸውን በየቦታው የሚገኙና ግጭት ባለባቸው ቦታዎች ያሉ ኦርቶዶክሳውያንን በማሰብ በመጪው የ2018 ዓ/ም ጾመ ሐዋርያት በመላው ዓለም ባሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ገዳማት፣ አድባራትና አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ጸሎተ ምሕላ እንዲደርስ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

በመላው ዓለም፣ በደቡብ አፍሪካና በሳውዲ ዐረቢያ የሚኖሩ ዜጎቻችን ሰብአዊ መብት እንዲከበር፣ የርኅራኄ ምሕረትና ፍትሕ እንዲያገኙ የሚመለከታቸው አካላት ተገቢውን ክትትል እንዲያደርጉ ቅዱስ ሲኖዶስ ሐዋርያዊ ጥሪውን በማቅረብ ለሰባት ቀናት ሲያካሂድ የሰነበተውን ቀኖናዊ ጉባኤ ዛሬ ግንቦት 6 ቀን 2018 ዓ.ም. በጸሎት አጠናቋል፡፡

እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ
አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ
ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም
ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት
አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
ግንቦት 6 ቀን 2018 ዓ/ም
መረጃው ፡ የኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ነው።

በማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ማዕከል ለአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤት ለተማሪ ወላጆች ስልጠና ሰጠ።=====+++++++===============  በማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ማዕከል የአቡነ ጎርጎርዮስ ትም...
06/05/2026

በማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ማዕከል ለአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤት ለተማሪ ወላጆች ስልጠና ሰጠ።
=====+++++++===============
በማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ማዕከል የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤት ' የወላጅ ትጋት ለልጅ ስኬት' በሚል መሪ ቃል ለተማሪ ወላጆች በጨርጨር 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አዳራሽ የጭሮ ከተማ የትምህርት ፅ/ቤት ኃላፊ በተገኙበት የስልጠና የምክክር መርሐግብር አደረገ።
ለተማሪ ወላጆች 'የወላጅ ትጋት ለልጅ እና የቤት ውስጥ ትምህርት ቤት' በመ/ር ቦጋለ ኃይሉ እና 'ክርስትያናዊ የልጆች አስተዳድግ እና የሚዲያ አጠቃቀም' በቀሲስ ዳዊት በላይነህ የማዕከሉ የጽ/ቤት ኃላፊ ተሰጥቷል።
በስልጠናው የተገኙት የትምህርት ቢሮ ኃላፊ የሆኑት አቶ ደሜ መስቀለ ባስተላለፉት መልክት 'አቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤት የትምህርትን ጥራትን ለማሳካት በተለያየ ጊዜ ለመምህራን የአቅም ማሳደጊያ ስልጠና በተደጋጋሚ መሰጡትን ገልጸው የዛሬው ስልጠናም የዚህ ዓላማ አንዱ አካል ነው እና ሊበረታታ የሚገባ ሲሆን ትምርት ቤቱን የሚያስመሰግነው ተግባር ነው። አክለውም ስልጠናው ወላጆች ልጆቻቸው ውጤታማ እንዲሆኑ የሚያደርግ ግብዓት ስልሆነ ልንጠቀምበት ይገባል። በመጨረሻም የጭሮ ከተማ ትምህርት ቤሮ ጽ/ቤት ኃላፊው ለትምህርት ጥራት ወላጆች፣ መምህራን እና ትምህርት ቤሮም በጋራ መስራት ይገባል በማለት አሳስበዋል።
በመጨረሻም በስልጠናው የተሳተፋት የተማሪ ወላጆች ስልጠናው ለቤተሰብ ትልቅ ድጋፍ እና አስፈላጊና ጠቃሚ ስለሆነ በቤታችን በቀጣይ ለመተግበር በያዝነው ክረምት እንዘጋጃለን ብለዋል።
"ትውልድን የሚተካ ትውልድ በተሻለ ጥራት እናፈራለን"

28/04/2026

የጭሮ ማእከል ገቢ ማስገኛ ፕሮጀክት እጣ ወጣ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ማእከል አገልግሎቱን ለማሳለጥ የገቢ ማስገኛ ፕሮጀክት ቀርጾ እየተገበረ መሆኑ ይታወቃል። በመሆኑም ለዚህ ፕሮጀክት ገቢ ማሰባሰብ መርሐ ግብር ልዩ ልዩ የእጣ ቲኬት ሲሸጥ የነበረ ሲሆን የዚህ ቲኬት እጣ ማውጣት ስነስርአት ትናንት ምሽት በየወሩ በሚካሔደው የቅዱስ ገብርኤል ዝክር መርሐ ግብር ላይ ተካሒዷል በዚህ መሰረት:-

