ማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ማዕከል ሚዲያ Waldaa Qulqullootaa Wiirtuu Ciroo

ማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ማዕከል ሚዲያ  Waldaa Qulqullootaa Wiirtuu Ciroo Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ማዕከል ሚዲያ Waldaa Qulqullootaa Wiirtuu Ciroo, Religious Center, Asebe Teferi.

14/08/2026

አሳዛኝ ዜና
በአሰቦት ደብረ ወገግ ቅድስት ሥላሴና አቡነ ሳሙኤል አንድነት ገዳም ባልታወቁ ኃይሎች አንድ መነኩሴ አባት አንገታቸው ላይ በጬቤ ተወጉ ።
✝✝✝✝✝✝✝✝✝✝✝✝✝✝
✍ የገዳሙ አገልጋይ በሆኑት አባ ተክለ ዮሐንስ ደረሰ በተባሉ አባት በእንጨት ለቀማ ላይ እያሉ ዛሬ ነሐሴ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 5:30 አካባቢ አደጋው እንደደረሰ ለሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት መረጃውን ገዳሙ አድርሶናል።

✍ ታጣቂዎቹ አባ ተክለ ዮሐንስ ደረሰ የተባሉ አገልጋይ መንኩሴ አባት በአሰቃቂ ሁኔታ ጉሮሯቸውን ወግተው ለመግደል ሲሞክሩ ለማምለጥ የቻሉ ሲሆን ገዳሙም በህይወትና በሞት መካከል ያሉትን አባት ወደ ህክምና የወሰዱ መሆናቸውን ገልጸው እየደረሰባቸው ያለውን ተደጋጋሚ ጥቃት ለሚመለከታቸው አካላት መረጃውን አድርሱልን በማለት አቅርበዋል።

✍ የሀገረ ስብከቱም ጽ/ቤት በአሰቦት ደብረ ወገግ ቅድስት ሥላሴና አቡነ ሳሙኤል አንድነት ገዳም ተደጋጋሚ ጥቃቶችና ችግር እንዲቀረፍና ገዳማውያኑም በተረጋጋ ሁኔታ እንዲኖሩና ለሀገር እንዲፀልዩ የመንግስት የፀጥታ አካላት መፍትሄ እንዲሰጥና ክትትል እንዲያደርግ ለሚመለከተው የዞኑ የፀጥታ አካላት የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ እንጦንስና የሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት ሪፖርት በማድረግ ክትትል እያደረጉ መሆኑን ይገልጻል።

ነሐሴ 8/2018 ዓ/ም

ጭሮ - ኢትዮጵያ
መረጃው የምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ገጽ ነው

ማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ማዕከል ያሰለጠናቸውን 33 ሰባኪያነ ወንጌል  አስመረቀ።—————————————————-ሐምሌ ፳፯/፳፻፲፰ ዓ.ም ጭር (አሰበ ተፈሪ)ማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ማዕከል ያሰለጠናቸውን...
03/08/2026

ማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ማዕከል ያሰለጠናቸውን 33 ሰባኪያነ ወንጌል አስመረቀ።
—————————————————-
ሐምሌ ፳፯/፳፻፲፰ ዓ.ም ጭር (አሰበ ተፈሪ)

ማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ማዕከል ያሰለጠናቸውን 33 ሰባክያነ ወንጌል በብጹዕ አቡነ እንጦስ የምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ቡራኬ በደብረ ጽ/ ቅድስት ልደታ ለማርያም ካቴድራል አስመረቀ።