1ኛ እጣ 43 ኢንች ቴሌቪዥን ቲኬት ቁጥር 1508
2ኛ እጣ የውሃ ማጣርያ ቲኬት ቁጥር 649
3ኛ እጣ ሃይማኖተ አበው መጽሐፍ ቲኬት ቁጥር 484
የወጣ መሆኑ ታውቋል።
እጣ የወጣላችሁ እድለኞችን እንኳን ደስ አላችሁ እያልን የወጣላችሁን እቃ ማእከሉ ጽ/ቤት መጥታቸሁ መረከብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃን።

የእለተ አኮቴት መርሐ ግብር ተካሔደ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።ማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ማእከል እለተ አኮቴት መርሐ ግብር በጭሮ ደ/ሰ/ቅ/እግዚአብሔርአብ ቤተ ክርስቲያን አከናወነ  ።...
03/04/2026

የእለተ አኮቴት መርሐ ግብር ተካሔደ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

ማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ማእከል እለተ አኮቴት መርሐ ግብር በጭሮ ደ/ሰ/ቅ/እግዚአብሔርአብ ቤተ ክርስቲያን አከናወነ ። መርሐ ግብሩ የምስጋና እና የልመና መርሐ ግብር እንደመሆኑ መጠን ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ እስከ ቀኑ 5:00 ሰአት ድረስ ዳዊት ውዳሴ ማርያም እና የነቢያት ጸሎት ደርሷል የደብሩ ካህናት ጸሎተ ወንጌል አድርሰው የጸሎት መርሐ ግብሩ ተጠናቋል። በማስከተልም የወንጌል ትምህርት ተሰጥቶ ወደ ቅዳሴ የተገባ ሲሆን ከቅዳሴ መልስ የጋራ ማእድ መቋደስ ተግባር ተከናውኗል። በመርሐ ግብሩ የኦዳቡልቱም እና የአንድነት ጊቢ ጉባኤ አባላት ተሳታፊ ሆነዋል። የማኅበሩ መልእክት በማእከሉ ሰብሳቢ ተላልፎ የእለቱ መርሐ ግብር ተጠናቋል። ይህ መርሐ ግብር የማኅበሩ አባላት ላለፉት ዓመታት አገልግሎት ለእግዚአብሔር ምስጋና እና ለወደፊቱ አገልግሎታቸው ልመና የሚያቀርቡበት የምስጋና መርሐ ግብር መሆኑ ይታወቃል።

በጉጉት የምንጠብቀው ቀን ደርሷል ስለደረስን ያደረሰንን እግዚአብሔርን እናመሰግንበታለን ለከርሞ እንዲያደርሰን እንለምንበታለን። ከነገ ወዲያ።
01/04/2026

በጉጉት የምንጠብቀው ቀን ደርሷል ስለደረስን ያደረሰንን እግዚአብሔርን እናመሰግንበታለን ለከርሞ እንዲያደርሰን እንለምንበታለን። ከነገ ወዲያ።

ከነገ ወዲያ
01/04/2026

ከነገ ወዲያ

ማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ማእከል ሐዊረ ሕይወት አካሔደ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። ማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ማእከል በቀን ፳/፯/፳፻፲፰ ዓ.ም ወደ ጭሮ ደብረ ሲና ቅዱስ ዑራአኤ...
31/03/2026

ማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ማእከል ሐዊረ ሕይወት አካሔደ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። ማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ማእከል በቀን ፳/፯/፳፻፲፰ ዓ.ም ወደ ጭሮ ደብረ ሲና ቅዱስ ዑራአኤል ቤተ ክርሰቲያን ፲፪ኛ ዙር የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር አካሔደ።