በመርሐግብሩ የተገኙት ብጹዕ አቡነ እንጦስ ወንጌልን ለተጠሙ ሁሉ በጥበብ መስበክ አለባችሁ። በዚህ ዓለም ስትኖሩም እንደ እባብ በጥበብ እንደ ርግብ በየዋህነት መሆን አለበት። ወንጌል ባልደረሰበት በገጠሪቱ ላለች ቤተ ክርስትያን እንድታስትምሩ የሠለጠናችሁ ስለሆናችሁ በትጋት በትግስት እና በጥበብ ማገልገል አለባችሁ ምክንያቱም ቅዱስ ወንጌል በጥበብ በትግስት በየዋህነት የሚሰበክ ነው።
ማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ማዕከል ስብከተ ወንጌልን በሀገረ ስብከቱ ለማስፋፋት ከሚተግብራቸው አገልግሎት አንዱ ሰባኪያነ ወንጌል አሰልጥኖ ማሰማራት ሲሆን ሠልጣኞቹ በምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት የስብከተ ወንጌል ባልደረሰበት አካባቢዎች ተዘዋውረው ወንጌልን የሚያስተምሩ መሆናቸውን የገለጹት የማዕከሉ ስብከተ ወንጌል እና ዜማ አገልግሎት ዋና ክፍል ኃላፊ ዲ/ን ኃይሌ አክሎግ ናቸው።
አክለውም ሰልጣኞቹ የአገልጋይ እጥረት ካሉባቸው አካባቢዎች የተመለመሉ የሠለጠኑ ሲሆኑ የስብከተ ወንጌል አገልግሎት ባልደረሰበት ቦታ የጠፋትን በመመለስ ያመኑትን በማጽናት ያላመኑትን እንዲያሳምኑ የቤተ ክርስትያንን ተልዕኮ እንዲፈጽሙ አሳስበዋል። የቤተክርስትያን ሕይወት መስቀል ነውና ከራሳችሁ ይልቅ ቤተ ክርስትያንን አስቀድሙ በማለት በማኅበሩ ስም አድራ ብለዋል።
በመጨረሻም ለስልጠናው በገንዘባቸው በእውቀታቸው እና በጊዜቸው አስተዋጽኦ ላደረጉት ስልጠናውን ለሰጡት መምህራን በማኅበሩ ስም ምስጋና አቅርበዋል።

Gamtaan Manneen Barnoota Sanbataa Mana Lubummaa Harargee Lixaa-manneen barnootaa sanbataa qindeessuf barsiisota bakka bu...
02/08/2026

Gamtaan Manneen Barnoota Sanbataa Mana Lubummaa Harargee Lixaa-manneen barnootaa sanbataa qindeessuf barsiisota bakka bu'an sadarkaa mana lubummaatti leenjisaa ture yeroo sadaffaaf eebbise jiraa.
የምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤት ማደራጃ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በሀገረ ስብከት ደረጃ ለ3ኛ ጊዜ ሲያሰለጥናቸው የቆዩ ተተኪ መምህራንን አስመረቀ።
✝✝✝✝✝✝✝✝✝✝✝✝✝✝✝✝
✍ በምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ ቤት ማደራጃ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ለ5ቀናት በመንበረ ጵጵስና ቅድስት ልደታ ቤተ ክርስቲያን ለ3ኛ ጊዜ ሲሰጠው የቆየውን የተተኪ መምህራን ስልጠና የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ እንጦንስ በተገኙበት አስመረቀ።
✍ ሥልጠናው ከ 9 ወረዳ ቤተ ክህነት የተውጣጡ 200 ያህል የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች የተካፈሉበት እንደሆነ፣ ሥልጠናው ታች በወረዳ እና በአጥቢያ ደረጃ የሰ/ት/ቤቶችን አገልግሎት የሚያሳድግ ሥርዓተ ትምህርት ትግበራውን የሚያሳልጥ መሆኑን የሀገረ ስብከቱ የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ ክፍል ሓላፊ መጋቤ ሥርዓት ቀሲስ ዘነበ ብርሃኑ ተናግረዋል። ይህ የሀገረ ስብከት ስልጠና በአዲስ አበባ ለሚደረገው የሀገር አቀፍ የአሰልጣኝ መምህራን ስልጠና መመልመያ አንዱ መድረክ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የሀገረ ስብከቱ ሰ/ት/ቤቶች አንድነት ተቀዳሚ ም/ሰብሳቢ መ/ር መኮንን አብዩ ናቸው።
✍ ሥልጠናው የተሰጠው ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምርያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በተወከሉ ኹለት መምህራን ነው። ይኸ ሥልጠና በሀገር አቀፍ አንድነቱ በዘንድሮው ዓመት ሀገረ ስብከቶች እንዲያሳኳቸው ከሚጠበቁ እና እንደ ዕቅድ ተይዞ ከሚሠራባቸው የሥልጠና ማዕከላት አንዱ እንደሆነ በምርቃት መርሐ ግብሩ የተገኙትና ሥልጠናውን የሰጡት፣ የሀገር አቀፍ ሰ/ት/ቤቶች አንድነት ሥርዓተ ትምህርት አስተባባሪ መ/ር ሚኪያስ ግዛቸው ገልጸዋል።
✍ አያይዘውም ሥልጠናው ሥርዓተ ትምህርት ትግበራ፣ የመምህራን ክህሎት ግንባታ፣ የክፍላተ ትምህርት ገለጻ ላይ ያተኮረ ሀገረ ስብከት አቀፍ ስልጠና እንደሆነ ተናግረዋል።
✍ በምርቃት መርሐ ግብሩ የ5ቀኑ የሥልጠና ሪፖርትና የሀገረ ስብከቱን አንድነት የሥርዓተ ትምህርት ትግበራ አካሔድ እና ሥልጠናውን በተመለከተ 12 ያህል የአቋም መግለጫ በማውጣት፣ ሰልጣኞችን ለላኩ እና በሥልጠናው ለተሳተፉ ተተኪ መምህራን የምስክር ወረቀት በመስጠት የጉባኤው ፍጻሜ ሆኗል።

ዘገባው ፦ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት

ሐምሌ 26/2018 ዓ.ም

ጭሮ- ኢትዮጵያ

ማዕከሉ 23ኛ ጠቅላላ ጉባዔውን አካሔደ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።፣፣፣።።ሐምሌ ፳፮ቀን ፳፻፲፹ ዓ.ም  ጭሮ (አሰበ ተፈሪ)ማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ማዕከል 23ኛ ጠቅላላ ጉባዔውን ...
02/08/2026

ማዕከሉ 23ኛ ጠቅላላ ጉባዔውን አካሔደ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።፣፣፣።።
ሐምሌ ፳፮ቀን ፳፻፲፹ ዓ.ም ጭሮ (አሰበ ተፈሪ)

ማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ማዕከል 23ኛ ጠቅላላ ጉባዔውን ከሐምሌ ፳፭-፳፮ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም የምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ እንጦንስ በተገኙበት በሀገረ ስብከቱ መሰብሰቢያ አዳራሽ አካሔደ።
ብጹዕነታቸው ማኅበሩ ለቤተ ክርስቲያን እየሰጠ ያለውን አገልግሎት ጠቅሰው በተለይ በውጪው ዓለም ለቤተ ክርስቲያን መስፉፉት ያደረገውን አስተዋጽኦ ገልጸዋል ። ስለሆነም ይህንኑ እና መሰል አገልግሎቱን አጠናክሮ እንዲቀጥል በማሳሰብ ብጹዕነታቸው የሚመሩት የምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከትም ለማኅበሩ አገልግሎት አስፈላጊውን እገዛ እንደሚያደርግ ተናግረዋል።

በጉባኤው የወረዳ ማዕከላት ተወካዮች አጋር አካላት ተገኝተዋል።
በጉባኤው የማዕከሉ የ2018 ዓ.ም የአፈጻጸም ሪፖርት ፣ የኦዲት እና የክዋኔ ኦዲት የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤት ሪፖርቶች በየተራ ቀርበው አስተያየት ተሰጥቶባቸው እንዲጸድቁ ተደርጓል። በሁለተኛ ቀን የጉባዔው ውሎ ከዋናው ማእከል በመጣ አጀንዳ ተሳታፊዎች በቡድን እና በተናጠል ውይይት ተደርጓል። የማዕከሉ የ2019ዓ.ም እቅድ በማዕከሉ ሰብሳቢ ዲ/ን ዳንኤል ሞገስ እንዲሁም የኦዲት ክፍል እቅድ በአቶ ሣሙኤል አግዜ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበት የጸደቀ ሲሆን የማጠቃለያ አስተያየቶች ከተሰጡ በኋላ የጉባኤው ፍጻሜ ሆኗል።

13/07/2026
ሦስቱ ወረዳ ማእከላት ጠቅላላ ጉባኤያቸውን አካሔዱ::================================ ማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ፳፱/፲/፳፻፲፰ ዓ.ምበማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ (አሰበ ተፈሪ)ማዕከል ...
06/07/2026

ሦስቱ ወረዳ ማእከላት ጠቅላላ ጉባኤያቸውን አካሔዱ::
================================

ማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ፳፱/፲/፳፻፲፰ ዓ.ም

በማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ (አሰበ ተፈሪ)ማዕከል መቻራ ወረዳ ማዕክለ ፣ቦኬ ወረዳ ማዕከል እና ዶባ ወረዳ ማዕከል በቀን ፳፰/፲/፳፻፲፱፰ዓ.ም ጠቅላላ ጉባኤያቸውን አካሔዱ ። በጠቅላላ ጉባኤው የወረዳ ማእከላቱ የአፈጻጸም ሪፖረት እና የቀጣይ ዓመት እቅዶች ቀርበው ከውይይት በኋላ ጸድቀዋል።