መርሐ ግብሩ ከወረዳ ማእከላት የመጡ በመቶዎች የሚቆጠሩ ምእምናንና ካህናት ተሳትፈውበታል።
ከአዲስ አበባ በመጡ መምህራን በሁለት ክፍል የወንጌል መርሐ ግብር የተሰጠ ሲሆን ከምእመናን ለቀረቡ ጥያቄዎችመ‍እ በሁለት ክፍል የምክረ አበው መርሐ ግብር መልስ ተሰጥቶበታል። በእለቱ በደብሩ ሰ/ት/ቤት መዘምራን እና በማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ማእከል መዘምራን የበገና እና ሌሎች ዝማሬዎች ቀርበዋል።

የደብሩ አስተዳዳሪ ሊቀ ብርሃናት ቀሲስ ወንደወሰን ስለ ደብሩ አመሰራረት እና አሁን ላይ እየተሰሩ ስላሉት የይዞታ ማስፉፊያ ስራዎች ማብራሪያ ከሰጡ በኋላ ሁሉም ክርስቲያን ደብሩ እየተገበረ ላለው የልማት ስራ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት ጥሪ አቅርበው መርሐ ግብሩን ላዘጋጀው ማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ማእከልም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

በመቀጠልም የማእከሉ ጽ/ቤት ኃላፊ ቀሲስ ዳዊት በላይነህ ስለ ማእከሉ አገልግሎት አጠር ያለ ማብራሪያ ከሰጡ በኋላ ምእመናን ማእከሉን ቀርበው አብረው እንዲያገለግሉ ጥሩ አቅርበዋል። የጽ/ ቤት ኃላፊው
ሐዊረ ሕይወቱ የተካሔደበት ደብረ ሲና ቅዱስ ዑራኤል በማኅበረ ቅዱሳን የስብከት ኬላ ተጀምሮ ወደ ደብርነት ያደገ መሆኑን አስታውሰው ደብሩን ለማልማት ሁሉም ክርስቲያኖች እንዲረባረቡ ጥሪ አቅርበዋል። መርሐ ግብሩ በማእከሉ ሕዝብ ግንኙነት እና ሚዲያ ዋና ክፍል ስር በተቋቋመ ኮሚቴ የተዘጋጀ እና በውጤት የተጠናቀቀ መሆኑን የዋና ክፍሉ ኃላፊ አቶ ሐብታሙ አጥሌ ገልጸዋል።

በእለተ ደብረ ዘይት በማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ማዕከል በተለያዩ አካባቢዮች ትምህርታ ጉባኤ ማከናውን አሳወቀ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።የማእከሉ ስብከተ ወንጌልና ዜማ አገልግ...
17/03/2026

በእለተ ደብረ ዘይት በማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ማዕከል በተለያዩ አካባቢዮች ትምህርታ ጉባኤ ማከናውን አሳወቀ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

የማእከሉ ስብከተ ወንጌልና ዜማ አገልግሎት ዋና ክፍል ዲ/ን ኃይሌ እንደገለጹት ትምህርታዊ ጉባኤው በሥትራቴጅክ እቅዱ ከያዛቸው የጠፉትን ለመመለስ፣ ያመኑትን ለማጽናት እና የአጽራረ ቤተክርስትያን እንቅስቃሴ ለመግታት ዓላማ ያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

ትምህርታዊ ጉባኤው በሀብሮ ወረዳ በበልበልቲ ደብረ ጽጌ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ፣ በቦኬ ኦዳ ቡልቱም ወረዳ ኢልፈታ መድኃኒአለም ቤተ ክርስትያን፣ በተለያዩ ስብከት ኬላዎች፣ በካረፈርሾ በገንደ ልቦ፣ በቦኬ ጉዶ፣ በጃንቦ እና በመሳሰሉት አካባቢዎች መሆኑን አሳውቀዋል።

በመጨረሻም ማኅበሩ በሥብከተ ወንጌል ለሚያከናውናቸው አገልግሎት መደገፍፍ የምትፈልጉ ኦርቶዶክስሳውያን ጭሮ ባህርዳር አካባቢ በሚገኘው የማዕከሉ ጽህፈት ቤት በአካል በመገኘት መደገፍ ትችላላችሁ። ለበለጠ መረጃ በ0928575859 ወይም0928526102 ይደውሉ። የማእከሉ ሒሳብ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000023696798

Address

Asebe Teferi

Telephone

+251255511626

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ማዕከል ሚዲያ Waldaa Qulqullootaa Wiirtuu Ciroo posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to ማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ማዕከል ሚዲያ Waldaa Qulqullootaa Wiirtuu Ciroo:

Share