በጠቅላላ ጉባኤው የወረዳ ማእከሉ አባላት የአብያተ ክርስቲያናት አስተዳዳሪዎች ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል ። በሦስቱም ወረዳ ማዕከላት ጠቅላላ ጉባዔ ከጭሮ ማእከል የተወከሉ ልዑካን ከዋናው ማዕከል እና ከጭሮ ማዕክል የተላኩ መልእክታትን አቅርበው ባኤያቱ በጸሎት ተፈጽመዋል።

ማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ (አሰበ ተፈሪ )ማዕክል ሲያስተምራቸው የነበሩ የጊቢ ጉባዔ ተማሪዎችን አስመረቀ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።በጭሮ ማአዕክል ስር ሲማሩ የቆዩት የኦዳ ቡ...
28/06/2026

ማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ (አሰበ ተፈሪ )ማዕክል ሲያስተምራቸው የነበሩ የጊቢ ጉባዔ ተማሪዎችን አስመረቀ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

በጭሮ ማአዕክል ስር ሲማሩ የቆዩት የኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ ጊቢ ጉባዔ ተማሪዎች ተመረቁ ።
የማዕከሉ ጊቢ ጉባዔ አገልግሎት ዋና ክፍል ኃላፊ አቶ መስፍን ባሕሩ ተማሪዎቹ በተለያዩ ፊልዶች የሰለጠኑ መሆናቸውን ገልጸዋል። ያስመረቅናቸዉ 24 ተማሪዎች ከ4 እስከ 5 ዓመታት በጊቢ የቆዩ ሲሆን ከዓለማዊ ትምህርታቸው ጎን ለጎን በማኅበሩ የሚሰጣቸውን መንፈሳዊ ትምህርት በጥሩ ሁኔታ ማጠናቀቃቸውን ገልጸዋል።

ከተመራቂዎች መካከል ሜሮን ኃ/ሚካኤል
አጠቃላይ ከግቢ ከሴቶች አንደኛ በመውጣት ዋንጫ እና ከኮሌጅ አንደኛ በመውጣት ሜዳሊያ (Midwifery)ተሸላሚ ሆናለች ። ሌላኛዋ ተመራቂ ፍቅር ባዚ በElectrical Enginering በሴቶች ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆናለች

የጭሮ ማዕከል ሰብሳቢ ዲ/ን ዳንኤል ሞገስ በምረቃ መርሐ ግብር ላይ ተገኝተው ለተመራቂዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት አስተላልፈዋል።
ሰኔ ፳፩ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም

ማኅበረ ቅዱሳን በዴሳ ወረዳ ማእከል ጠቅላላ ጉባዔውን አካሔደ። ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።ማኅበረ ቅዱሳን በዴሳ ወረዳ ማእከል ጠቅላላ ጉባኤውን ዛሬ ሰኔ ፳፩ ቀን ፳፻፲...
28/06/2026

ማኅበረ ቅዱሳን በዴሳ ወረዳ ማእከል ጠቅላላ ጉባዔውን አካሔደ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

ማኅበረ ቅዱሳን በዴሳ ወረዳ ማእከል ጠቅላላ ጉባኤውን ዛሬ ሰኔ ፳፩ ቀን ፳፻፲፰ ዓ. ም
የወረዳ ማዕከሉ አባላት የግንኙነት ጣቢያዎች ተወካዮች እንዲሁም ካህናት እና ምእመናን አጋር አካላት በተገኙበት አካሔደ። በወረዳ ማዕከሉ ሰብሳቢ ዲ/ን ተስፉ ወንዱ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክት ከተላለፈ በኋላ የ፳፻፲፰ ዓ.ም የወረዳ ማዕከሉ አፈጻፀም ሪፖርት የኦዲት እና ኢንስፔክሽን እንዲሁም የአቡነ ጎርጎርዮስ ት/ቤት ሪፖርት በየተራ የቀረቡ ሲሆን ውይይት ተደርጎባቸው ጸድቀዋል።

በጉባኤው ከጭሮ ማዕከል በተገኙት ተወካይ ቀሲስ ዳዊት በላይነህ ስብከተ ወንጌል ከተሰጠ በኋላ ከዋናው ማዕከል የተላከ አጠቃላይ የማኅበሩ የዚህ አመት አፈጻጸም ሪፖርት በንባብ ተሰምቷል። በማስከተልም የወረዳ ማዕከሉ የ፳፻፲፱ ዓ.ም እቅድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበት በማጽደቅ የጉባኤው ፍጻ ሜ ሆኗል ።
ሰኔ ፳፩ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም

ማኅበረ ቅዱሳን በምዕራብ ሐረርጌ ዞን የተለያዩ ቦታዎች ለሚገኙ ተፈናቃዮች  አስቸኳይ የምግብ ግብዓቶች ድጋፍ አደረገ። EOTCMK Chiro ሰኔ 20 ቀን 2018 ዓ.ም የማኅበረ ቅዱሳን ሙያ፣...
27/06/2026

ማኅበረ ቅዱሳን በምዕራብ ሐረርጌ ዞን የተለያዩ ቦታዎች ለሚገኙ ተፈናቃዮች አስቸኳይ የምግብ ግብዓቶች ድጋፍ አደረገ።

EOTCMK Chiro ሰኔ 20 ቀን 2018 ዓ.ም

የማኅበረ ቅዱሳን ሙያ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት በምዕራብ ሐረርጌ ዞን በአሰቦት በዶባ እና በመቻራ ለሚገኙ ተፈናቃዮች ከ1 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የሆነበት አስቸኳይ የምግብ ግብዓቶች ድጋፍ አድርጓል።

ባለፉት ጊዜያት በምዕራብ ሀረርጌ ዞን በሚገኙ አንዳንድ አካባቢዎች በጸጥታ ችግር ምክንያት ከመኖሪያ ቀዬአቸው የተፈናቀሉ ከ400 የሚልቁ ወገኖች በተለያየ ሁኔታ ከማኅበረሰቡ ጋር ተጠልለው እንደሚገኙ መረጃዎች ያሳያሉ።

ይህንንም ችግር የተረዳው ማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ (አሰበ ተፈሪ) ማእከል ሰኔ 18እና19 ቀን 2018 ዓ.ም በቦታው በመገኘት ከ1.2 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የሆነበት ከ100 ኩንታል በላይ የማሽላ ምግብ በድጋፍ አድርጓል ። በርክክብ ወቅትም የማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል የተላኩ ተወካዮች የማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ማእከል ጽ/ቤት ኃላፊ ቀሲስ ዳዊት በላይነህ በጋራ ተገኝተው ድጋፉን ለተጎጅዎች እጅ በእጅ አስረክበዋል። የምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ እንጦንስ ለተፈናቃዮች የተደረገውንእርዳታ አስመልክተው ማኅበሩን አመስግነዋል የሀገረ ስብከቱ ዋና ስራ አስኪያጅ ሊቀ ኅሩያን ቆሞስ አባ ፍቅረ ዮሐንስ ብርሃኑም ይህንን ዘመን ተደጋግፎ ማለፍ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸው ለወገኖቻችን ለተደረገው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ይህ ድጋፍ የተደረገው በሀገረ አሜሪካ ከሚገኘ ኦርቶዶክሳውያን በተገኘ የገንዘብ እርዳታ የተሸፈነ መሆኑ ተገልጿል።

ለተፈታኞች የስነ ልቡና ዝግጅት ምክር ተሰጠ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።ማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ማዕከል አቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤት የ6ኛ ክፍል ሚኒስትሪ ፈተና ለሚፈተኑ...
13/06/2026

ለተፈታኞች የስነ ልቡና ዝግጅት ምክር ተሰጠ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

ማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ማዕከል አቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤት የ6ኛ ክፍል ሚኒስትሪ ፈተና ለሚፈተኑ ተማሪዎች የስነ ልቡና ዝግጅት ስልጠና ተሰጣቸው።
ተማሪዎቹ ለሦስት ቀናት በጸሎት የቆዩ ሲሆን ዛሬ በማጠቃለያው ፈተናውን ተረጋግተው በማስተዋል ሆነው እንዲሰሩ ምክር እና ስልጠና ተሰጣቸው።
በመርሐ ግብሩ የት/ቤቱ የቦርድ አባላት ርእሳነ
መምህራን እና መምህራን ተገኝተው የማበረታቻ ምክር ለተማሪዎቻቸው ሰጥተዋል።

Address

Asebe Teferi

Telephone

+251255511626

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ማዕከል ሚዲያ Waldaa Qulqullootaa Wiirtuu Ciroo posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to ማኅበረ ቅዱሳን ጭሮ ማዕከል ሚዲያ Waldaa Qulqullootaa Wiirtuu Ciroo:

Shortcuts

Share